በኢትዮጵያ ሕግ የግል የኮንስትራክሽን ውሎች ምንነት፣ የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮችና የመፍትሔ ሀሳቦች

 

“And they said, Go to, let us build us a city and a tower, whose top may reach unto heaven; let us make as a name, lest we be scattered abroad upon the face of the whole earth…Therefore is the name of is called Babel; because the Lord did there confound the language of all earth…” Genesis 11:4-9

መግቢያ

የኮንስትራክሽን ውል በጣም ውስብስብና ብዙ ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ ውል ነው፡፡ በይዘትም ሆነ በጥልቀት በጣም ሠፊ ከመሆኑ የተነሳ ውቂያኖስ መሰል ውል ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ለምን ቢባል በተለያየ ዕውቀትና ሙያ ዘርፍ የሚሳተፋ ሰወች ከመኖራቸው አልፎ በየደረጃው ዘርፈ ብዙ ግንኙነቶች መኖራቸው፤ የተለያዩ ጊዜ ወሰድ የዲዛይን ለውጦችና ማሻሻያወች ስለሚስተዋሉበት ጭምር  ነው፡፡

ኮንስትራክሽን የሰው ልጅ ወደ ምድር ከመጣ ጊዜ ጀምሮ የነበረ፤ ያለና የሚኖር እንቅስቃሴ ነው፡፡ የመጀመሪያው ግንባታ የሚባለውም በጥንታዊ ጋርዮሽ ሥርዓተ ማኅበር የሰው ልጅ ለመጠለያነት የተጠቀማቸው መጠለያ ጎጆወች ናቸው፡፡ በዓለም ታሪክም አንኳር የሚባሉ ግንባታወች ወስጥ ዋና የሚባሉት በጽሑፋ መግቢያ ላይ የተጠቆመው የባቢሎን ግንብ፤ ግብፅ (ምስር) ውስጥ በፈርዖኖች 2700-2500 . የተሰሩ ፒራሚዶች፤ በንጉስ ሽን ሁኣንግ ትዕዛዝ በጄኔራል ሜይንግ ቲን 220 . ገደማ የተሰራው ታላቁ የቻይና ግንብ እና የሮማዊያን የውሃ ማቆሪያ ግንባታወች ተጠቃሽ ናቸው፡፡

Continue reading
  22432 Hits

በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት ለሚስተዋሉ ጉዳቶች (Risks) ተጠያቂ ማን ነው?

“All courses of action are risky, so prudence is not in avoiding danger (it’s impossible), but calculating risk and acting decisively. Make mistakes of ambition and not mistakes of sloth. Develop the strength to do bold things, not the strength to suffer.” 

Niccolo Machiavelli, The Prince

መግቢያ

እንደሚታወቀው ግጭትና አደጋ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ዋና መገለጫወች እስኪመስሉ ድረስ በተደጋጋሚ የሚከሰቱ ነገሮች ናቸው፡፡  (ብሪያን ሻፒሮ፡1) የኮንስትራክሽን ውል በጣም ውስብስብና ብዙ ባለድርሻ አካላትን የሚያሳትፍ ውል ነው፡፡ በይዘትም ሆነ በጥልቀት በጣም ሠፊ ከመሆኑ የተነሳ ውቂያኖስ መሰል ውል ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ለምን ቢባል በተለያየ ዕውቀትና ሙያ ዘርፍ የሚሳተፋ ሰወች ከመኖራቸው አልፎ በየደረጃው ዘርፈ-ብዙ ግንኙነቶች መኖራቸው፤  የተለያዩ ጊዜ ወሰድ የዲዛይን ለውጦችና ማሻሻያወች ስለሚስተዋሉበት ነው፡፡  (ዮሐንስ እንየው፡2008፡1)

ታዲያ! ይህ ውል በሚፈጸምበት ወቅት የተለያዩ ግጭቶችና አለመግባባቶች መነሳታቸው የማይቀር ነው፡፡ ለነዚህ ግጭቶች ደግሞ መነሳት የአንበሳውን ድርሻ (lion’s share) የሚወስደው ጉዳቶችን እና አደጋን ማን ይሸከም (shouldering risks) እንዲሁም ማን ይውሰድ የሚለው ጉዳይ ነው፡፡

Continue reading
  14088 Hits
Tags:

የኮንስትራክሽን መብቶች (Claims) ምንነት እና የሚስተዋሉ ችግሮች

 

እንደ መነሻ

ማንኛውም ሰው በማህበራዊ ኑሮ ውስጥ በሚገጥመው መስተጋብር የተለያዩ ጥያቄዎች ወይም መብቶች (Claims) ሊኖረው ይችላል፡፡ ከዚህ ንድፈ ሃሳብ በመነሳት ታዲያ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውም በርካታ የመብት ጥያቄዎች መነሳታቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው! እንደሚታወቀው የግንባታ ዘርፍ ብዙ ባለድርሻ አካላትን ማሳተፋ ብቻ ሳይሆን የሚገርመው በተለያየ ሙያ ያሉ ሰዎች መሳተፋቸውም ጭምር ነው፡፡ ይህም በመሆኑም በርካታ የመብት ጥያቄዎች መነሳታቸው የግድ ነው፡፡ ከዚህ ብሂል በመነሳት አንዳንዶች ከውል በመነጨ ጉዳይ የውል የመብት ጥያቄ ሲያነሱ ሌሎች ደግሞ ሕጉ አስቀድሞ ባስቀመጠው ቅድመ ሁኔታ መሠረት ውል ሳይኖር አላፊነት በመኖሩ ምክንያት መብታቸውን ከውል ውጭ ሲጠይቁ ይስታዋላል፡፡

ምናልባት በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ውስጥ ለሚነሱ አለመግባባቶች እና ቁርሾዎች እንደ ምክንያትነት የሚነሣው የመብቶች ጥያቄ ጉዳይ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ቅድሚያውንም የሚወስዱት በተለይም ከሥራ ርክክብ መዘግይት እንዲሁም ከውል መለወጥ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በሃገራችንም ምንም እንኳን ልማዱ በዓለም አቀፍ ሥራ ተቋራጮች በርከት ቢልም ቅሉ፤ የሃገር ውስጥ ሥራ ተቋራጮችም ቢሆን አሁን አሁን የተለያዩ የኮንስትራክሽን የመብት ጥያቄዎች ሲያስተጋቡ ይስተዋላል፡፡

Continue reading
  17174 Hits

በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት የመሀንዲሱ ሚና እና የጥቅም ግጭት

መግቢያ

እንደሚታወቀው በኮንስትራክሽን ውሎች አፈጻጸም ወቅት መሀንዲሱ የሚጫወተው ሚና እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ አንዳንዴም መሀንዲሱ በውኑ የመሀንዲስ አድራጎት የማይመስሉ ተግባራትን ሲያከናውን ይሰተዋላል፡፡ ይህም ነገሩ አጀብ! ቢያሰኝም እውነታው ግን ከዚህ የራቀ አይደለም፡፡

እርግጥ ነው መሀንዲሱ ብዙ አልፎ አልፎም እርስ በእርሳቸው የሚጣረሱ ተግባራትን የሚያከናውንበት ጊዜ አለ፡፡ ለአብነት ያህልም፡-የግንባታው ዲዛይነር፣ የአሰሪው ወኪል (employer’s agent)፣ አማካሪ (supervisor)፣ የሥራ ርክክብ አረጋጋጭ (certifier)፣ ብሎም አንዳንዴ አራጊ ፈጣሪ ገላጋይ ዳኛ ወይም ከፊል አስታራቂ (adjudicator or quasi-arbitrator) ሊሆን ይችላል፡፡

በነገራችን ላይ የመሀንዲሱ ሚና ከላይ በጠቀስናቸው ተግባራት ላይ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ በግንባታ ውሉ አፈጻጸም ወቅት አስቀድሞ ለፕሮጀክቱ አፈጻጸም የሚሆኑ ሥራዎን በራሱ አነሻሽነት (proactive works) ወይም ፕሮጀክቱ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ ለውሉ አፈጻጸም የሚሆኑ ተግባራት እና ሥራዎችን በአሰሪው ወይም ሥራ ተቋራጩ ትእዛዝ (reactive works) እንዲሁም በውሉ በግልጽ ተለይተው ባይሰጡትም ለፕሮጀክት አፈጻጸም አንድ መደበኛ መሀንዲስ ሊሰራቸው የሚችሉ ሥራወችን ሊያከናውን ይችላል፡፡

አንዳንዴም ባለሃብቶች የመገንባት ሃሳቡ ኑሯቸው ወደ ስራው ሊገቡ ሲሉ ዘርፈ ብዙ የቴክኒክ ችግሮች፣ የምርታማነት እና ንግድ ጉዳዮች እንዲሁም የሕግ መወሳሰብ ባለማወቃቸው ብሎም ከግምት ባለማስገባታቸው የተነሳ እክል ሊገጥማቸው ይችላል፡፡ በሲቪል ምህንድስናው ዘርፍም ይህንን የባለሃብቱን ሃሳብ እና ስጋት ወደ እውነት ለመተግበር አማካሪ መሀንዲሱ ወይም መሀንዲሱየተባለውን ጉዳይ ሊፈጽምለት ይችላል፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው! መሀንዲሱም ሆነ አማካሪ መሀንዲሱ በውል የተጣለባቸውን ሥራወች ሲሰሩ ግልጽ የሆነ የጥቅም ግጭት (manifest conflict of interest) ሊከሰት ይችላል፡፡ እነዚህ የጥቅም ግጭቶችም በሥራው ላይ ከተፈጥሮ ሕግ እና ርትዕ(natural law and equity) አንጻር የፍትሃዊነት ጥያቄ ስለሚያስነሳ በጥልቀት እና በአንክሮ መታየት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

Continue reading
  17197 Hits

አስገዳጁ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ የሕንጻ መደርመስን ይከላከለው ይሆን?

መግቢያ

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ጉዳይ ልክ የዛሬ አመት ገደማ በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ስሙ ሰሚት በሚባል ስፍራ የተደረመሰውን ህንጻ እና እሱን ተከትሎ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደብዳቤ (circular) መሰረት አስገዳጅ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ በድጋሜ እንዲኖር መደረጉን በማስመልከት ነው፡፡

እንደሚታወቀው ኢንሹራንስ (መድን) የሚለው ቃል ሲነሳ ምንግዜም ቢሆን ሊዘነጋ የማይችለውጉዳይ የአደጋ (risk) መኖር ነው፡፡ የአደጋ መከሰት ለመድን ቅድመ ሁኔታ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

ስለ መድን ታሪክ በአጭሩ ለመናገር ስነሳ አባይን በጭልፋ ኢንዲሉ! በጥቅቱ ጠቆም ለማድረግ ያህል የሚከተለውን ዐረፍተ ነገር እጽፋለሁ፡፡ በአለማችን ጥንታዊ የሚባለው መድንበ3ሺህ ዓ.ዓ ቻይናዊያን የጀመሩት ሲሆኑ በወቅቱም ነጋዲያን በሸቀጦቻቸው ላይ በአንድ ማጓጓዢያ እቃ መጫን እና መጠቀም የሚደርሰውን አደጋ ብሎም የሚመጡ የጎርፋ እና መሰል አደጋወችን ለመከላከል በርካታ የማጓጓዣ አማራጮች በወሰዱ ማግስት ነበር፡፡ ከዚያም በሜሶፖታሚያ (ሳምራዊያን) ስልጣኔ ወቅት እየተስፋፋ መመጣቱ በድርሳናት ላይ ሰፍሯል፡፡ በተለይም እኤአ በ1750 ዓ.ዓ በሰፈረው የንጉስ ሐሙራቢ ሕግ እንደተመለከተው ነጋድያን በባህር በሚነግዱበት ወቅት እቃውን በጥሩ ሁኔታ እንዲደርስ አስቀድመው በብድር ያስጭናሉ፤እቃውም በጥሩ ሁኔታ ከደረሰ ለአበዳሪው ተጨማሪ ገንዘብ ጭምር እንደሚከፍል ይናገራል፡፡ ዳሩ ግን ይህ ሳይሆን ቀርቶ ዕቃው ቢጠፋ ወይም ቢዘረፍ የአበዳሪው ዋስትና ሙሉ ኃላፊነት ነው፡፡ (ቫውግሃን፡1997፡3) ከዚያም በኋላ በሜዲትራንያን ባህር የሚደረጉ የንግድ እንቅስቃሴወች ከነጋዲያን አስቀድሞ በተሰበሰበ አረቦን/Premium/ ለሚደርሱ የባህር ላይ ንግድ አደጋወች ማካካሻ ተደርገው ሲሰራባቸው ቆይቷል፡፡

በመካከለኛው ዘመንም በጥናታዊቷ የጣሊያን ዋጀንዋ ከተማ እኤአ በ1347 የመጀመሪያው ዘመናዊ የመድን ውል በሥራ ላይ ዋለ፡፡ ከዚህም የተነሳ መድን ከሌሎች ዓይነት የፍትሃብሄር ድርጊቶች ለመለየት ተሞክሯል፡፡ (ፍራንክሊን፡2001፡274)

ስለ መድን ውል በጠቅላላው ሲታሰብ ከትልቀቱ እና ስፋቱ የተነሳ በርካታ ተግዳሮቶች እንደሚኖሩ የታመነ ነው፡፡ በኢትዮጵያ መድን ሕግ እና ውሎች ዙሪያ በርካታ አሳሳቢ ችግሮች አሉ ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ እንኳንስ በሁለቱም ማለትም በሕግ እና በውሎች ዙሪያ ቀርቶ ከውሎች ውስጥ ጥቂቶችን በሚገባ ተመርጠው በአግባቡ ቢፈተሹ ብዙ አሳሳቢ ችግሮች እንደሚገኙባቸው የሚያከራክር አይደለም፡፡ (ዘካሪያስ ቀንዓ፡1998፡1)

Continue reading
  13558 Hits

ድጋፍ የተሳነው እና እየተዘነጋ የመጣው የኮንስትራክሽን ውሎች አማራጭ የግጭት አፈታት

 “In business as in life, you don’t get what you deserve, you get what you negotiate.”

Dr.Chester L. Karrass

መግቢያ

ግጭት የሰው ልጅ ወደ ምድር ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ  የነበረ፣ ያለ እንዲሁም በእልት ተዕለት የማህበራዊ መስተጋብር ውስጥ ሊከሰት የሚችል አለመግባባት ወይም ልዩነት ነው፡፡ ይህም አለመግባባት በጊዜና በሚገባ ካልተፈታ፣ በማህበረሰብ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትና አለመረጋጋት ሊፈጥር ይችላል፡፡ ይህንንም ተግዳሮት ለማስቀረት በማሰብ አብዛኛውን ጊዜ የመንግስት ባህላዊ ተግባር (traditional functions of government) በመባል የሚታወቀው ማለትም ቋሚ የሕግና ፍትሕ ሥርዓት በመገንባት ለሚነሱ ቁርሾዎች መላ ሊያገኙበት የሚችልበትን ሥርዓት መዘርጋት ነው፡፡ ይህም ሊሆን የሚችልበት አንዱ መንገድ መደበኛ ፍርድ ቤቶችን ወይም አማራጭ የግጭት መፍቻ መንገዶችን በየደረጃው በማቋቋምና ለሚነሱ ግጭቶች በጊዜ መፍትሄ በመስጠት ሊሆን ይችላል፡፡

በዓለምአቀፍም ሆነ በአገር ወስጥ የሕግ ሥርዓት አስተማማኝና በቂ የግጭት አፈታት ሥርዓት መኖር በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ይህም መሆኑ በህብረተሰቡ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ኑሮ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት ከማምጣቱ ባሻገር ተጠባቂ የሕግ ሥርዓት (Predictable legal system) እንዲኖረን ያደርጋል፡፡

የግጭት አፈታት ሲባልም በግራ ቀኝ በኩል የሚመጣ ማነኛውም ግጭት ወይም አለመግባባት ለመፍታት የሚተገበር ሥነ-ስርዓት ሲሆን ይህም በመደበኛው የፍርድ ሂደት ወይም በአማራጭ የግጭት አፈታት (alternative dispute resolution) መንገድ ሊከናወን ይችላል፡፡

Continue reading
  13330 Hits

የኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነትና በተግባር የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶች - ክፍል 1

መግቢያ

ይህ ጹሑፍ በ6ኛው የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ “የኮንስትራክሽን ዋስትና ሕጎች እና የገንዘብ ተቋማት አሰራር” በሚል አውደ ጥናት ላይ ለውይይት የቀረበ ነው፡፡

ዋስትና በውል አፈጻጸም ወቅት እንደተጨማሪ ግዴታ የሚቆጠር በሕግ ፊት ሊጸና የሚችል (juridical act) ተግባር ነው፡፡ በአለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ በአለማችን ከኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር ታያይዞ ዋስትና (security) የመጠቀም ልማድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጧል፡፡

ሆኖም ግን እኤአ ከ2007 ዓ.ም በኋላ ከዓለም ኢኮኖሚ መዳከም ጋር ተያይዞ የዋስትና ጥቅም በአግባቡ የታየበት ብሎም አሰፈላጊነቱም ጭምር ጥያቄ ምልክት ውስጥ የገባበት ጊዜም አይዘነጋም፡፡

ዋስትና መልኩ ይለያይ እንጂ በተግባር አገልግሎት ላይ መዋል የጀመረው እእኤ ከ2750ዓ.ዓ ገደማ ጀምሮ ነበር፡፡ በወቅቱም ዋስትናው ጥሬ ገንዘብ እንደመያዣነት በማቅረብ ነበር፡፡ በተለይ ስለ ሰው ዋስትና (surety) ሕግጋት እና መርሆዎች በተመለከተ ጥናታዊ ሮማዊያን እኤአ በ150ዓ.ም ገደማ ያዘጋጁት ተጠቃሽ ነው፡፡ (ጄፈሪ በርተን፡2000፡9) ከዚያም የሦስተኛ ወገን ዋስትና ወደ ማቅረብ የተሄደበትም ጊዜ ነበር፡፡ ዘመናዊ የፋይናንስ ተቋማት ማደግን ተክትሎ በዋናነት ለዓለምአቀፍ የሽያጭ ግብይቶች ክሬዲ (letters of credit) እየተስፋፋ የመጣበትን ሁኔታ እናገኛልን፡፡

Continue reading
  16350 Hits

የኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነትና በተግባር የሚስተዋሉ የሕግ ክፍተቶች - ክፍል 2

በክፍል 1 ላይ ጸሐፊው ስለ አጠቃላይ የዋስትና የሕግ ማዕቀፍ በአጭሩ ለማቅረብ ሞክሯል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ ስለ ኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነት፣ ዓይነቶች እንዲሁም በተግባር የሚታዩ ክፍተቶች ይዳስሳል፡፡

 

1. የኮንስትራክሽን ዋስትና (Construction security)

 

በኮንስትራክሽን ውል አፈጻጸም ወቅት በርካታ የዋስትና ዓይነቶች ሲተገበሩ ይታያል፡፡ ከቅድመ ግንባታ ጀምሮ በግንባታ ወቅት አንዳንዴም ከግንባታ በኋላ ለሚከሰቱ ችግሮች ዋስትና ጥቅም ላይ ሲውል ይሰተዋላል፡፡ በተለይም የህንጻ አሰሪዎች (Clients) ግንባታው በፈለጉት ጊዜና ዕቅድ መሰረት እንዲካናወንላቸው ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሳ ውሉ እንዲፈጸምላቸው አሰፈላጊ ከለላ እንዲኖራቸው ይሻሉ፡፡

በኢትዮጵያም አብዛኛው የኮንስትራክሽን ውሎች መንግስት አሰሪ በመሆን የሚቀርብባቸው ናቸው፡፡ ለማሳያ ያህል የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ፣ የኢንዲስትሪ ፓርኮች ግንባታ፣ የባቡር ዝርጋታ፣ የመንገድ ግንባታዎች ወዘተ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በተለምዶው የመንግስት ኪስ እርጥብ (solvent) ነው ቢባልም በውል አስተዳደር ወቅት በተለያዩ ምክንያቶች የክፍያ መዘግየት ይስተዋላል፡፡ በዚህ ጊዜም ሥራ ተቋራጩ ልክ እንደ አሰሪው ሁሉ ግዴታ አለተፈጸመልኝም ብሎ ጥያቄ ማቅረብ ይችላል፡፡ በመርህ ደረጃ አሰሪ ሆኖ የቀረበው የመንግስት መስሪያ ቤት ውል ባለመፈጸሙ ምክንያት ሥራ ተቋራጩ ውል አልተፈጸም በሚል መከራከሪያ ሊያቀርብ እንደማይችል ከፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 3177 ድንጋጌ እና ከተለመደው የላቲን አባባል፡- ‘Exceptio non adimpleti contractus’ (ግዴታ አለተፈጸመልኝምን እንደ መከራከሪያ አለማቅረብ) መረዳት ይቻላል፡፡

Continue reading
  20849 Hits

Political risks in construction industry in Ethiopia: who shall bear such risks?

 

 

1. Introduction

Risk is part of every human endeavor. From the moment we get up in the morning, drive or take public transportation to get to school or to work until we get back into our beds (and perhaps even afterwards), we are exposed to risks of different degrees. What makes the study of risk fascinating is that while some of this risk bearing may not be completely voluntary, we seek out some risks on our own (speeding on the highways or gambling, for instance) and enjoy them. While some of these risks may seem trivial, others make a significant difference in the way we live our lives.

Given the ubiquity of risk in almost every human activity, it is surprising how little consensus there is about how to define risk.

Continue reading
  6235 Hits