Brief summary major reforms introduced by Movable Property Security Rights Proclamation, No.1147/2019

 

Introduction

Before the enactment of movable property security right proclamation, Ethiopian movable security right law is ultimately unsatisfactory because it is fragmented, and contained in four different pieces of legislation: The Civil and Commercial Codes, the Business Mortgage Proclamation, the Proclamation to Provide for a Warehouse Receipts System (Warehouse Receipts Proclamation), and the Capital Goods Leasing Business Proclamation. Under this system, security rights in many movable assets are not registered.

Continue reading
  5576 Hits

በገጠር መሬት የመጠቀም መብትን በዋስትና ማስያዝና አርሶ አደሩ

 

መሬት ካለው ተፈጥሮዋዊ ባሕርይም ሆነ ግዙፍነት የተነሳ በሃገራችን ፖለቲካል ኢኮኖሚ ማዕከል ሆኖ እስካሁን ዘልቋል፡፡ በተለይም አብዛኛው ሕዝብ በእርሻ  የሚተዳደር ባለበት ሃገር የመሬት ጉዳይ የኢኮኖሚያዊ መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካዊ የሆነ ጠቀሜታ አለው፡፡ የሃገሪቱን የመሬት ስሪት (land tenure) ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከተው በእያንዳንዱርዓት የተለየ ባሕርይ ይዞ እናገኘዋለን፡፡

1966 . በፊት የነበረው የመሬት ስሪት የራሱ ሆነ ባሕርይ የነበረው ሲሆንየርስት ጉልትግንኙነትን ያማከለ ነበር፡፡ መሬት በአብዘኛው የቤተ ክርስቲያን ይዞታ፣ የርስት ጉልት ይዞታ በሚል የተከፋፈለ ነው፡፡ ይህ የመሬት ስሪት በሃገሪቱ አብዛኛውን ክፍል በሚሸፍነው እና መተዳደሪያ መሬት ያለውን አርሶ አደሩን የሚያገል፣ የባለቤትነትም ሆነ የመጠቀም መብትን ዋስትና በማይሰጥ መልኩ የተዋቀረ እንደመሆኑ መሬት በጥቂቶች እጅ እንዲሆን ያደረገ ነበር፡፡

1966 . ተከትሎ የመጣው ለውጥ ቀደም ሲል የነበረውን የርስት ጉልት ግንኙነት በመሻር በመሬት ላይ አዲስ መዕራፍ ከፍቷል፡፡ በጊዜው ወደ ሥልጣን የመጣው የደርግ ሥርዓት ይከተል በነበረውን የሶሻሊስት ርዮተ ዓለም በመመራት ኢኮኖሚውን የሚመሩትን ዋና ዋና ነገሮች ከግል ባለቤትነት ወደ ሕዝብ ባለቤትነት ሲያሸጋግር መሬትም የገጠር መሬትን የሕዝብ ኃብት ለማድረግ በሚል አዋጅ ቁጥር 31/67 የሕዝብ ኃብት በሚል ታወጀ፡፡ አዋጁም መሬት አይሸጥም አይለወጥም የሚለውን ጥብቅ የሆነና የመሬት ጉዳይን ከሌሎች ንብረቶች የሚለየውን ገደብ ይዞ ብቅ ብሎ ነበር፡፡ 

ምንም እንኳን እንደ አዲስ የተደረገው የመሬት ስሪት ለውጥ ከገባር ሥርዓት አውጥቶ ወደ ሕዝብ ያሸጋገረ ክስተት ቢሆንም መሬት ተጠቃሚውን መብት ያጣበበ ነበር፡፡ የገጠር መሬትን የሕዝብ ለማድረግ በወጣው አዋጅ ቁጥር 31/67 አንቀጽ 5 አንድ የመሬት ተጠቃሚ  በይዞታ የያዘውን መብት መሸጥ፣ መለወጥ፣ በስጦታ ማስተላለፍ፣ በማስያዝ፣ በወልድ አገድ ወይም በሌላ ሁኔታ ማስተላለፍ እንደማይችል ገደብ ያስቀምጣል፡፡

Continue reading
  28043 Hits

ስለ ንብረት የዋጋ ግምት ጥቂት ነጥቦች

 

ለፍርድ ቤቶች በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ የንብረትን ትክክለኛ የዋጋ ግምት ማወቅ የግድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያቶች አሉ፡፡ ለመሆኑ የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ያስፈልጋል? የንብረት የዋጋ ግምት ተገምቶ እንዲቀርብ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት የመገመት ኃላፊነት በሕግ የተሰጠው ለማን ነው? በአሠራር ደረጃ የንብረት የዋጋ ግምት በማን እና እንዴት እየተገመተ ይገኛል? የንብረት ዋጋ ግምትን አስመልክቶ የሚታዩ ችግሮች ምንድን ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት ሲሰራ በመሠረታዊነት ሊካተቱ የሚገባቸው ነጥቦችስ ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ፅሁፍ በጥቂቱ እንዳስሳለን፡፡        

  1. የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ይጠቅማል?

የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፡፡ እነዚህም፡ -

  • ፍትሐዊና ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት እንዲቻል፤
  • የፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ሥልጣን ለመወሰን እንዲቻል፤
  • ለፍርድ ቤቶች ተገቢውን የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ለማከፈል፤
  • ጥፋተኛ ተብለው በወንጀል የሚፈረድባቸው ሠዎች ላይ ተመጣጣኝና የተገኘውን ልተገባ የጥቅም መጠን ወይም የደረሰውን የጉዳት መጠን መሠረት ያደረገ ቅጣት ለመወሰን ነው፡፡
  1. ተከራካሪ ወገኖች የንብረት ዋጋ ግምት መጠን እንዲጠቅሱ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው?
  • ክስ የሚቀርበው አንድን ንብረት ለማስለቀቅ ወይም ከአንድ ንብረት ላይ ድርሻ ለመጠየቅ በሆነ ጊዜ ክስ የቀረበበትን ንብረት ወይም የንብረቱን ወይም ከንብረቱ ላይ የሚገኘውን የድርሻ የዋጋ ግምት በክስ አቤቱታ ላይ ሊጠቀስ እንደሚገባ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ 222 /1/ /ቀ/ እና 226 /3/ /4/ ላይ ይጠይቃል፤
  • የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም በወጣው በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 11 /1/ እና 14 መሠረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከብር 500,000.00/አምስት መቶ ሺሕ/ በላይ የሆኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን እንዲሁም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከብር 500,000.00/አምስት መቶ ሺሕ/ በታች የሆኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን አከራክረው የመወሰን ሥልጣን ተሠጥቷቸዋል፡፡ ተከራካሪ ወገኖችም የሚያቀርቡትን የገንዘብ ወይም የንብረት ክርክር የዋጋ ግምት በክሳቸው ላይ መግለፃቸው የፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ሥልጣን የሚወስን በመሆኑ በአዋጁና በሥነ ሥርዓት ሕጉ መሠረት በዳኝነት የሚጠይቁትን የገንዘብ መጠን ወይም የንብረት የዋጋ ግምት የመጥቀስ ግዴታ ተጥሏል፤
  • ስለ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ገንዘብ አከፋፈል በወጣው የ1945 ዓ.ም. አስራ ሁለተኛ ዓመት ቁጥር 15 የሕግ ክፍል ማስታወቂያ ቁጥር 177 መሠረት ከሳሽ የሆነ ወገን ዳኝነት በሚጠይቅበት ገንዘብ መጠን ልክ ለፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ሊከፍል እንደሚገባና ተመኑም ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም አንድን ንብረት አስመልክቶ የፍትሐብሔር ክስ የሚያቀረብ ሠው ለፍርድ ቤቶች የዳኝነት የአገልገሎት ክፍያ አከፋፈል እንዲያመች የንብረቱን የዋጋ ግምት በክስ አቤቱታው ላይ የመግለፅ ግዴታ አለበት፡፡
  • የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባወጣው የተሻሻለው የቅጣት አወሳስን መመሪያ ቁጥር 2/2006 መሠረት በፍርድ ጥፋተኛ በተባሉ ሠዎች ላይ ቅጣትን ለመጣል በወንጀል ድርጊት የተገኘውን የንብረት ጥቅም ግምት ወይም የደረሰውን የንብረት ጉዳት ግምት ማወቅ አስፈላጊ ከመሆኑም ባለፈ የተጠቀሰው ሕግ የንብረት የዋጋ ግምት መጠን ላይ ክርክር ከተነሳበት የዋጋ ግምቱ ተለይቶ እንዲጠቀስና እንዲቀርብ ይጠይቃሉ፡፡    
  1. በሕጉ መሠረት የንብረት የዋጋ ግምት ላይ ክርክር ከቀረበ ግምቱን የሚገምተው ማን ነው? የግምት ሥራውስ እንዴትና በምን መመዘኛ ይሰራል?

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 250 መሠረት ከተከራካሪ ወገኖች መካከል አንደኛው የሚያቀርበውን የዋጋ ግምት ሌላኛው ተከራካሪ ወገን በዋጋ ግምቱ ባለመስማማት ሊቃወም እንደሚችልና የግምት ክርክር ከተነሳ ደግሞ ፍርድ ቤቶች የሀብቱን ወይም የንብረቱን የዋጋ ግምት በመገመት ለፍርድ ቤቱ እንዲያሳውቁ ምትክ ዳኞችን በመሾም ሊያስገምቱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡ 

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ላይ የንብረት ዋጋ ግምት እንዲገምቱ የሚሾሙ ምትክ ዳኞችም የንብረት ዋጋ ግምቱን ምንን መሠረት በማድረግና እንዴት እንደሚከናወኑ የሚያመለክተው ነገር ባይኖርም ምትክ ዳኞቹ የግምት ሥራ ሲሰሩ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 132 እስከ 135 በተመለከቱ ቅድመ ሁኔታዎችና የአሠራር ሥርዓት መሠረት የዋጋ ግምቱን ገምተው ሪፖርት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

Continue reading
  16420 Hits

በፍርድ ከሄደች በቅሎየ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦየ (ለውጥ የሚሹ የፍርድ ቤት ጉዳዮች)


ፍርድ ቤት የበደል ስር የሚቆረጥበት ፤ ተበዳይ የሚካስበት፤ አጥፊ የሚቀጣበትና መንግስት ከህግ በታች መሆኑ የሚረጋገጥበት መድረክ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ፍትህ ከረቂቅነት ከፍ ብላ የምትታይ ፣ የምትሰማ እና የምትዳሰስ ህልው መሆኗ የሚታወቅበት አደባባይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት የሰለጠነ ህዝብ የኔ የሚለውን ህግ የሚያስከብርበት መሳሪያ ነው፡፡ ህይወቱ ፣ ንብረቱና የኔ የሚላቸው እሴቶቹ ሁሉ ጥበቃ ያላቸው ስለመሆኑ የሚተማመንበት ዋሱ ነው ፍርድ ቤት፡፡


የምትታሰረው ፣ የምትፈታው፣ ከአታላዮች ገንዘብህን የምታስመልስው፣ ስሜ አስጠላኝ ልቀይር ፣ ትዳር ከበደኝ ልፋታ ካልክ መሄጃህ ፍርድ ቤት ነው፡፡ ሞት የሚፈርደብህ፣ ቀሪ ዘመንህን በአንድ የተከለለ የቆርቆሮ ግቢ ውስጥ በጥበቃ ስር ሆነህ እንድታሳልፍ የምትገደደውም በፍርድ ቤት ነው፡፡ ተበድያለሁ ልካስ ፣ በድሏል ይቀጣ ፣ የመናገር ነፃነቴ ይከበር ፣ የመዘዋወር መብቴ ተገደበ ብለህ የምትጮህውም ፍርድ ቤት ነው፡፡ ክብሬ ተንክቷል ልከበር ፣ ስሜ ጠፍቷል ይታደስ ፣ ገንዘቤ ተወስዷል ይመለስ ማለት የምትችለውም በዚያው ነው፡፡ አርእስቱን የተቀኘው ባለቅኔም በፍርድ ከሄደች ብዙ ዋጋ ከምታወጣው በቅሎው ይልቅ ያለፍርድ የሄደችው በሳንቲም የምትተመነው ጭብጦው የቆጨችው ያለፍርድ በዘፈቀደ የሚደረግ ድርጊት የፍትህ መዛባት የፍርድ መጓደል አድርጎ ስለሚመለከተው ነው፡፡


ታዲያ ይህን ሁሉ ማድረግ የሚችሉት ፍርድ ቤቶቻችን እነዚህን ጉዳዮች በጊዜው ፣ በእኩል እና ያለአድሎ ለመፈጸም በሚያስችላቸው ቁመና ላይ ይገኛሉ? በርግጥስ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚታመን ሲቀጣም ሲፈታም ልክ ነው የሚባል ፍርድ ቤት ገንብተናል? ፍትህ ለሁሉም በግዜው ተደራሽ ሆኗል?


ፀሃፊው ለጥያቄዎቹ የሚሰጠው ምላሽ ከፁሁፉ አርእስት ጋር አንድ እና ያው ነው፡፡ ይህ ፅሁፉ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ክብርት ፕሬዝዳንቷ ከመሾማቸው ቀደም ብሎ ለንባብ ለማብቃት ታስቦ በመሃል ክብርት ፕሬዝዳንቷ በመመረጣቸው የፅሁፉ ፋይዳ ከትችት ወደ ቸግር ተቋሚነት ከፍ ብሏል፡፡ የትላንቱ የፍርድ ቤት ዘመን አጥፍቶም ሆነ አልምቶ አልፏል፡፡ ለለውጥ የተሾሙት እና የሚሾሙት አዲስ ሀይሎች የትላንቱን ችግር መፍትሄ ማፈላለጊያ በማድረግ አዲስ ዘመን እንደሚያነጉ ይታመናል፡፡
ይህ ፅሁፍ መንግስት ለፍርድ ቤቶች ትኩረት ከመንፈጉ የተነሳ፣ በተበላሸ አስተዳደር ምክንያት ፣ ለሙግት ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ቤቶችን በማጨናነቃቸው ሳቢያ ፣ ለነሱም ትኩረት እና ምስጋና ሳይቸራቸው በሚቻላቸው መጠን በችግሮቹ መሀል ያላቸውን የሰጡ ለሀቅ እና ለፍትህ የቆሙ ዳኞችን አይመለከትም፡፡ ይልቁንስ በዚህ ችግር መሃል የቻሉትን አድርገዋል እና ምስጋናየ ይድረሰቻው፡፡ ይልቁንም ፅሁፉ ለችግሮቹ ዋና ምክንያት የሆኑትን የትኩረት ማጣት፣ የአስተዳደር ብልሽት እና ስሁት የሆኑ የፖሊሲ ጉዳዬች ላይ ያተኩራል፡፡


ዳኛ መሆን የሚገባው ማን ነው፡፡

Continue reading
  10388 Hits
Tags:

Legal Effects of Unregistered Property Interests on Third Parties: What is the Position of Ethiopian Law?

If you have an interest on a property and this interest is registered, it will have legal effects on third parties. The idea is the third party knew or should have known of a prior interest registered before the acquisition of his own interest. Government enhances certainty and security of land transactions by providing a registry system. The purpose of this registry system is to register anyone who has prescribed interests (such as mortgage) on a land so that third parties would have a chance to inspect the registry and decide whether to make another transaction. There is of course a practical question of as to whether the current registry system provides such service to inquirers. Leaving this aside, another question is what if the interest is not registered because the law does not require such interest to be registered in the first place or because of other reasons. Consider the following:

 

X owns a building part of which is rented to Y on the basis of a written but unregistered contract for a period of 15 years. Y has undertaken to pay the rent quarterly in advance. X developed a business idea and borrowed money from Easymoney Share Company by providing his building as collateral. The contract of mortgage is registered. Now that X defaulted in paying back the sum he borrowed, Easymoney plans to foreclose the building. The question is now as to whether Easymoney or any purchaser of the building will have the right to evict Y?

 

The above set of facts presents two competing interests. On the one hand, there is the property interest of the bank which did not know of the existence of this long-term contract of rent. On the other hand, you have the contractual interest of Y which has planned all his business on the understanding that he would have the right to the use of the building for the agreed period of time. It is true that this contract was not registered but it is also true that the law does not require such contracts to be registered. In a recent case, the Cassation Division of the Federal Supreme Court decided that Article 1723(1) does not include contracts of leases (Rental Houses Administration Agency v Sosina Asfaw [2005] File Number 15992). Article 1723(1) provides that "a contract creating or assigning rights in ownership or bare ownership on an immovable or an usufruct, servitude or mortgage of an immovable shall be in writing and registered with a court or notary". It should be noted that Article 1723 is concerned with the validity of the contract between the parties and not with its effect on third parties. Therefore, it can be argued that contracts of lease for whatever period of time could be made in any form and will still be valid. The question relates to the effect of contracts of lease on third parties. In this regard, Article 2899(1) provides that "leases for a period exceeding five years shall not affect third parties until they are entered in the registers of immovable property at the place where the immovable is situate". It follows therefore that even if oral or written but unregistered contracts of lease are binding on the parties, their effect on third parties depend on the period of time they are made and whether they are registered. If the lease is made for a period of time exceeding five years, it should be registered for it to have affect third parties. In the above example, the contract of lease is for a period of 15 years but not registered. In such cases, Article 2899(2) provides that the contract of lease affects third parties only for five years from the day when the the third party has registered his/her right on the immovable. It follows therefore that the contract of lease between X and Y affects Easymoney for a period of five years. If on the other hand, the period of time for which the contracts of lease is made is not certain and the contract of lease is not registered, Article 2933(1) and Article 2899(3) provide that this contract is deemed to have been made for indeterminate period of time. Assume in the above case the period of time for which the contract of lease is made is uncertain; in such cases, Easymoney can presume this contract to have been made for indeterminate period of time. The question is what will be the effect of that presumption? According to Article 2966, contracts of leases for an indeterminate periods of time can be terminated by giving default notice. To conclude, it can be said that contracts of lease is binding on the parties in whatever form and for however it is made. But is the effect on third parties depends on two factors:

Continue reading
  13223 Hits