ስለባልና ሚስት የጋራ እና የግል ንብረቶች በተመለከተ የፌዴራሉን የቤተሰብ ሕግና የተመረጡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የቀረበ

መግቢያ

በፌዴራሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 213/1992 ከአንቀጽ 2 እስከ 4 በተጠቀሱት ድንጋጌዎች  ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣ በኃይማኖት እና በባሕል ሥርዓት መሠረት ሊፈጸም ይችላል፡፡ ከእነዚህ የጋብቻ መፈጸሚያ ስርዓቶች ውስጥ በአንደኛው ስነ-ስርዓት ጋብቻ የተፈጸመ እንደሆነ በጥንዶቹ መካከል በሕግ እውቅና የተሰጠው የትዳር ግንኙነት ተመስርቷል ይባላል፡፡ ጥንዶቹ ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት የጋብቻ መፈጸሚያ መንገዶች ውስጥ በአንዱ ጋብቻ ቢፈጽሙ የጋብቻ ውጤትን መሠረት በማድረግ በሕግ የጋራ እና የግል ንብረቶቻቸው ላይ የሚኖረው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡  

Continue reading
  5628 Hits

በፍርድ የተከለከለ ሰው ሞግዚት ፍቺ የመጠየቅ ሥልጣን አለው ወይ? በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በተሰጠ ውሳኔ ላይ የቀረበ ትችት

ከሰሞኑ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፍቺን በተመለከተ ለየት ያለ ውሳኔ ተሰጥቷል፡: ይህን ውሳኔ ለሕዝብ ይፋ ቢደረግ ጠቃሚ ሃሳብ እንዲሸራሸር ሊረዳ የሚችል ከመሆኑም በላይ ሕጉንም ለመፈተሸ ይረዳል በሚል አስተያየት ለአንባብያን ለማድረስ እሞክራለሁ፡፡ ጉዳዩ ይፋ ቢሆንም ይግባኝ ሊቀርብበት የሚችል በመሆኑ ለጊዜው የግለሰቦችን ስም ተቀይሯል፡፡ የጉዳዩ ዝርዝር ሁኔታውም ከዚህ በታች ባለው መልኩ ተቀምጧል፡፡

አቶ ሀ እና ወ/ሮ ለ 42 ዓመታት በትዳር ቆይተዋል፡፡ ትዳራቸውም የተደላደለ ነበር፡፡ በዚህ ትዳራቸው ጊዜ ውስጥ ልጅ ያልወለዱ ሲሆን አቶ ሀ ግን ከሌላ የወለዱት  አንድ ወንድ ልጅ አላቸው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አቶ ሀ በእድሜ መግፋት (እድሜያቸው 90 ይሆናል) ምክንያት አእምሮአቸው ላይ ከፍተኛ ችግር የተከሰተ በመሆኑ የሚሰሩትን አያውቁም፡፡ የአእምሮ ችግሩን መሰረት በማድረግም የአቶ ሀ ልጅ ወላጅ አባቴ በአእምሮ ችግር የተነሳ የሚሰሩትን አያውቁም በማለት በፍርድ ይከልከሉ፤ የሞግዚትነት ስልጣንም ይሰጠኝ ሲል ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመለከቱ፡፡ ፍርድ ቤቱም የግለሰቡን የጤና ሁኔታ የሚያሳይ የሕክምና ማስረጃ እንዲቀርብ እና ግለሰቡም በችሎት ቀርበው ሁኔታቸው እንዲታይ በማድረግ ፍርድ ቤቱ ግለሰቡ በራሳቸው ራሳቸውንና ንብረታቸውን ለመቆጣጠር የማይችሉ መሆኑን ተገንዝቧል፡፡ ይህን ተከትሎም ፍርድ ቤቱ አቶ ሀ ላይ የክልከላ (Judicial Interdiction) ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ በመቀጠልም የአቶ ሀ ልጅ አሳዳሪና ሞግዚት አድርጎ ሾሟቸዋል፡፡

የአቶ ሀ ልጅም ሞግዚትና አሳዳሪ የሚለውን ሹመት ካገኘ በኋላም ይህንን ሥልጣን መሰረት በማድረግ፣ ሞግዚት አድራጊዬ በእድሜ መግፋት ምክንያት በአእምሮአቸው ላይ የጤና መታወክ የተከሰተ ቢሆንም ተጠሪ ሊንከባከቧቸው አልቻሉም፤ ተለያይተው መኖር ከጀመሩም ረጅም ጊዜ ተቆጥሯል፡፡ ስለዚህ የሞግዚት አድራጊዬና የተጠሪ ጋብቻ እንዲፈርስ ይወሰንልኝ በማለት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልክተዋል፡፡ ወ/ሮ ለ ሞግዚቱ የፍቺ ጥያቄ ይወሰንልኝ ጥያቄ ለማቅረብም ሆነ ፍርድ ቤት ቀርቦ ለመከራከር አይችሉም፣ ለፍቺ የሚያበቃም ምክንያት የለም ሲሉ መቃወሚያና መልስ ሰጥተዋል፡፡

የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤትም፣ ሞግዚቱ ጋብቻ እንዲፈርስ ለመጠየቅ ስልጣን አላቸው ወይስ የላቸውም? የግራ ቀኙ ጋብቻ ሊፈርስ ይገባል ወይስ አይገባም? የሚል ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን መርምሮታል፡፡ አንደኛውን ጭብጥ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ሲተነትን

“… በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 370(1) መሰረት ሞግዚት አድራጊ ጋብቻ እንዲፈርስ ለመጠየቅ የሚችል መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ስለዚህ የአቶ ሀ ሞግዚት የሆኑት ልጃቸው ጋብቻው እንዲፈርስ ለመጠየቅ በሕግ ሥልጣን አላቻው ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በወ/ሮ ለ የቀረበውን ሞግዚት አድራጊው ጋብቻ እንዲፈርስ ለመጠየቅ አይችሉም የሚል ክርክርን አልተቀበለውም፡፡” 

Continue reading
  10767 Hits

Ilmi Maqaan Abbaa Isaa akka jijjiirramuuf kallattiidhaan gaafachuu ni danda’aa?

Ilmi Maqaan Abbaa Isaa akka jijjiirramuuf kallattiidhaan gaafachuu ni danda’aa? Xiinxala Raawwatiinsa SHH Kwt 42 fi 43 irratti taasifame.

Bu’uura Heera Mootummaa Federaalaa Kwt 36(1)(b) tiin daa’imni kamuu maqaa fi lammummaa qabaachuuf mirga qaba jechuun kaa’eera. Gama kanaan seerri maqaa namni tokko qabaachuu kan danda’u haala kamiin akka ta’e kaa’u immoo S/H/H kwt 32-46 akkasumas kwt 3358- 3360 tti jiran jalatti kaa’ameera. Bu’uuruma kanaan namni tokkoo maqaa firaa(family name),maqaa dhuunfaa tokko ykn isaa ol (first name) fi maqaa abbaa(patronymic ) qabaachuu akka qabu qajeeltoon isaa S/H/H kwt 32 jalatti kaa’ameera.

Continue reading
  2298 Hits

አዲስ ለተወለደ ህፃን ልጅ ስም የማውጣት መብት፤ የእናት ወይስ የአባት? - የሕግ ባለሙያዎች ወግ

 

መግቢያ

ከሰሞኑ በአንድ ጠበቆች፣ ዳኞች፣ ዓቃቢያነ ሕግች፣ የሕግ ምሁራን እና የሴቶች መብት አቀንቃኞች የተገኙበት የሴቶች እኩልነት እና ሰብዓዊ መብቶች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ተገኝቼ ሳለሁ፤ አንዲት ተሳታፊ ጠበቂት ሃሳቧን ስታጋራ ለህፃን ስያሜ የመስጠት መብት የወላጆች የጋራ መብት ነው ብላ በደፈናው ተናግራ ስትጨርስ የውይይቱ መሪ ይህን ሀሳብ በሕግ የተደነገገ መብት ነው ብላ ስትደግም ከተሳታፊዎች ጉርምምታ ሲበዛ ለምን አላጠራውም በሚል፤ ይህንን ንግግሯን የሚደግፍ የሕግ ማዕቀፍ ካለ በሚል ጥያቄ አቅርቤላት ነበር፡፡ አወያዪዋም የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ እና ሕገ-መንግሥቱ ይደነግጋል በማለት ምላሽ ስትሰጥ፤ በዚህ ነጥብ ላይ የጦፈ ክርክር ይነሳል፡፡

Continue reading
  3844 Hits

በ-ያለእድሜ ጋብቻ የሚጣሱ መብቶች

ጋብቻ ክቡር፣ ምኝታውም ቅዱስ እንደ ሆነ የሀይማኖት መጻህፍት ያስተምራሉ፡፡ ከዚህም ሌላ ጋብቻ የህብረተሰብ ተፈጥሯዊ መነሻ የሆነው ቤተሰብ የሚመሰረትበት በመሆኑ ከመንግስትና ከህብረተሰብ ያላሰለሰ የህግ ጥበቃ ይደረግለታል፡፡ ይህም ጉዳይ በበርካታ አለም አቀፋዊ፣ አህጉራዊና ብሄራዊ ህጎች እውቅና አግኝቷል፡፡

ይሁንና የጋብቻው ክቡርነትም ይሁን የምኝታው ቅዱስነት የሚረጋገጠው እንዲሁም መንግስትና ህብረተሰብ ህጋዊ ጥበቃ የሚያደርጉለትን ቤተሰብ ለመመስረት ብቁነት የሚኖረው ጋብቻው በህግ መሰረት የተፈጸመ ሲሆን ነው፡፡ ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒው በአማራ ክልል ከሚመሰረቱ ትዳሮች መሀከል ሰማኒያ ሁለት ከመቶ የሚሆኑት ያለ እድሜ ጋብቻ የሚፈጸምባቸው ናቸው፡፡

ከላይ የተገለጸው አሀዝ ከፍተኛነት ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነ ሲሆን ጽሁፉ ያለ እድሜ ጋብቻን ምንነት፣ የሰብአዊ መብት ስምምነቶች ስለ ያለ እድሜ ጋብቻ ያላቸውን አቋምና ያለ እድሜ ጋብቻን ለማስቆም የሚያጋጥሙ ችግሮችን በአጭሩ ይዳስሳል፡፡ በመቀጠልም በያለ እድሜ ጋብቻ የሚጣሱ መብቶችንና ያለ እድሜ ጋብቻ መፈጸም የሚያስከትለውን የህግ ተጠያቂነት በዝርዝር ይመለከታል፡፡

ያለ እድሜ ጋብቻ ምንነትና የሰብአዊ መብት ስምምነቶች አቋም

ኢትዮጵያ ውስጥ ከ140 በላይ የሚሆኑ ጐጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ አንዱና ዋናው ደግሞ ያለ እድሜ ጋብቻ ነው፡፡ በዚህ ያለ እድሜ ጋብቻ የአማራ ክልል በሀገር ደረጃ ቀዳሚውን ስፍራ የያዘ ሲሆን ይሄው ድርጊት ከገጠሩ የክልሉ ክፍሎች አልፎ በከተሞች አካባቢም ይፈጸማል፡፡

Continue reading
  17663 Hits
Tags:

የጋብቻ እና ፍቺ ሕጋዊ ውጤቶች ከተሸሻለው የቤተሰብ ሕግ አንፃር

 

መግቢያ

የሰው ልጆች በዚህ ምድር ላይ መኖር የጀመሩትና ማህበራዊ መስተጋብር እንድ ህብረተሰብ ክፍል ብሎም እንደ ሀገር መኖር የጀመሩበት ጊዜ እና ቦታ ላይ የታሪክ ሊቃውንት በእርግጥ ይሄ ጊዜና ቦታ ባይሉንም ረጅም ዘመናትን እንዳስቆጠሩ ይገልፃሉ፡፡ የአንድ ሀገር ወይም ማህበረሰብ መሠረት የሆነው ቤተሰብ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ የሕብረተሰብ መሠረት የሆነው ቤተሰብ የሚመሰረተው በተለያየ መልኩ ቢሆንም ዋናው ግን የህብረተሰቡ አካል የሆኑት ሰዎ (ወንድ እና ሴት) በሚፈጸሙት ጋብቻ ነው፡፡ ቤተሰብ የህበረተሰቡ ዋና መሶሶ በመሆኑ ትልቅ ቦታና ከበሬታ የሚሰጠው ነው፡፡ ይህ ትልቅ ቦታና ከበሬታ የሚሰጠው የህብረተሰቡ መሠረት የሆነ ተቋም እንደ ተቋም ከመቋቋሙ አንስቶ እስከ መጨረሻው ጊዜው ድረስ በሕግና እና ስርዓት መመራት ይኖርበታል፡፡ የቤተሰብ መመስርቻ የሆነው ጋብቻ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ኖሮት እንዲዘልቅ ህብረተሰቡ ባወጣው ሕግ መሠረት መመሥረት ይኖርበታል፡፡ እንዲሁም በቆይታው ጊዜ የሚፈጠሩትን ግንኝነቶችና ውጤቶች እንዲሁም በሕግ መሠረት ከለላ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ለምሳሌ ያህል የልጅ አስተዳደግና አስተዳደር፣ በትዳር ውስጥ ስለሚፈጠሩ ንብረቶች፣ ከትዳር በፊት የነበሩ ንብረቶች፣ በባልና ሚስት መሀል ስለሚኖረው ግለሰባዊ ግንኙነቶች፣ በዚህ ትዳር ውስጥ ሆኖ ማድረግ ስለተከለከሉ ነገሮች እና ወዘተ የመሳሰሉት በሕግ መሠረት መደንገግ ይኖርባቸዋል፡፡

ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ይህን የህብረተሰብ ምሰሶ የሆነውን ትዳር (ቤተሰብ) ሊያፈርሱት ይችላሉ፡፡ ይህ በሕግ መሠረት የተቋቋመው ተቋም በሕግ መሠረት ሕጋዊ በሆነ መልኩ ነው መፍረስ ያለበት፡፡ ፍቺ በሕጉ መሠረት በመፈጸም ትዳር ሲፈርስ የራሱ የሆነ ሕጋዊ ውጤት ይኖረዋል፡፡ የልጆች ቀለብ በትዳር ውስጥ የፈሩ ንብረቶች አከፋፈል ወዘተ በሕግ መሠረት መሆን ይኖርበታል፡፡

በዚህ ጽሑፍ ውስጥም የጋብቻና ፍቺ ሕጋዊ ውጤቶቻቸው ከቀለብ መስጠት፣ ንብረት ግንኙነት (Pecuniary effect) እና ግላዊ የተጋቢዎቹ ግንኙነት (personal effect) ላይ በማተኮር በአሁኑ ሰዓት በፌዴራል መንግስት ደረጃ የወጣውን የተሻሻለውን የቤተሰብ ሕግ ዙሪያ ያለውን የሕግ ማዕቀፍ እና አተገገባበሩ ላይ ትኩረት በማድረግ የሚዳሰስ ይሆናል፡፡

Continue reading
  58009 Hits

ሳይፋቱ ፍቺ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

 

1. መግቢ

ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ በጣም ጠቃሚ እና መሠረት የሆነ አካል ነው፡፡ ቤተሰብ አንድ ግለሰብን ከአጠቃላይ ማኅበረሰብ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ ድልድይ ነው፡፡ እንዲሁም ተፈጥሮዊ ኢኮነሚያዊ እና ማኅበረሰባዊ ጥቅም አለው፡፡ በእርግጥ ቤተሰብ በቁጥር ትንሽ ሊሆን ይችላል ነገረግን የአንድ ቤተሰብ መፍረስ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ይጎዳል፡፡

ቤተሰብ በጋብቻ እንደሚመሠረት ሁሉ በፍቺ ይፈርሳል፡፡ በተለምዶ በቤተሰብ ሕጋችን ከተቀመጡት ጋብቻ ከሚፈርስባቸው መንገዶች በተጨማሪ ተጋቢዎች ለተለያዩ ምክንያቶች ሲሉ ህጋዊ ፍቺ ሳይፈፅሙ የሚያደርጉት መለያየት አንዱ ሲሆን ሳይፋቱ ፍቺ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ሳይፋቱ ፍቺ ምንም እንኳን በሕግ አግባብ የሚደረግ ፍቺ ባይሆንም እንኳን ውርስ ላይ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ አሉት፡፡

 

Continue reading
  18940 Hits

ቀለብ የመስጠጥ ግዴታ ፅንሰ ሀሳብ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

 

1. መግቢ

ግዴታ ህጋዊ ግንኙነት ሲሆን መሰረታዊ መርሁም የሚያካተው አንድ ዕዳ ያለበት ሰው ወይም ባለዕዳ ለአበዳሪው ዕዳውን የሚፈጽምበት ሂደት ነው፡፡ በዚህ ግንኙነት ውስጥ ባለዕዳው ለአበዳሪው አንድን ነገር ለማድረግ ፣ ለመስጠት ወይም ላለማድረግና ላለመስጠት የሚያደርገው ህጋዊ ግዴታ ነው፤ በተቃራኒው ደግሞ አበዳሪው ከባለዕዳው የሚገባውን እና በሕግ የተፈቀደለትን ጥቅም የሚያገኝበት ሁነት ነው፡፡ ግዴታዎች ከሁለት ምንጮች ይቀዳሉ፤ የመጀመሪያው ከውል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከሕግ ነው፡፡ ከውል የሚመነጭ የግዴታ አይነት በተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ላይ የሚመሰረት ሲሆን ስምምነቱም በተዋዋይ ወገኖቹ ላይ እንደ ሕግ እንደሚያገለግል የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 1731 ያትታል፡፡ ሁለተኛው የግዴታ ምንጭ ደግሞ ከሕግ የሚመዘዝ ነው፤ የዚህ አይነት ግዴታዎች በቀጥታ ከሕግ  የሚመነጩ ሲሆን ግዴታውም በባለዕዳው እና አበዳሪ ሰዎች ሊቀየር ፣ ሊሻሻል እንዲሁም ሊቀር አይችልም፡፡       

ቤተሰብ የአንድ ማህበረሰብ በጣም ጠቃሚ እና መሰረት የሆነ አካል ነው፡፡ ቤተሰብ አንድ ግለሰብን ከአጠቃላይ ማህበረሰብ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ ድልድይ ነው፡፡ እንዲሁም ተፈጥሮዊ ኢኮነሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ጥቅም አለው፡፡ ቀለብ የመስጠት ግዴታ በአብዛኛው በቤተሰብ መካከል የሚገኝ ሲሆን ተገላቢጦሽ ባህሪ አለው፡፡ ይህም ወላጆች ለልጆቻቸው ለሚያደርጉላቸው እንክብካቤ እና ለማሳደግ ላለባቸው ግዴታ ልጆችም በተራቸው ለቤተሰቦቻቸው በዕርጅና ወቅት፣ በችግር ላይ ላሉ ወንድም እና እህት እና ለሚወልዷቸው ልጆች ቀለብ የመስጠት ግዴታ ይኖርባቸዋል፡፡ ቀለብ የመስጠት ግዴታ ዋንኛ ምንጩ ከሕግ ቢሆንም በስምምነት ግዴታውን መመስረት ግን በግልጽ በሕግ አልተከለከለም፡፡ ይህ የሆነውም ቀለብ የመስጠት ግዴታ መሰረቱ በቤተሰብ መካከል የሚገኝን ግብረገባዊ ወይም ስነ-ምግባራዊ የመተጋገዝ ፣ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ተግባር ስለሆነ ነው፡፡    

 

Continue reading
  13271 Hits

ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር፤ አንድምታዎቹ እና ተግዳሮቶቹ

 

  1. መግቢያ

በተሻሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 1 መሰረት ህጋዊ ጋብቻ በተለያዩ ሰነ-ስረዓቶች ሊፈፀም ይችላል፡፡ እነሱም በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣በሐይማኖት እና በባህል መሰረት የሚፈፀሙ የጋብቻ አይነቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ጋብቻ ከላይ በተጠቀሱት በአንዳቸው ስነ-ስርዓቶች ቢፈፀም እንኳን ውጤቱም አንድ መሆኑን የዚሁ ህግ አንቀፅ 40 ያትታል፡፡ ህጋዊ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ላይ ሁለት ዓይነት ውጤት ይኖረዋል፡፡ የመጀመሪያው በተጋቢዎች ግለዊ ግንኙነት ላይ የሚኖረው ውጤት ሲሆን፤ በስሩም የመከባበር ፣ የመተጋገዝና የመደጋገፍ ግዴታ ፣ ቤተሰብን በጋራ የመስተዳደር እና በጋራ አንድ ላይ የመኖር ግዴታዎችን ያቅፋል፡፡ ሁለተኛው ውጤት ደግሞ ጋብቻ በተጋቢዎች ንብረት ላይ የሚኖረው ውጤት ነው፡፡ ይህም ተጋቢዎች  ጋብቻቸውን በሚፈፅሙበት ጊዜ በግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ እና በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንበረታቸው ሆነው ሲቀሩ ከዚህ ውጪ ያሉ ንብረቶች በሙሉ የጋራ  ንብረት ይሆናሉ፡፡

ከጥንት ጀምሮ በወነዶችና በሴቶች መካከል ከነበሩ ማህበራዊ ግንኙነቶች መካከል ጋብቻ ሳይፈፀሙ እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር አንዱ ነው፡፡ የዚህ አይነት ግንኙነት ምንም እንኳን ለቤተሰብ መመስረት ምክንያት  ቢሆንም በህግ አግባብ የሚደረግ ጋብቻ ሟሟላት ያለባቸውን ሁኔታዎችን ያላሟላ ስርዓት ነው፡፡ በሀገራችን እንደ ፍትሃ ነገስት ያሉ ጥንታዊ ጋብቻ ህጎች ጋብቻ ሳይፈፅሙ እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖሩን ቢያወግዝም የፍትሐብሔር ህግ እና በተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አስፈላጊነቱን በማመን ከለላ አድረግውታል፡፡

  1. አንድምታዎቹ

የተሸሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ በአንቀፅ 98 ስር እንደሚያትተው ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር ማለት አንድ ወንድ እና አንድ ሴት በህግ በሚፀና አኳኋን ጋብቻ ሳይፈፀሙ በትዳር መልክ የኖሩ ሲሆን ነው፡፡ የዚህ አይነቱ ግንኙነት በህግ አግባብ  ከሚደረጉ ጋብቻ ጋር ተቃራኒ ነው ተብሎ ሰለሚታሰብ እንደ “ፍተሃ ነገስት” ያሉ ጥንታዊ ህጎች እንደ ሃጥያት በመቁጠር ያወግዙት ነበር፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ  በዓለማችን ከትዳር ውጪ የሚወለዱ ልጆችና የፍቺ መጠን ፍጥነት እየጨመረ ሲመጣ በተቃራኒው ደግሞ ከትዳር ውጪ አብሮ መኖር እየተለመደና እየበዛ መጥቷል፡፡ ይህም ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖርን ከለላ መስጠት አስፈላጊ እና የማይታለፍ መሆኑን ህጉ ተቀብሎታል::  እንደምክንያትነትም የኢትዮጲያ ህግ መንግስት አንቀፅ 34 ለቤተሰብ የሚሰጠው ከለላ ይነሳል፤ ይህም ልክ በህግ እንደሚደረግ ጋብቻ ሁሉ ጋብቻ ሳይፈፀም እንደ ባልና ሚስት አብሮ መኖርም ቤተሰብን ይመሰረታል፡፡

Continue reading
  16375 Hits

ጋብቻ በሚፈርስበት ወቅት የባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ሥነ-ሥርዓት ከሰበር ውሳኔዎች ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

 

መግቢያ

ጋብቻ የተፈጸመበት ስነ-ስርዓት ማናቸውም አይነት ቢሆንም የጋብቻ መፍረስ የሚያስከትለው ውጤት ተመሳሳይ ነው፡፡ ጋብቻ ከተጋቢዎቹ አንዱ ሲሞት ወይም በፍርድ ቤት የመጥፋት ውሳኔ ሲሰጥ ወይም ጋብቻ ለመፈጸም መሟላት ያለባቸው ሁኔታዎች አንዱ በመጣሱ ምክንያት በሕግ ጋብቻው እንዲፈርስ ሲወሰን ወይም የፍቺ ውሳኔ ሲሰጥ ሊፈርስ ይችላል፡፡

Continue reading
  14567 Hits