Legal updates on federal court establishment proclamation, proclamation number 1234/2021

Introduction

The Federal Court Proclamation no 25/96 its amendment, which has been in force for many years, is repealed and replaced by the federal courts' Proclamation number 1234/2021.  When we look at the existing proclamation, the new law introduced new elements. In these short notes, we will briefly explore the new features of the proclamation and the reason behind the improvements of the proclamation to its current content.

Continue reading
  10283 Hits
Tags:

Brief summary major reforms introduced by Movable Property Security Rights Proclamation, No.1147/2019

 

Introduction

Before the enactment of movable property security right proclamation, Ethiopian movable security right law is ultimately unsatisfactory because it is fragmented, and contained in four different pieces of legislation: The Civil and Commercial Codes, the Business Mortgage Proclamation, the Proclamation to Provide for a Warehouse Receipts System (Warehouse Receipts Proclamation), and the Capital Goods Leasing Business Proclamation. Under this system, security rights in many movable assets are not registered.

Continue reading
  8101 Hits

Updates on the recent administrative procedure proclamation no 1183/2020

Before the enactments of the Federal Administrative Procedure Proclamation, there is a gap in the Ethiopian legal regime due to the absence of administrative procedure law. This is a neglected subject both by the legal academia and practitioners. It is very difficult and challenges to talk about the history of administrative law in Ethiopia. Administrative law is still not well developed, and it is an area of law characterized by the lack of legislative reform.

Continue reading
  7031 Hits

ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል

 

 

መግቢያ

የዚህ ጽሑፍ ዋና ዓላማ ያለደረሰኝ ግብይት የማከናወን ወንጀል ላይ መሠረታዊ የሆነ መረዳት እንዲኖር ማድረግ እና ያለደረሰኝ ግብይት ከማከናወን ወንጀል ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ያሉ አንዳንድ ማብራሪያዎች (commentaries) ላይ የሚስተዋሉትን ግድፈቶች ማቃናት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

ያለደሰኝ ግብይት ወንጀል የኢትዮጵያ የታክስ ሕግ ወንጀል አካል ሆኖ የተደነገገው በ2001 ዓ.ም ሲሆን ይህም በአዋጅ 609/2001 አንቀጽ 50 (ሐ) እና 50 (መ) 2 መሠረት ነው፡፡ ምንም እንኳ ጥቂት ለውጥ ቢደረግባቸውም እነዚህ አንቀፆች በታክስ አስተዳደር አዋጅ 983/2008 አንቀጽ 120/1 እና 131(1)(ለ) ላይ ከተደነገገውና ያለደረሰኝ ግብይትን የወንጀል ተግባር አድርጎ ከሚደነግጉት አንቀፆች ጋር የጎላ የይዘት ልዩነት የላቸውም፡፡

Continue reading
  8380 Hits

ፍላጎት ላጣው መራጭ ምን ይደረግ?

 

ለፌዴራል እና ለክልል ሕግ አውጪ ምክር ቤቶች የሕዝብ እንደራሴዎችን ለመምረጥ የሚከናወነው መጪው አገር አቀፍ ምርጫ ከተደጋጋሚ መስተጓጎሎች በኋላ የድምጽ መስጫ ዕለቱ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲደረግ ቀን ተቆርጦለት ዝግጅቶቹ ቀጥለዋል፡፡ ይህ ምርጫ ከዓመት በፊት ማለትም በሕገ-መንግሥታዊ ትርጉም ከመራዘሙ በፊት ካለው ጊዜ ጋር ሲነጻጸር፤ በትግራዩ ጦርነት፣ በሰላምና ደህንነት ስጋቶቹ፣ የተዳከመው የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ፣ የተጽዕኖ ፈጣሪ ፖለቲከኞች እስር፣ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት እና የውጪ አገራት ጫና ያደበዘዘው ይመስላል፡፡ እንዲህም ሆኖ ግን፤ ድህረ-2010 የታዩት የሕግ እና የተቋማት ማሻሻያዎች፣ አንጻራዊ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን እና የሲቪክ ምሕዳሮች ስፋት የዘንድሮውን ምርጫ በጉጉት ተጠባቂ እንዲሆን ማድረጋቸው አልቀረም፡፡

ምርጫ 2013 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳውን ይፋ ካደረገበት ወርኃ ጥር ጀምሮ እስካሁን ድረስ በርከት ያሉ የቅድመ-ምርጫ ተግባራት ተከናውነውበታል። ከእነዚህ መካከል የምርጫ ቁሳቁሶች ዝግጅት፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላ፣ የእጩዎች ምዝገባ፣ የመራጮች ትምህርት እና የመራጮች ምዝገባ ተጠቃሽ ክንውኖች ናቸው።

በእነዚህ ወሳኝ የቅድመ-ምርጫ ክንውኖች ውስጥ የተነሱት እና በቀሩት ጊዜያትም ሊነሱ የሚችሉት በተለይም የሕግ ጉዳዮች የዘንድሮውን ምርጫ የተለየ መሆንነት አጉልተው የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ለአብነት እንኳ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ያስከተለው ውዝግብ፣ ከፌዴራሉና ከሌሎቹ ክልሎች ምክር ቤት አባላት ምርጫ ቀን ተለይቶ የነበረው የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ምክር ቤቶች ምርጫ ጉዳይ፣ የአፋር እና የሶማሌ ክልሎች የምርጫ ጣቢያዎች ውዝግብ፣ የሐረሪ ክልል ብሔራዊ ጉባኤ አባላት ምርጫ እና አነጋጋሪው የእጩዎች ምዝገባ የፍርድ ቤቶች ክርክር የዘንድሮው ምርጫ በቀጣይ ለሚከናወኑ ምርጫዎች አስቀምጦ የሚያልፈው ልምምድ ቀላል የሚባል አለመሆኑን የሚያስገነዝቡ ናቸው፡፡

ወሳኝ የምርጫ ባለድርሻ አካላት ከሆኑት ልዩ ልዩ ተቋማት መካከል ምርጫ ቦርድ፣ ፍርድ ቤቶች እና የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች በእስካሁኖቹ የምርጫ ሂደቶች ያሳዩት  ጥረት የምንመኘውን ነጻ፣ ትክክለኛ እና ተዓማኒ ምርጫ ወደፊት ለማድረግ እጅግ ጠቃሚ ናቸው። በዚያው ልክ ግን በሒደቶቹ ውስጥ የታዩ የጎሎ ክፍተቶች የዘንድሮውን ጨምሮ በቀጣይ ለሚደረጉትም ምርጫዎች የራሳቸው አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደራቸው አይቀርም።

Continue reading
  4930 Hits
Tags:

በማሻሻያ አዋጅ 1160/2011 በጉምሩክ ወንጀሎች ላይ የተደረጉ ማሻሻያዎች

 

                                                                 

አዋጅ ቁጥር-1160/2011 የጉምሩክ አዋጅ 859/2006 ማሻሻያ አዋጅ ሲሆን በዚህ አዋጅ የጉምሩክ አዋጅ 859/2006 ውስጥ ባሉት አንዳንድ ድንጋጌዎች ላይ ማሻሻያ ተደርጓል፡፡ ከተደረጉ ማሻሻያዎች በዋናነት የሚጠቀሰው በአከራካሪ የወንጀል ድንጋጌዎች ላይ የተደረገው ማሻሻያ ሲሆን በዚህ ፅሁፍ በማሻሻያ አዋጁ የተሸሩ፣የተሸሻሉና እንደ አዲስ የተካተቱ የወንጀል ድንጋጌዎች አጠር ባለመልኩ ተዳሰዋል፡፡

 

1. የኮንትሮባንድ ወንጀል፡-

Continue reading
  9859 Hits

በመመሪያ ቁጥር 67/2013 በጨው ላይ የሰፈረውን ድንጋጌ ከኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2011 አንጻር የተደረገ አጭር ዳሰሳ

 

መግቢያ

አዲሱ የኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ ቁጥር 1186/2012 እየተሰራበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይህንን አዋጅ ለማስፈጸም የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር ስለኤክሳይዝ ታክስ አዋጅ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 67/2013 ጸድቆ ከጥቅምት 6 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በመመሪያው አንቀጽ 38 ላይ በጨው ላይ የሚከፈል የኤክሳይዝ ታክስን በተመለከተ የሰፈረውን ድንጋጌ ከአዋጁ አጠቃላይ ይዘትና መንፈስ አንጻር በጥቂቱ ለመዳሰስ ነው፡፡

 

1. በጨው ምርትና ግብይት ላይ ወሳኝ ባለድርሻ አካላት

Continue reading
  5668 Hits

የሕገ-መንግሥት ፍርድ ቤት፡ የብሔርና ብሔረሰቦች ሉዓላዊነት መቃብር

 

 

በሀገራችን ህዝባዊ አመጽን ተከትሎ በሰኔ 2010 ዓ.ም ብትረ መንግሥቱን የሚዘውረው የብልጽግና ፓርቲ ለአመጹ ምክንያት የሆኑትን የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ የተቋም ግንባታ እና የህግ ለውጦችን እያደረገ ነው፡፡

በተጨማሪም ገዢው የብልጽግና ፓርቲ ከኦሮሚያ እና አማራ ብሔር ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በቅርቡ በተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ሕገ-መንግሥቱን በጋራ እንዲሻሻል ለማድረግ የሚሰሩ ስለመሆኑ ተፈራርመዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲሚሻሻሉ በጋራ የተስማሙባቸው የሕገ-መንግሥት የአንቀጾች ዝርዝር ላይ ስምምነት ላይ አልደረሱም(ወይም ለህዝብ ሊገልጹት አልፈለጉም)፡፡ ነገር ግን በመግባቢያው ሰነድ ላይ ከፈረሙት አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከጥቂት የሕገ-መንግሥት ምሁራን እንዲሻሻል ጥያቄ የሚቀርብበት አንዱ ድንጋጌ የሕገ-መንግሥት አንቀጽ 62(1) የሆነውና “ሕገ-መንግሥትን የመተርጓም” እና በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ የመስጠት የፌዴሬሽን ምክር ቤት ስልጣንን ከምክር ቤቱ ተወስዶ የሕገ-መንግሥት ጉዳይን የሚያይና የሚወስን የሕገ-መንግሥት ፍ/ቤት እንዲቋቋም በማለት ባህር አቋርጠው የምዕራቡንና የምስራቁም ልምድ በማስረጃነት በመጥቀስ በሀገራችንም ይህ ተግባራዊ እንዲሆን እየሞገቱ ይገኛሉ፡፡

Continue reading
  5850 Hits

በፍትሐብሔር ክርክር ቅድመ-ሙግት ሂደት ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች

የዚህ ጽሑፍ ዋና ትኩረት  ከሙግት በፊት ያሉ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደቶች አንድን ክርክር ላይ ያላቸዉን  ሚና ማጉላት እና ፋይዳቸዉን ማሳየት ነዉ፡፡ በፍትሐ ብሔር ክርክር ሂደት ቅደመ ሙግት የሚባለዉ ለክርክሩ መሪ ጭብጥ ተይዞ ግራ ቀኙ ማስረጃ ማሰማት ከመጀመራቸዉ በፊት ያለዉ ሂደት ነዉ፡፡ በፍትሐ ብሔር ክርክር ዋናዉ ሙግት የሚጀምረዉ ጭብጥ ተይዞ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ 257 እና ተከታይ ድንጋጌዎቹ ተከራካሪዎች ማስረጃዎቻቸዉ የሚያስረዷቸዉን ጭብጥ እያስመዘገቡ ማስረጃ ማሰማት ሲጀምሩ ነዉ፡፡ ከዋናዉ ሙግት በፊት ባለዉ  የቅድመ ሙግት ሂደት በዋናነት ክስና ማስረጃ ማቅረብ፣ መጥሪያ ማድረስ፣ መልስ እና ማስረጃ መቅረብ፣ ክስ መሰማት እና የክስ መቃወሚያዉ ላይ የመወሰን ተግባሮች ይፈፀማሉ፡፡ ይህ የክርክር ሂደት ክርክሩን ለመምራት ዋና መሰረት የሆነዉ ነዉ፡፡ የክርክሩ አቅጣጫ የሚወሰነዉም በዚህ የክርክር ደረጃ ላይ  በሚሰሩ ስራዎች ነዉ፡፡ ክርክሩን ግልፅ እና አጭር በሆነ ሂደት ለመፈፀም የሚያስችለዉም የቅድመ ሙግት ሂደቱ ጤናማ መሆን ከቻለ ነዉ፡፡

Continue reading
  9492 Hits

አዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ 1234/2013 ምን አዲስ ነገር ይዟል - በወፍ በረር

የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ 1234/2013 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመ 15 ከፍተኛ የሕግ ባለሙያዎችን በአባልነት ያካተተ የዳኝነት ሥርዓት አማካሪ ጉባኤ ረቂቁ ተዘጋጅቶ በፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ በሕግ ባለሙያዎች እና በሕዝብ ተሳትፎ ዳብሮ ከሁለት አመታት ቆይታ በኋላ ጥር 13 ቀን/ 2013 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል።

Continue reading
  24328 Hits
Tags: