ተገዶ የመያዝን ሕጋዊነት ለማጣራት የሚቀርብ ክስ (Habeas corpus) እና የፍትሐብሔር እንድምታው

የአካል ነጻነት መብት በኢፌዲሪ ህገ መንግስት እውቅና ከተሰጣቸው የሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ እና ዋነኛው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይኸውም የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 17 ድንጋጌ በግልጽ ማንም ሰው በህግ ከተደነገገው ስርአት ውጪ ሊያዝ እንዲሁም ክስ ሳይቀርብበት እና ሳይፈረድበት ሊታሰር የማይችል ስለመሆኑ ያስቀምጣል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት በዚሁ ሕገ መንግስት መሰረት የሀገሪቱ የህግ አካል የሆኑ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ስምምነነት ሰነዶችም ቢሆን እውቅና ከተሰጧቸው የሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ ስለመሆኑ እሙን ነው፡፡ 

ይሁን እና የዚህ አጭር ጽሁፍ ዋነኛ አላማ የዚህን መብት መሰረታዊ  ነጥቦችን ወይም ወሰኑን ለማብራራት ሳይሆን አንድ የአካል ነጻነት መብቴ ተገፏል የሚል ሰው ይህ መብቱን ፍ/ቤት እንዲያስከብርለት አቤቱታ ቢያቀርብ ክርክሩ ከመደበኛው የፍታብሄር ጉዳዮች ክርክር የሚለይበትን ዋና ዋና የሥነ-ሥርዓት  ነጥቦች ለማብራራት ነው፡፡

Continue reading
  3932 Hits