Exploring the Protection for Tibeb Patterns under Ethiopian Law: Are Tibeb Patterns Works of Applied Art or Traditional Cultural Expressions?

Abstract

Traditional dresses are highly dignified among Ethiopians. It is very common to beautify traditional dresses with handwoven embroidery designs, locally referred to as Tibeb. Ethiopians wear traditional dresses decorated with handwoven Tibeb patterns also at important occasions such as religious ceremonies, wedding programs, funerals, public festivals and other cultural events.

Continue reading
  3131 Hits

የኃይማኖት ነክ ሥራዎች የቅጂ መብቶች

-    ሃይማኖታዊ ይዘት ያላቸው ስራዎች የቅጂ መብት በአዋጁ እንዴት ይታያል?

-    ያለ ባለቤቱ ፍቃድ ማሳተም አለመከልከሉ የቅጂ መብትን ሌላ ሰው እንዲጠቀም መፍቀድ ማለት ነው፤

-    በመፅሔት፣ በጋዜጣ እና በመፅሐፍ የወጡ ስራዎች የሚኖራቸው የቅጂ መብት ጥበቃ ይለያያል?

-    በአለቃ አያሌው ታምሩ ወራሾችና በአንድ አሳታሚና ማተሚያ ቤት መሀከል እስከ ሰበር የደረሰው የቅጂ መብት ጥሰት ክርክር በምን ተቋጨ?

1. ሃይማኖታዊ ስራዎችና የቅጂ መብት

Continue reading
  11860 Hits

Software Patents: Justifications and Arguments

I. Introduction

As one part of the subject matter of Intellectual Property Law (hereinafter IP), patent is mostly referred as “hard IP” as opposed to “soft IP” which is used to refer copyright, trademark, trade secret and other form of protection. Patent law maintains the lion’s share in the discussion of the subject matter of IP.

Any jurisdiction that tries to govern the patent regime primarily defines the statutory subject matter and provides what should and should not be patented. Under the United States (US) patent system, Section of the Patent Act  provides “Whoever invents or discovers any new and useful process, machine, manufacture, or composition of matter, or any new and useful improvement thereof, may obtain a patent.” While this provision clearly instructs what to take before the United States Patent and Trademark Office (USPTO) claiming patent protection, the US Supreme Court in the Bensoncase  has provided categories which are not patent-able subject matter, these include; natural phenomenon, laws of nature, abstract ideas, and mathematical algorithms.

The main purpose of the law to confer the patentable and non-patentable subject matter is because, patent protection grants a monopoly right excluding the invention from the public domain. This paper mainly focuses on the issue of patentability of computer programs (software). The emergence of the idea of software patent in ’s and early ’s invites scientists and legal scholars to the discussion table and led to variety of arguments in favor and against of this concept.

In this paper, the writer primarily addresses the theoretical basis for software patent, and discusses the selected arguments in favor of and against the protection thereof. Then, briefly discuss the likely impact of excluding software patent on other fields of technology as well economic development at large.

Continue reading
  14103 Hits

Copyright Protection in Ethiopia Shining Law, Zero Effect

The idea of enacting a copyright law was first developed to encourage creativity and further grew on that sole purpose and protecting companies’ and individuals’ right to ownership.  Such protections of copyright is expressed by giving the author or the owner of copyrightable works the exclusive right of reproduction, sale, rent, transfer, and other communication of the work to the public.

According to David Bainbridge, a well-known writer on Intellectual Property, copyright means an intangible, incorporeal property right granted by the law to the owner of the specified types of literary and artistic works such as films and sound recordings. Furthermore, copyright protection subsists in original works of authorship fixed in any tangible medium of expression. In no case does copyright protection for an original work of authorship extend to any idea, procedure, process, and system, method of operation, concept, principle, or discovery.

One important feature of copyright law is that it does not protect ideas, rather protects the expression of an idea.

However, protecting the interest of the owner of the copyrightable work is not the only purpose of the copyright law. Copyright law has to also take in to account the interest of the society at large.

The protection given by the law to the owner of the copyright, in recognition of the time and effort taken to create the work, ensures a fair balance between the needs of the copyright user and the rights of the copyright owner. People need to be able to copy materials produced by others, but if there were no limits in place, the owners of the copyright material would not be remunerated for their work, and there would be no incentive to create further work.

Continue reading
  13118 Hits
Tags:

In Response to the comment given by a Fitsum Yifrashewa

ፍጹም ይፍራሸዋ ለሰጠኀኝ አስተያየት እና ለላክልኝ ጽሁፍ አመሰግናለሁ፡፡ በጽሁፋ ላይ ለማንሳት የወደድኩት የንግድ ምልክት በኢትዮጵያ ህጎች ደረጃ ቀለል ባለ ሁኔታ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያህል ነው፡፡ በሌላው ጸሃፊ የተጻፈውንና አንተም የላክልኝን በዚሁ ድረ-ገጽ ላይ ስለ ንግድ ምልክት የተጻፈውን ጽሁፍ ለማየት ሞክሬያለሁ፡፡ ጸሃፊው በንድግ ምልክቶች ላይ የጻፈው ጽሁፍ ጠቃሚና ስለንግድ ምልክቶች ለማወቅ የሚረዳ መሆኑን ለማስገንዘብም እወዳለሁ፡፡ ይህም በጽ/ቤቱ በስራ ባሳለፍኩባቸው ግዝያቶች አጠቃላይ ከሚታዩ ሁኔታዎች ይልቅ በአሰራርና ህጉን በተገቢው መንገድ በኢንተርናሽናል ደረጃና ከህጉ አላማ አንጻር መሬት ላይ ለማውረድ ችግር ወደፈጠሩት ሁኔታዎች ትኩረት ሰጥቸ እንድጽፍ አነሳስቶኛል፡፡ሆኖም ግን በጽሁፉ ላይ መስተካከል ይገባቸዋል የምላቸውን ነገሮች ከዚህ በታች እንደሚከተለው ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡

የንግድ ምልክት ማለት የአንድ ምርት ወይም አገልግሎት መይም ምንጭ(Origin) በማስመዝገብ እንደ ብቸኛ መለያ(Exclusive sign) ተወስዶ ሰዎች አንድን ምርት መይም አገልግሎት ከሌላው ምርት ለመለየት የሚያገለግል ምልክት ሆኖ ማሳከር(Confusion) የማስወገድ አላማ ያለው ነው፡፡ ተብሎ በጸሃፊው በተቀመጠው ላይ ከዚህ በታች ያሉት ማስተካከያዎች መግባት እንዳለባቸው አምናለሁ፡፡

በመጀመሪያ “የንግድ ምልክት ማለት የአንድ ምርት ወይም አገልግሎት መይም ምንጭ(Origin) በማስመዝገብ……” ተብሎ የተጠቀሰው በንግድ ምልክት ምዝገባና ጥበቃ አዋጅ 501/1998 አንቀጽ 6(ሸ) ላይ በተጠቀሰው መሰረት የአንድን ምርት ወይም አገልግሎት የመነጨበትን ቦታ በንግድ ምልክቱ የቀረበ እንደሆነ የንግድ ምልክቱ ለምዝገባ ብቁ እንደማይሆንና ይህም ሁኔታ በዚሁ አዋጅ በአንቀጽ 6(2) መሰረትም ስናየው በምንም አይነት መልኩ በአንቀጽ 6(ሸ) ላይ የተቀመጠው የህግ አግባብ exception እንደሌለውም በግልጽ ሲያሳይ ይታያል፡፡ የአንድን ምርት ወይም አገልግሎት የመነጨበትን ቦታ በምልክትነት ማስመዝገብ የሚቻለው በንግድ ምልክት ሳይሆን በወል የንግድ ምልክት እንደሆነና በሁለቱ መሃከልም ብዙ ልዩነት እንዳለ ማጤኑም ተገቢ ይሆናል ብየ አስባለሁ፡፡

በሁለተኛነት “እንደ ብቸኛ መለያ (Exclusive sign) ተወስዶ ሰዎች አንድን ምርት መይም አገልግሎት ከሌላው ምርት ለመለየት የሚያገለግል ምልክት ሆኖ…” የሚለው አገላለጽ ጠቦ መተርጎም ብቻ ሳይሆን መስተካከልም አለበት ብየ አምናለሁ፡፡ ይህንንም ለማለት የፈለኩት አንድ የንግድ ምልክት ከሌሎች ምርቶች ወይም አገልግሎቶች ሳይሆን ሌሎቹ ንግድ ምልክቶቹ ካልተመዘገቡ አንድ አይነት ወይም ተመሳሳይ ከሆኑ የንግድ ምልክቶች የተለየ እንዲሆን የሚጠበቅበት ሲሆን  በሌላ መንገድ ደግሞ ሌሎቹ የንግድ ምልቶች ከተመዘገቡ እንደሆነ ደግሞ  አንድ አይነት ወይም ተመሳሳይ ከሆኑ ምርቶቻቸው ወይም አገልግሎቶቻቸው በተጨማሪ በዕቃወቹ ወይም አገልግሎቶቹ መካከል ግንኙነት እንዳለ በማያሳይ መልኩ መቅረብ እነዳለበት እንጂ በአጠቃላይ ከሌላው ምርት ጋር መለየት አለበት ተብሎ መቀመጥ እንደሌለበት መታወቅ አለበት ፡፡

በሌላው የጸሃፊው የጽሁፍ አካል ውስጥ “የንግድ ምልክት ህጋዊነት የሚመሰረተው ወይም ጥበቃ የሚያገኘው በምዝገባ እንደሆነ በአዋጁ አንቀጽ 4፣5፣15 እና 16 መረዳት የሚቻል ሲሆን……” ተብሎ የተገለጸው ውስጥ ከዚህ በታች በተገለጸው መልክ መታረም አለበት እላለሁ፡፡

Continue reading
  8058 Hits

"ድፍረት" ፊልም - የቅጅ መብት ጥበቃ ለታሪካዊ እውነታ ወይስ ለአእምሮ ፈጠራ?

በአእምሯዊ ንብረት ማዕቀፍ ተካተው በህግ ጥበቃ ከሚደረግላቸው ኢ-ቁሳዊ የንብረት ባለቤትነት መብቶች መካከል የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንሰ ሃሳብ ውልደት የኃልዮሽ ተጉዞ በታሪክ ተጠቃሽ ወደ ሆነውና  ከታላቋ ብሪታንያ ተነስቶ ወደ ሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ ወደ ተስፋፋው የኢንዲስትሪ አብዮት ይወስደናል፡፡ የዚህ ዘመን ካፈራቸው እውቅ ሳይንቲስቶች መካከል አንዱ በሆነው ጆን ጉተንበርግ የተፈጠረው የህትመት ማሽን ለቅጅ መብት ጥያቄ መጠንሰስ ምክንያት በመሆን የኋላ የኋላም በወቅቱ የብሪታንያ ንግስት በነበሩት ንግስት አን ስም ለተሰየመው የአን ስታቲዩት (Anne Statute) ተብሎ ለሚታወቀው የህግ ማዕቀፍ እ.ኤ.አ በ1710 ዓ.ም መደንገግ ምክንያት ሆኗል፡፡ የህትመት ማሽኑ መፈጠር በወቅቱ በነበሩ ደራስያን የሚጻፉ መጽሃፍት በፍጥነት እየተባዙ ወደ አንባቢዎች እጅ እንዲደርሱ በማድረግ ከአሳታሚዎች ፍቃድ ውጪ የሚታተሙ መጽሃፍት እየበዙ እንዲመጡ አስገድዷል፡፡ ይህም በአሳታሚዎች ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያደረሰ በመምጣቱ በወቅቱ በተሰሚነት እና በገንዘብ አቅም ገናና የነበሩት አሳታሚዎች መንግስት ለመብታቸው መከበር ህጋዊ ሽፋን ይሰጣቸው ዘንድ መወትወታቸውን ተከትሎ ነበር የአን ስታቲዩት (Anne Statute) በሀገረ እንግሊዝ ሊታወጅ የቻለው፡፡

በዚህ መልኩ ወጥ የሆነ የህግ ማዕቀፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ወጥቶለት በሀገረ እንግሊዝ የተጀመረው የቅጅ መብት ጥበቃ በጎረቤት የአውሮፓ ሀገራት እየተስፋፋ የመጣውን የመጻሃፍት ህትመት እና ስርጭት ተከትሎ ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ የህግ ከለላዎችን መሻቱ አልቀረም፡፡ በዚህም ሳቢያ ዓለም ዓቀፍ የቅጅ መብት ስምምነቶች አስፈላጊነት አሳማኝ እየሆነ በመምጣቱ ሀገራት በዜጎቻቸው የሚሰሩ የፈጠራ ስራዎች በሌሎች ሀገራት ውስጥ የህግ ከለላ እንዲያገኙ የሚያስችሉ ስምምነቶችን በመፈራረም በድንበር ተወስኖ የነበረው የህግ ከለላ ዓለም ዓቀፋዊ ይዘት እንዲይዝ አድርገዋል፡፡ በዘርፉ ከተደረጉ ስምምነቶች መካከልም የበርን ስነጽሁፍ እና ኪነ ጥበብ ስራዎች ጥበቃ ዓለም ዓቀፍ ስምምነት እና ዩኒቨርሳል የቅጅ መብት ኮንቬንሽን በቀደምትነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከፍ ሲል በጥቅሉ በተገለጸው መልኩ እየተስፋፋ የመጣው የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንስ ሃሳብ እየጎለበተ እና እየዳበረ መጥቶ በኪነ-ጥበብ እና በስነ-ጥበብ ዘርፍ ከስራ አመንጪዎች ጋር ተጓዳኝ ተሳትፎ ላላቸው እንደ ከዋኝ፣ የድምጽ ሪከርዲንግ ፕሮዲውሰሮች እና የብሮድካስት ተቋማት የተዛማጅ መብቶች ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ የዛሬውን የተሟላ የህግ ጥበቃ ስርዓት መልክ ለመያዝ በቅቷል፡፡

ሀገራችንም በ1957ቱ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ እና በ1960 ዓ.ም በደነገገችው የፍትሐብሔር ህግ የቅጅ መብት ጥበቃን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በማካተት የፈጠራ ስራ አመንጪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የህግ ከለላ እንዲኖራቸው ማድረግ ችላለች፡፡ ሆኖም የእነዚህ ህጎች ወሰንም ሆነ አተገባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ በአይነት እና በይዘት እየጨመረ የመጣውን የፈጠራ ስራዎች ግብይት ሊመጥኑ የሚችሉ ባለመሆናቸው በ1996 ዓ.ም የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ ቁ. 410/96 ን በመደንገግ ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች፡፡

የዚህ ጽሁፍ ዋነኛ ዳሰሳ የቅጅ መብት ጥበቃ ለታሪካዊ እውነታ ወይስ ለአእምሮ ፈጠራ? የሚለውን ርዕሰ ጉዳይ በአሁን ወቅት በስራ ላይ በሚገኘው የሀገራችን የህግ ማዕቀፍም ሆነ በዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች ተቀባይነት ባገኙ ዓለም ዐቀፋዊ መርሆች እይታ መቃኘት ነውና የቅጅን መብት ጥበቃ አጀማመር ታሪካዊ ዳራ በዚህ መልኩ ከጠቆምኩ ወደዚሁ አንኳር ነጥብ ላምራ፡፡ መግቢያዬ ላይ እንደጠቆምኩት የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንሰ ሃሳብ የጀመረው ለአእምሮ ፈጠራ ውጤት ለሆኑ የስነ ጽሁፍ ስራዎች ጥበቃ በመስጠት ነው፡፡ ለእነዚህ የፈጠራ ስራዎች ጥበቃ ለማድረግ የተደነገጉ የህግ ማዕቀፎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ መጥተው ሌሎች በኪነ ጥበብ፣ በስነ ጥበብ እና በሳይንሳዊ መስክ የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች የጥበቃው አካል እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡ በሀገራችን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ አንቀጽ 2(30) ስር እንደተደነገገው በአዋጁ ጥበቃ የሚያገኙ ስራዎች እንደ መጽሃፍ፣ ቡክሌት፣ መጣጥፍ፣ ንግግር፣ ሌክቸር፣ ለአንድ ለተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል የሚደረግ መልዕክት አዘል ንግግር፣ የሃይማኖት ስብከት እና በይዘት ደረጃ ሌላ በቃል የቀረበ ስራ፣ ድራማ፣ ድራማዊ የሙዚቃ ስራ፣ በእንቅስቃሴ ብቻ የሚቀርብ ድራማ /ፓንቶምይምስ/፣ የመድረክ ውዝዋዜ፣ የሙዚቃ ስራ፣ ኦድዮቪዥዋል ስራ፣ የፎቶግራፍ ስራ፣ የስዕል ስራ፣ ካርታ፣ ፕላን፣ ስዕላዊ መግለጫ፣ የንድፍ ስራ እንዲሁም የጥልፍና የፊደል ቅርጽ ስራዎች፣ ኪነ - ህንጻ፣ የሀውልት፣ የቅርጻ ቅርጽ እና የኮምፒውተር ፕሮግራሞችን እና የመሳሰሉትን ያካትታል፡፡ ከዚህ የህግ ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የምንችለው የቅጅ መብት ባለቤት ለመሆን በመጀመሪያ ደረጃ ከላይ ከተዘረዘሩ ወይም መሰል ስራዎች መካከል የአንዱ ባለቤት መሆን የግድ ይሆናል፡፡ በቅጅ መብት ጥበቃ ዘርፍ የመጀመሪያ ሰፊ ተቀባይነት ባገኘው የበርን የስነ ጽሁፍ እና የኪነጥበብ ስራዎች ጥበቃ ዓለም ዓቀፍ ስምምነት አንቀጽ 2 ላይም በግልጽ እንደተመላከተው የስምምነቱ አባል ሀገራት የቅጅ መብት ጥበቃ እንዲሰጡ የሚገደዱት ከላይ በተዘረዘሩት የስራ ዘርፎች አስቀድሞ የተሰራ ስራ ሲኖር ብቻ ነው፡፡

Continue reading
  9392 Hits
Tags:

የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥብቃ በኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ

 

መግቢያ

የሥነ ጽሑፍ፣ የኪነ ጥበብ፣ ሳይንሳዊ ፈጠራዎች እና ተመሳሳይ የፈጠራ ሥራዎች የአንድ ሀገር ባህላዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ ልማትን በማፍጠን ረገድ ትልቅ ሚና የሚጫወቱ መሣሪያዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም የዚህ ሥራ ፈጣሪዎች የሚበረታቱበትንና አዳዲስ ፈጠራዎችን የሚያበረክቱበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር እጅጉን አስፈላጊ ነው፡፡

የሥነ ጽሑፍ፣ የኪነ ጥበብ ሳይንሳዊ ፈጠራዎች እና ተመሳሳይ የፈጠራ ሥራዎችን ውጤታማ ለማድረግ በሚከናወኑ ሥራዎች ላይ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች በሕግ እውቅና መስጠትና ጥበቃ ማድረግ አዳዲስ ፈጠራዎች እንዲበራታቱ እና የሚጠበቅባቸውን በህላዊ፣ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ እድገት በኅብረተሰቡ ውስጥ እንዲያመጡ እንዲሁም የፈጠራው ባለቤቶች ከሥራቸው እንዲጠቀሙ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡

የኢ... ሕገ መንግሥት አንቀጽ 91(3) ላይ መንግሥት አቅም በፈቀደ መጠን ኪነ ጥበብን፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂን የማስፋፋት ግዴታ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ በዚሁ መሠረት  መንግሥትም የቅጅና ተዛማጅ መብቶችን ለማክበርና ለማስከበር ይረዳው ዘንድ አዋጅ ቁጥር 410/1996 በማውጣት ሥራ ላይ አውሎ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ሁል ጊዜ እያደጉ እና እየተለዋወጡ የሚሄዱ በመሆናቸው በአዋጅ ቁጥር 410/1996 ላይ የተወሰነ ማሻሻያና ጭማሪ በማስፈለጉ ይህ አዋጅ በአዋጅ ቁጥር 872/2007 ማሻሻያ አድርጎ በሥራ ላይ አውሏል፡፡ ይህም መሆኑ ከአለም እና ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር ለመራመድ ያስችላል፡፡

Continue reading
  15231 Hits
Tags:

ሕግ መንግሥቱን በፖለሲ ማዕቀፍ ሥር?

ሰሞኑን በአንድ ካፌ ገብቼ የተደረደሩ ቀን ያለፈባቸው ጋዜጦች ስመለከት የሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 1/2009 የእለተ-እሁድ እትሙ ላይ “ሰበር ሰሚ ችሎት  በክራውን ሆቴል የንግድ ምልክት ላይ የሰጠው የመጨረሻ ውሳኔ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል ተባለ” በሚል ርእስ ባወጣው ዘገባ ላይ ዐይኔ አረፈ። ከዚህ በፊት በርካታ ጉዳዮች ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለመቅረባቸው አውቃለሁ። በሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ላይ የሕገ መንግሥት ጉዳይ ክርክር ተነስቶበት ወደ ጉባኤው ስለመቅረቡ ሳነብ ግን የመጀመሪያዬ ነው።  ምናልባት እኔ ያላወቅኳዋቸው ተመሳሳይ ጉዳዮች ከዚህ በፊት ቀርበው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ ርእሰ ጉዳዩ ቀልቤን ስለሳበው ባለጉዳዮቹ  ስለተከራከሩበት ጉዳይና የችሎቱ ውሰኔ  ለማወቅ ጉጉት አደረብኝ። እናም  ወደ ሕገ መንግሥት አጣሪ ጉባኤ ስለተወሰደው የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔና ስለክርክሩ ከሥሩ ለማየት ወሰንኩ። ስለሆነም የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ቅጂ ፈልጌ በመመልከት የሚከተለውን  የግል እስተያየቴን ለመጻፍ ውደድኩኝ።

ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ያስፈልገዋል የተባለው ውሳኔ ምንነት

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሰኔ የሰጠበት ጉዳይ በክራውን ሆቴል  ባለቤት (አመልካች) እና ሲክስ ኮንትኔታል ሆቴልስ (ተጠሪ) ከ2006 ዓ.ም ጀመሮ ከአእምሮ ንብረት ጽሕፈት እሰከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብሎም ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበ  ክርክር ነው። ይህ የመዝገብ ቁጥሩ 117013 የሆነውና ሰበር ሰሚ ችሎቱ በሰኔ 22 ቀን 2008 በዋለውና አምስት ዳኞች በተሰየሙበት ችሎት የተወሰነው ውሳኔ ከንግድ ምልክት ጥበቃ ጋር የተያየዘ ክርክር ነው። ወደ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበው ጉዳይ ከንግድ ምልክት ምዝገባ  ተቃውሞ ጋር በተያየዘ የክራውን ሆቴል ባለቤት በአእምሮ ጽሕፈት ቤት ውሰኔ ቅር ተሰኝተው ለከፈተኛ ፍርድ ቤት ይገባኝ ያሉበት ጉዳይ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእእምሮ ጽሕፈት ቤት ውሳኔውን ስለኣጸና የፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ስለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ሲሆን፤ ሰበር ሰሚ ችሎቱም ጉዳዩን ከስር መሰረቱ በመፈተሽ መሠረታዊ የሕግ ስህተት አለበት ብሎ ለአመልካች ወስኗል። 

ጉዳዩ ከመሰረቱ ሲታይ በወርሃ ነሃሴ 2005 “CROWNE PLAZA” በሚል በተጠሪ በኩል  በቀረበው የንግድ ምልክት ምዝገባ ጥያቄ ላይ ተቃውሞ ካለ በቀረበው የጋዜጣ ጥሪ መሠረት አመልካች (CROWN HOTEL) በቃልና በጽሁፍ በተደጋጋሚ ተቃውሞ ያቀርባሉ። ለተቃውሞ ምክንያት የሆነው በሕግ ጠበቃ ያገኘውን የንግድ ምልክት የቀዳሚነት መብቴን ይጥሳል የሚል ነው። ተቃውሞው የተመሠረተው በአዋጅ 501/ 2005 አንቀጽ 6 እና  አንቀጽ 7 መሠረት ሲሆን በተለይም በአንቀጽ 7(1) “ከአንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይ እቃዎች ወይም አግልግሎቶች  ጋር የተያያዘ  የሌላ ሰው ቀዳሚ የንግድ ምልክት ጋር አንድ ዓይነት ወይም መሳከርን ሊያስከትል ተመሳሳይነት ያለው”  ሲሆን ለምዝጋባ በቁ አይደለም ብሎ በሚደነግገው መሠረት እንዲሁም በተጨማሪም በንግድ ምዝጋባ አዋጅ 686/2002 አንቀጽ 24 (3) (ሀ) መሠረት የንግድ መዝጋቢው አካል “ቀደም ሲል ከተመዘገቡት የንግድ ስሞች ጋር አንድ ዓይነት ወይም ተመሳሳይና አሳሳች አለመሆን  24 (3) (በ) መሠረት ደግሞ በንግድ ስም መዝገብ  በተመዘገበ የንግድ ስም ላይ ላይ ከፊቱ ወይም ከኋላው ቃላት በመጨመር ያልቀረበ መሆኑን በማረጋገጥ እንዲመዘገብ በሚደነግገው መሠረት ቀደም ሲል ተመዝግቦ ሥራ ላይ ካለው CROWN HOTEL+ logo ጋር ይመሳሰል። በዚህም በሕግ ጥበቃ ያገኘው መልካም ስሜና ዝናዬ ይነካል የሚል ነበር። እውነት ነው የእእመሮ ንብረት ጽሕፈት ቤት ትኩረት የንግድ ምልክቱ ወይም የፈጠራው ጉዳይ ላይ ሲሆን የንግድ መዝጋቢው አካል ደግሞ በንግድ ስሙ ላይ ያተኩራል። ቀዳሚነት ያለው የንግድ ምልክት “CROWN HOTEL” የሚል ሲሆን፤ አዲሱ የንግድ ምልክት “CROWNE PLAZA” የሚል ነው። የተጨመሩት ነገሮች በ CROWN ላይ” E”  እንዲሁም “PLAZA”  የሚለው ቃል ነው።  ሁሉቱም የሆቴል አግልግሎት ሰጪዎች መሆናቸው ልብ ይሏል። በክርከር ሂደቱ በርካታ ጭብጦት ለክርክር ቀርበው የነበረ ሲሆን የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በክርክር ሂደቱ በጭብጥነት ተይዞ እስከ መጨረሻ በዘለቀው  ጭብጥ ላይ ብቻ  የሚያተኵር ይሆናል። 

በፍርድ ሃተታው እንደተመለከተው በአመልካች በኩል ለተቃውሞ መነሻ የሆኑት የሕግ መሰረቶች  የንግድ ምዝገባ አዋጅ እና የንግድ ምልክት ምዝጋባ አዎጅ ሲሆኑ  ጽሕፈት ቤቱ በመጀመሪያ  ተቃውሞውን  ከአዋጅ 501/ 1998 ጋር በማገናዘብ ተቀበሎ የምዝገባ ሂደቱን አቋረጦ የነበረ ቢሆንም ለሁለተኛ ጊዜ ውሳኔውን ሊቀለበሰው ችሏል። ውሳኔው ለአመልካች ከተነገረ በኋላ እንደገና ውሰኔውን በመቀየር የሚከተሉት ምክንያቶችን አቅርቧል። ጽሕፈት ቤቱ የንግድ ምልክቶቹ መመሳሰል ሳይክድ ኢንቨስትመነትን ለማበረታት ይጠቅማል በሚል ሁለቱም የንግድ ምልክቶች እንዲቀጥሉ ወስኗል። አክሎም ጽሕፈት ቤቱ ውሳኔው እንዳይደገም ራሱን አስጠንቅቆ ዘግቶታል። ይህም ውሰኔው ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት ካለው ፍላጎት ውጭ ተገቢ እንዳለሆን ያመነበት ይመስላል። ምክንያቱ ይህንን ውሳኔ ከሰጠ በኋላ ተመሳሰይ ውሳኔ እንዳይደገም በራሱ ላይ እግድ አስቀምጧል። እዚህ ላይ ሊነሳ የሚቸለው ጥያቄ ውሳኔው ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እስከ ሆነ ድርስ የማይደገመበት ምክንያት ምንድ ነው? ከአዲሱ ድርጅት የተሻለ ኢንቨስትመነት ይዘው በተመሳሳይ  የንግድ ምልክት ለሚቀርቡ ባለሃብቶችስ ምን ዓይነት ምላሽ ሊስጥ ነው? ዜጎችን በእኩልና ፍታሃዊ መንገድ ሊያገልግል የቋቋመ ተቋም ልክ እንዳልሆነ አምኖ እንዳይደገም የሚለውን ውሳኔ እንዴት ሊወስን ይችላል? CRROWN HOTELS and Convention Center የሚል የንግድ ምልክት ይዞ ከቀደሙት ሁለቱ ሆቴሎች ይልቅ የተሻለ አቅም ያለው ባለሀብት ለምዝገባ ቢያመለክትስ? ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል።

Continue reading
  12845 Hits

Ethiopia’s Accession to World Trade Organization (WTO): The Need to Reform Ethiopian Patent Law to Facilitate Access to Medicine

 

Abstract

As a country dealing with a pending WTO accession procedures, Ethiopia is required / expected to go through different legal reforms in order to have WTO-compliant domestic laws. Inter alia, the country specifically needs to review its intellectual property laws to provide a protection for intellectual properties as envisaged under the rule of WTO. However, adopting WTO-compliant rules to protect intellectual property, especially patent, exhibits a cross-road of patent protection and access to patented invention such as pharmaceuticals. It is logical to think that strong patent protection highly challenges an eased public access to the patented invention since the very nature of patent provides a stronger exclusive right to the right holder. To systematically deal with the issue of balancing patent protection to right holders and access to medicine to the public, different countries successfully reformed their laws to facilitate access to medicine while still adhering to WTO’s rules on patent. Thus, scrutinizing areas of reforms under Ethiopian patent law, in order to facilitate access to medicine before joining WTO, would help the country to adopt WTO-compliant rules which exhaustively addresses / exploits all exceptions, flexibilities and legal loopholes available to facilitate access to medicine.

 

Part One - Introductory Remarks

Before rushing into examining or establishing the details of Ethiopian patent law with regard to its role on facilitating access to pharmaceuticals, it would be helpful to shortly point out the relationship between patent and access to patented innovations in general. Lately, literatures seem to show / define that intellectual properties, especially patentable innovations, and public demand to access patented inventions, as two competing interest (“Monopoly” and “Access”) which hinges on a balance.

Continue reading
  11476 Hits