ስለ ይዞታ እና የቀዳሚነት ግዥ ይገባኛል የማለት መብት

በዚህ አጭር ጽሁፍ የይዞታ ትርጉም ምን እንደሆነ፣ ይዞታን መሰረት ያደረገ የሁከት ይወገድልኝ ክስ በምን አግባብ ሊቀርብ እንደሚችልና ይህ ክስ ከባለቤትነት ክርክር ጋር ያለው ልዩነት ምን እንደሆነ፣ ሁከት ይወገድልኝ የሚል ክስ ሲቀርብ ፍርድ ቤቶች የሚይዙት ጭብጥ በተመለከተ ዳሰሳ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቀዳሚነት ግዥ ይገባኛል የማለት መብት ትርጓሜው ምን እንደሆነና ቀዳሚ የመግዛት መብት ካለው መሀከል ባልና ሚስትን፣ ወራሾችን በተመለከተ በህጉ ሊስተናገዱ የሚችሉበት አግባብ ለማየት ተሞክሯል፡፡ በስተመጨረሻም የቅድሚያ ግዥ መብት ያለው ሰው በሚገዛበት ጊዜ ስላለው የሽያጭ ስነ-ስርዓት፣ ግድግዳና ጣራቸው በአንድ በኩል የተያያዙ ቤቶችን በተመለከተ በቅድሚያ ግዥ መብት ሊስተናገዱ የሚችሉበት የህግ አግባብና የዘመዶች በቅድሚያ የመግዛት መብትን እስመልክቶ በጽሁፍ በወፍ በረር ቅኝት ተደርጎበታል፡፡ 

  6074 Hits

በሠራተኛ ቅጥር ሂደት ስለሚፈፀም የኋላ ታሪክ ፍተሻ፣ አስፈላጊነት እና ሕጋዊነት

መግቢያ

በዚህ የውድድር ዘመን አሰሪዎች ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት ወይም ምርት በጥራት እና በፍጥነት ለደንበኞቻቸው ማቅረብ ይገባቸዋል። ከዚህም ባለፈ አንዳንድ ሙያዎች በባህሪያቸው በአደራና እምነት ላይ የተመሰረቱ (positions of trust) ስለሆነ ሰራተኛው ለዚህ የሥራ መደብ የተገባ መሆን ይገባዋል።  በመሆኑም አሰሪዎች መልካም ስማቸውን ጠብቀው የገበያ ተወዳዳሪነታቸውን ለማሳደግ በቴክኖሎጂ እና በሰለጠነ የሰው ሃይል ተቋማቸውን ያጠናክራሉ። ሆኖም ግን የሰው ሃይል ቅጥር በሚፈፅሙበት ወቅት ከግለሰብ የግል ባህሪ እና በዲጅታል ቴክኖሎች መሳሪያዎች ሀሰተኛ ሰነድ ለማዘጋጀት ከመቼው ጊዜ በላይ ለመለየት በሚያስቸግር መልኩ ረቂቅ፣ በቀላሉ የሚገኝና ተግባር ላይ የሚውል በመሆኑ የቅጥር መስፈርቱን የማያሟላ እና ለስራው ትክክለኛና ተገቢ ያልሆነው ስራተኛ እንዲቀጥሩ በማድረግ ከገበያ ተወዳዳሪነት የሚያስወጣ የስጋት ተጋላጭነታቸውን አሳድጎታል።

  4905 Hits

ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃ (Provisional Interim measure) እና የፍርድ ቤት ሥልጣን

ይህ ጽሑፍ በግልግል ወይም በእርቅ የሚታዩ ጉዳዮችን ተከትሎ የሚሰጡ ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃዎች ወይም ትዕዛዝ ያላቸዉን የሕግ ማዕቀፍ እና ተግባራዊ አፈጻጸም የሚዳስስ ነዉ፡፡

በሕጉ ዘርፍ በአብዛኛዉ  ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃ (Provisional Interim measure) ሀሳብ ከግልግል ዳኝነት ሂደቶች ጋር ተያይዞ የሚነሳ  እንደሆነ ብዙ ድርሳኖች  ያወሳሉ፡፡ የብላክስ ሎዉ መዝገብ ቃላትም  ጊዜያዊ የመጠባበቂያ ትዕዛዝን ከዓለም ዓቀፍ የግልግል አሰራር ጋር በማገናኘት ትርጉም የሚሰጠዉ ሲሆን የግልግል ፍርድ ቤት  የሙግቱን ዉጤት ሊጎዳ የሚችልን ያልተገባ ተግባር ለመከላከል ከፍርድ በፊት የሚሰጠዉ ትዕዛዝ እንደሆነና በብሔራዊ ሕጎች ከሚሰጠዉ ጊዜያዊ የእግድ ትዕዛዝ (temporary injunction) ጋር አቻ እንደሆነ ይገልፀዋል፡፡ 

  5807 Hits

የዋስትና መብት መከበር ላይ በፖሊስ የሚቀርብ የይግባኝ ጥያቄ ህጋዊ አንድምታው ሲገመገም

መግቢያ

በኢፌዲሪ ህገመንግስትም ይሁን ኢትዮጵያ በአፀደቀቻቸው አለማቀፋዊ የሰበዓዊ መብት ስምምነቶች እንዲሁም በሌሎች አዋጆች ላይ የተቀመጡ አያሌ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተፈፃሚነት እንዲኖራቸው በህግ እና በስርዓት የሚመሩ፤ ዋና ግባቸው እና የሥራ መለኪያቸው ህግ እና ሥርዓትን ማስከበር የሆኑ ተቋማት መኖራቸው ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ቅድመ ሁኔታ ነው። እነዚህ ተቋማት እርስ በራሳቸው በሚኖራቸውም ግንኙነት ግልፅ የሆነ የሚና ወይም የተግባር ልዩነት ሊኖራቸው የተገባ መሆኑም የሚታመን ነው። በዚህ መርህ ውስጥ የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች አፈፃፀምን በሚመለከት ቀዳሚ ኃላፊነት ከተሰጣቸው የመንግስት አካላት ውስጥ በተለይም የህግ አስፈፃሚው እና የህግ-ተርጓሚው ሚና በእጅጉ የሚልቅ ነው። እነዚህ ተቋማት በሌሎች ሀገራት ላይ ያላቸው መስተጋብር እና ጤናማ የሆነ ውድድር የዜጎች የሰብዓዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በተሻለ እንዲከበሩ አስተዋፅኦ አድርጓል።

  8359 Hits

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here)

The arbitration agreement is an indispensable precondition for domestic and international commercial arbitration.  This is due to the fact that an arbitration contract is a process through which parties in dispute freely appoint their own private judge in lieu of a state judge to settle their dispute.  Nonetheless, whether the parties are at liberty to set all matters as they like, including the law(s) that will be applied to their case, is an issue. On the other hand, whether the arbitrators could settle as per the principle of laws or according to law and whether they have full autonomy to revise or rewrite the arbitration agreement to settle the parties’ dispute is also an issue. Seyoum’s article examines Ethiopian laws from hereinabove mentioned issues’ perspective. 

  7367 Hits

ስለ ወንጀል ተጎጂዎች - የአዲስ ዕይታ አስፈላጊነት በረቂቁ የወንጀል ሕግ የሥነ-ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ላይ

መግቢያ ፡- ተበዳዮች በወንጀል ፍትሕ ሥርዓቱ የነበራቸው የተሳትፎ ሚና፡ ጥቅል ምልከታ

በኢትዮጵያ የወንጀል ተጎጂዎች በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ውስጥ ያላቸው ሚና ከነበረበት የማማ ደረጃ በጊዜ ሂደት ‹‹ከማማ የመውረድ›› ያህል ዝቅ እያለ መጥቷል። ሀገሪቱ በዳግም የኢጣሊያ ወረራ ተፈፅሞባት ከመያዝዋ እ.እ.አ ከ 1935 ዓ.ም በፊት በወንጀል ጉዳት ደርሶባቸው በቀጥታ ተበዳይ የሆኑ ሰዎች ወይም የተበዳይ ተወካይና ቤተዘመዶች በደል ካደረሰባቸው ሰው ፍትሕን በገዛ እጃቸው ያገኙ ነበር። ተበዳይ ጥቃት ያደረሰበትን ሰው ሲፈልግ ይበቀላል፣ ሲፈልግ በፍርድ አደባባይ ይከሳል ወይም ለደረሰበት በደል ከተበዳይ ከሳ ይቀበላል። አይ ይህን ሁሉ አልፈልግም ካለም ከሁሉም ታቅቦ ፍትሕን ከእግዚአብሔር እየጠየቀ ይኖራል። በዚህ ጊዜ ምርመራ አጣርቶ ክስ የሚመሰርት የዐቃቤ ሕግ ተቋም በሀገሪቱ አልነበረም። በግለሰቦች መሀከል የሚፈጠር አለመግባባቶችን ‹‹የወንጀል›› ጉዳይ እና የግለሰቦች የፍትሐብሔር ጉዳይ ብሎ የሚከፋፍል የሕግ ስርአት ባለመኖሩ ጥቂት በሀይማኖትና በመንግስት ላይ የሚፈፀሙ በአሁኑ ሰአት የፓለቲካ ወንጀል እየተባሉ ከሚጠሩ ወንጀሎች በስተቀር ሁሉም አለመግባባቶች ላይ ግለሰቦች በራሳቸው ከሳሽ በመሆን ጉዳያቸውን ለፍርድ ቤት ያቀርባሉ ወይም ፍትሕን በእጃቸው ያገኙ ነበር። ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት የሚወስዱ ከሆነ ክስ የመመስረት፣ የተጀመረን ክስ የሟቋረጥ፣ ቅጣትን በመምረጥ ተበዳይ ግለሰብ ሁሉን አድራጊ ነበር። የወንጀል ይዘት ያላቸው ጉዳዮችን ከፍትሀብሔር ጉዳዮች ጋር በማጣመር የጉዳት ካሳን መጠየቅም ይቻል ነበር። በዘመኑ የወንጀል ተበዳዮች በወንጀል ጉዳይ የሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች ነበሩ።

  6603 Hits

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።

  5635 Hits

የግልግል ስምምነት /Arbitration Agreement/ እና የፍርድ ቤቶች ሥልጣን

ከረጅም ጊዜ በኋላ ይህንን የጻፍኩት በቅርቡ ባነበብኩትና ሰበር የግልግል ስምምነትና የፍርድ ቤቶች ሥልጣንን አስመልክቶ በሰጠው ውሳኔ ላይ የተወሰነ ሐሳብ መስጠት ስለፈለኩ ነው፡፡ ለዚህ ጽሑፍ ብቻ የሚጠቅመኝን የውሳኔ ክፍል በማውጣት እጠቀማለሁ እንጂ ሁሉንም ፍሬ ሐሳብ አልዳስስም ነገር ግን ማንበብ ለሚፈልግ ሰው ውሳኔው ያለበት ቅጽና መዝገብ ቁጥር አስቀምጣለሁ (ቅጽ 25 መ.ቁ 180793)፡፡

  9433 Hits

ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

በፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 ከአንቀጽ 2 እስከ 4 በተጠቀሱት ድንጋጌዎች  ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣ በኃይማኖት እና በባሕል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ መፈጸሚያ ስርዓቶች ውስጥ በአንደኛው ስነ-ስርዓት ጋብቻ የተፈጸመ እንደሆነ በጥንዶቹ መካከል በሕግ እውቅና የተሰጠው የትዳር ግንኙነት ተመስርቷል ይባላል፡፡ ጥንዶቹ ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት የጋብቻ መፈጸሚያ መንገዶች ውስጥ በአንዱ ጋብቻ ቢፈጽሙ የጋብቻ ውጤትን መሠረት በማድረግ በሕግ የጋራ እና የግል ንብረቶቻቸው ላይ የሚኖረው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡  

  25135 Hits

የወንጀል ምርመራና የፍርድ ቤቶች ሚና

መግቢያ

አንድን የወንጀል ተግባር በሕግ አግባብ አጣርቶና መርምሮ ወደ ፍርድ ሂደቱ ለማስገባትና ውሳኔ ለማሰጠት አስቀድመው ከሚከናወኑ ዐበይት ተግባራት መካከል የመጀመሪያው የወንጀል የምርመራ ሥራ ነው። በመሰረታዊነት የወንጀል የምርመራ ተግባርን የማከናወን ኃላፊነትና ሥልጣን የፖሊስና የዐቃቤ ሕግ መሆኑ ቢታወቅም በብዙ የሂደቱ ደረጃዎች ፍርድ ቤቶች ያላቸው ሚና ላቅ ያለ መሆኑም የሚታወቅ ነው። መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪውን በሕግ አግባብ መያዙን፣ ከያዘውም በኋላ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ፍርድ ቤት ማቅረቡን፣ የአቆያየት ሁኔታውን በተመለከተም በአግባቡ አይቶና መርምሮ ተገቢ ናቸው ያላቸውን ሕጋዊ ትዕዛዛትና የማስረጃ አሰባሰብ ጉዳዮችን (ለምሳሌ፡- የቀዳሚ ምርመራ፣ የመያዣና የብርበራ ትዕዛዛት…) ኹሉ በበላይነት በመምራትና በመቆጣጠር የግለሰቦችንና የህዝብን መብትና ጥቅም የማስከበር ኃላፊነት አለባቸው።

  10102 Hits