የባንክ ዋስትና ሰነዶች (Letter of Guarantees) በኢትዮጵያ ሕግ ያላቸው ሽፋን

የዋስትና ሰነዶች ባንኮች በተለይም ለደንበኞቻቸው ከሚሰጧቸው የብድር አገልግሎቶች መካከል ዋነኞቹ ናቸው። የዋስትና ሰነዶች በተለያዩ ስያሜዎች የሚጠሩ ሲሆን በዚህም መሠረት በእንግሊዝኛ ‘independent undertakings’, ‘performance bonds/guarantees’, ‘tender bonds/guarantees’, ‘independent (bank) guarantees’, ‘demand guarantees’, ‘first demand guarantees’, ‘bank guarantees’, and ‘default undertakings’ በሚሉ ስሞች ሊጠሩ ይችላሉ። ከዚህ በተጨማሪም እነዚሁ ሰነዶች ‘standby Letters of Credit’ ተብለው ሊጠሩ እንደሚችሉ የተለያዩ ጽሑፎች ያሳያሉ። በዚህ መጽሐፍ ውስጥም የዋስትና ሰነዶች የሚለው ጥቅል ስያሜን ለመጠቀም የተሞከረ ሲሆን አንዳንዶቹ ስያሜዎችም የዋስትና ዓይነቶችን የሚያመለክቱ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። የዋስትና ሰነዶች በባንኮች የሚሰጡት ደንበኞች የተለያዩ ስምምነቶችን ከሌሎች ሦስተኛ ወገኞች ጋር ፈጽመው ያለባቸውን ግዴታ በአግባቡ ለመወጣታቸው ከባንኮች ዋስትና እንዲሰጥላቸው በሚያቀርቡት ጥያቄ መሠረት ነው። የዋስትና ደብዳቤ የሚሰጠውም አንድን ሰው የብድር አገልግሎት ወይም እቃዎቸንና አገልግሎቶችን ለሌላ ሦስተኛ ወገን በብቃት እንዲያቀርብ መተማመኛ በመሆን ነው። ዋስትና ሰነድም አንድ ሰው አንድን የተለየና የተወሰነ ሥራ ለሌላ ሰው ለመሥራት ግዴታ ከገባ ይኸው ሰው በውሉ መሠረት የገባውን ግዴታ መፈጸም የሚችል መሆኑን ለማረጋገጥ ሌላው ሰው የሚያቀርበው ውል ነው። (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የሰበር መዝገብ ቁጥር 47004 ተመልከቱ) የዋስትና ሰነዶች የባንክ የብድር ዓይነቶች ወይም የብድር አገልግሎት መሆናቸውን ከማየታችን በፊት ግን የዋስትና ሰነዶች ምን ማለት እንደሆኑ ማየቱ ተገቢነት ይኖረዋል።

የዋስትና ደብዳቤ አንድ ደንበኛ የፈለገውን የንግድ እንቅስቃሴዎችና ግንኙነቶችን እንዲፈጽም ለማስቻል ደንበኛው ለአቅራቢው ወይም የአገልግሎት ተግባር ለመፈጸም የተዋዋለውን ደንበኛ ሥራውን እንዲያከናውን ለማስቻል የሚሰጥ ደብዳቤ ሲሆን የዋስትና ደብዳቤውን የሚያዘጋጀው ባንክም ሰነዱ የተዘጋጀለት ደንበኛ ግዴታውን መወጣት ባይችል ለተጠቃሚው በቀጥታ ግዴታውን እንደሚወጣ በማረጋገጥ  የሚዘጋጅ ነው። የዋስትና ሰነዶችን በተመለከተ የሕግ ሽፋን የሰጠው የተባበሩት መንግስታት ኮንቬንሽን (UN Convention on Independent Guarantees and Standby Letters of Credit) የዋስትና ደብዳቤ ምን ማለት እንደሆነ እና የዋስትና ደብዳቤ ዓይነቶችንም ለመዘርዘር ሞክሯል። በዚሁ አለም አቀፍ ሕግ መሠረትም የዋስትና ደብዳቤ በአዘጋጁ (በብዛት ባንኮች ሲሆኑ) ደብዳቤው ለተዘጋጀለት ተጠቃሚ ዋስትና የተገባለት ግዴታ በባለዕዳው የማይከፈል ቢሆን የዋስትና ደብዳቤውን የጻፉት ባንኮች ባለዕዳውን ተክተው ክፍያውን (ዕዳውን) ለመክፈል ዋስትና እንደሚሆኑ በመግለጽ የሚሰጥ ደብዳቤ ነው። ይሁንና ይህ ኮንቬንሽን የሚያገለግለው አለም አቀፍ የሆኑ ግብይቶችን በተመለከተ እንደሆነ ተገልጿል። ኮንቬንሽኑንም የፈረሙት ሀገሮች ጥቂት በመሆናቸው ሁሉም ሀገሮች በዚህ ስምምነት መሠረት ይዳኛሉ ባይባልም አብዛኛው ሀገራት ግን የዋስትና ሰነዶችን በተመለከተ በሚያወጧቸው ሕጎች የዚህን ስምምነት አንቀጾች ከግንዛቤ በመክተት ሊሆን ይችላል። ኮንቬንሽኑ በተለይም የተለያዩ ዓይነት የዋስትና ደብዳቤ ዓይነቶች እንዳሉ ደንግጓል።

በኢትዮጵያ ሕግ ከዋስትና ሰነዶች ጋር በተያያዘ መነሳትና መዳሰስ ካለበት ዋና ነጥቦች መካከል የዋስትና ደብዳቤ ምን ማለት እንደሆነ፤ የዋስትና ደብዳቤ ምን ምን ነገሮችን ማካተት እንዳለበት፤ የዋስትና ደብዳቤዎች ያላቸው ሕጋዊ አስገዳጅነት፤ የዋስትና ሰነዶች ከሌሎች የዋስትና ዓይነቶች (እንደ ሰው ዋስትና እና የንብረት ዋስትና) ጋር ያላቸው አንድነት እና ልዩነት፤ እንዲሁም የዋስትና ሰነዶች እየተሰራባቸው ካለው ልማዳዊ አሰራር መነሻ ያደረገ ሌላ ሕግ አስፈላጊነት እና የመሳሰሉት ነጥቦች መብራራት ያለባቸው ናቸው።

ዋስትና የገንዘብ፣ የሰው እንዲሁም የንብረት እና የሰነድ ዋስትና ሊሆን ይችላል። እነዚህ የዋስትና ዓይነቶች ግን በየራሳቸው ልዩነት ያላቸው ሲሆን ሁሉንም በተመሳሳይ መልኩ ትርጉም በመስጠት ወይም አንዱን በአንዱ እያቀያየርን መጠቀም በመደረታዊነት ያሉትን የተለያዩ የዋስትና ዓይነቶች እና ያላቸውን ጠቀሜታ የሚያጠፋ ይሆናል። በዋናነት በንብረት፤ በሰው እና በሰነድ ዋስትና መካከል ያለውን ልዩነት ለመገንዘብ የፍትሐብሔር ሕጉን ድንጋጌዎች መመልከት ያስፈልጋል።

የፍትሐብሔር ሕጉ የሰው ዋስትናን (Suretyships or Guaranteership) በተመለከተ ከአንቀጽ 1920 እስከ 1951 ድረስ ባሉት ድንጋጌዎች ሰፊ ሽፋን ሰጥቷል። እነዚህ የሕጉ ድንጋጌዎች ግን የሚገለጹት ስለ ሰው ዋስትና ሲሆን በዚህም መሠረት ግለሰቦች ራሳቸውን ለአንድ ብድር ዋስትና አከፋፈል ባለዕዳው በገባው ውል መሠረት ግዴታውን መፈጸም እንዲችል ለማረጋገጥ የሚሰጡት ዋስትና ነው። በፍትሐብሔር ሕጉ ላይ የተገለጹት ዋስትናን የተመለከቱት ድንጋጌዎች ከውል ሕግ ጋር የሚያያዙ በመሆናቸው የባንክ የብድር ግንኙነቶችን አስመልክቶ በባንክ የሚዘጋጁትን የዋስትና ደብዳቤዎችን የማይወክሉና የማይመለከቱ ናቸው። በባንክ የሚዘጋጁት የዋስትና ደብዳቤዎች በባንኮች ከመዘጋጀታቸው በፊት ዋስትና ደብዳቤው እንዲዘጋጅለት የጠየቀው ደንበኛ የዋስትና ደብዳቤውን ከማግኘቱ በፊት ለደብዳቤው መሠረት የሆኑ ሁለት ዓይነት የተለያዩ እና በራሳቸው የቆሙ ውሎችን ይዋዋላል። አንደኛው ውል የዋስትና ደብዳቤው እንዲዘጋጅለት የጠየቀው ሰው ሊፈጽመው የገባው የአገልግሎት ወይም የአቅርቦት ወይም ሌላ ግዴታን የተመለከተና ከሦስተኛ ወገን ጋር የሚገባው ውል ነው። ሁለተኛው ውል ደግሞ የዋስትና ደብዳቤውን ከባንክ እንዲፈቀድለት የሚጠይቀው ሰው ከባንኩ ጋር የሚገባው ውል ነው። ይህ ውል የዋስትና ደብዳቤ እንዲጻፍለት ጥያቄ ያቀረበው ሰው ደብዳቤው በባንኩ እንዲጻፍለት ባንኩ የሚጠይቀውን ዓይነት ዋስትና ማለትም የንብረት ወይም የጥሬ ገንዘብ ዋስትና በማቅረብ የሚዋዋለው የመያዣ ውል ነው። እነዚህ ሁለት ውሎችም እርስ በእርሳቸው የማይገናኙ እና በራሳቸው የቆሙ ናቸው ማለት ይቻላል። የዋስትና ደብዳቤው ደግሞ ከእነዚህ ውሎች በኋላ በባንኮች የሚሰጥ የዋስትና ሰነድ ሲሆን ይህንን በባንኮች ተዘጋጅቶ ለባለእዳው የሚሰጠውን ደብዳቤ ግን እንደ ውል ልንቆጥረው የምንችለው ሳይሆን በቅድሚያ ባንኮች እና የዋስትና ሰነዱን የጠየቀው ሰው በገቡት የመያዣ ውል አማካኝነት የሚዘጋጅ ደብዳቤ እንደሆነ የሚቆጠር ነው።  

በመሆኑም የዋስትና ደብዳቤው የሚዘጋጀው በባንኮች በመሆኑና በደብዳቤው ላይ የሚፈርመውም የሚያዘጋጀው ባንክ ብቻ በመሆኑና የዋስትና ደብዳቤው ላይ ዋስትና የተገባለት ሰውም ፊርማውን የማያኖር ሲሆን በደብዳቤው ላይም የምስክሮች ፊርማም ሆነ ስም በአብዛኛው አይቀመጥም። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚያሳየው ደብዳቤውን ውል ለማለት የውል መሠረታዊ ሁኔታዎችን ያላሟላ መሆኑን ሲሆን ውል ነው የምንል ቢሆን እንኳን ከራስ ጋር የተደረገ ውል እንደሆነ ከመቆጠር ውጪ ሌሎች ውሎች የሚያሟሉትን ነጥቦች የሚያሟላ አይደለም። በዚህም መሠረት የዋስትና ደብዳቤን ለማዘጋጀት በአብዛኛው የሚቀርበው የመያዣ ንብረት በመሆኑና የሰው ዋስትና በፍትሐብሔር ሕጉ በተቀመጠው መሠረት የዋስትና ደብዳቤ ለመጻፍ እንደመያዣ የማይቀርብ በመሆኑ በሰው ዋስትናና በሰነዶች ዋስትና መካከል መሠረታዊና ሰፊ ልዩነት እንዳለ መገንዘብ ያስፈልጋል ማለት ነው። በመሆኑም ይህ የዋስትና አገልግሎት በዋናነት ሰውን እንደዋስትና ወይም እንደ መያዣ ማቅረብን የሚመለከት አይደለም። ለዚህም ይመስላል የፍትሐብሔር ሕጉ ራሱ የሰው ዋስትናን እንደ አንድ የዋስትና ዓይነት በዘረዘረበት የሕጉ ድንጋጌዎች አሁን ባንኮች የሚጠቀሙባቸውን የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና፣ የውል ማስከበሪያ ዋስትና፣ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ደብዳቤዎችንና ሌሎችንም የተለያዩ ቅድመ ሁኔታዎችን መሠረት አድርገው እና ለተለያዩ ዓላማ የሚውሉትን የዋስትና ዓይነቶችም ቢሆን ለመዘርዘር ያልቻለው።

Continue reading
  20258 Hits

የኢትዮጵያ የብር ኖቶችና የባንኮች አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓተ-ልማድ ከአካል-ጉዳተኞች መብት አንጻር  

 

መግቢያ

 

በሀገራችን ከ20 ሚሊዮን  በላይ የአካል ጉዳት ያለባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ይገኛሉ፡፡ እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደማንኛውም ሰው የተለያዩ የመንግሥትና የግል ተቋማት አገልግሎቶችን ለመጠቀም የተለያዩ መሰናክሎች ይገጥሟቸዋል፡፡ በዚህ ጽሑፍ አካል-ጉዳተኞች በኢትዮጵያ የብር ኖቶች አጠቃቀም እና በባንክ አገልግሎት አሰጣጥ ረገድ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች ከሕግ እና ከአሰራር አንጻር እንዳስሳለን፡፡

 

Continue reading
  5358 Hits

Major Departures of the New Micro-Finance Business Proclamation

 

Unlike the mainstreaming financial institutions, microfinance institutions play an important role in providing access to finance for rural farmers, small businesses, and other people who are engaged in similar activities, and hence, it was necessitated to have a legal framework to govern this issue i.e., Proclamation No. 626/2009. However, for a variety of reasons the existing proclamation needs amendment and the lawmakers came up with a new proclamation, Proclamation No. 1164/2019 (‘the new proclamation’), which introduces some innovative concepts to the existing proclamation. Therefore, in this piece, I will display some of the fundamental issues which are introduced in the new amending Proclamation. 

 

The existing Proclamation defines ‘company’ as a share company in which capital is fully owned by Ethiopian nationals and hence, it clearly excludes foreign nationals of Ethiopian origin. As part of the policy shift however, the new Proclamation expands the meaning of ‘company’ as a share company as defined under the Commercial Code in which capital is fully owned by Ethiopian or Foreigners of Ethiopian origin (diaspora) or jointly owned by the Ethiopian and Foreigners of Ethiopian origin. Even though the company is registered in another country, as far as its capital is contributed by Ethiopian or Foreigners of Ethiopian origin, as stated under Proclamation No. 270/2002, the law still recognizes it as a ‘company’. Still and all, the new Proclamation excluded foreigners from the microfinance business. 

 

Continue reading
  4502 Hits

የሚንቀሳቀሱ ንብረቶችን በዋስትና በማስያዝ ብድር የመስጠት የባንኮች ኃላፊነት

 

 

መግቢያ

በሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ባንኮችና አበዳሪ የገንዘብ ተቋማት ብድር ለማበደር እንደመያዣነት ከሚመርጧቸው ንብረቶች መካከል በዋናነት የማይንቀሳቀስ ንብረት (ማለትም ህንጻዎችንና ቤትን) እንዲሁም ከተንቀሳቃሽ ንብረቶች ውስጥ ደግሞ መኪናን እንዲሁም ትላልቅ ማሽነሪዎችን ብቻ ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ በዚህም በተለይም አበዳሪ ባንኮች በዋናነት በቀላሉ ብድራቸውን ማስመለስ የሚችሉት በቀላሉ ሊጠፉ የማይችሉ ንብረቶችን በመያዣነት በመያዝ ነበር፡፡ ይህ ሁኔታም በተለይም ተበዳሪዎች የብድር ገንዘብ አግኝተው የንግድ እንቅስቃሴ ውስጥ ለመሳተፍ እና ለኢኮኖሚው እድገትም አስተዋጽኦ ከማድረግ አንጻር ሁኔታው አዳጋች እንደነበር የሚታወቅ ነው፡፡ በዚያው ልክም የብድር አቅርቦት ውስኑነትም ባንኮች ብድርን በሰፊው ላለማቅረባቸው ሌላው ምክንያት ነው፡፡

አሁን በተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ በነጋሪት ጋዜጣ የታተመው የሚንቀሳቀሱ ንብረቶችን በዋስትና በማስያዝ ብድር ለመበደር የሚያስችል አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1147/2011 (pdf)) (አዋጅ ቁጥር 1147/2011 በነጋሪ መተግበሪያ) በቅርቡ በስራ ላይ እንዲውል ታትሟል፡፡ በተለይም አዋጁ የያዛቸውና የሚያተኩርባቸው ነጥቦች ለአበዳሪ ባንኮችም ጭምር አዲስ በመሆናቸው አዋጁን የሚጠቀሙት አስፈጻሚዎችም ሆኑ የባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም ከዚህ አዋጅ ተጠቃሚ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ስለአዋጁ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ማድረግ ውስብስብነት የሚታይበትን ይህንኑ አዋጅ መሰረታዊ ነጥቦቹን ለማስገንዘብ ከፍኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ከዚህ በዘለለም አዋጅ የያዛቸው ሀሳቦች አዳዲስና ውስብስብ በመሆናቸው አዋጁ ላይ ግንዛቤ ካልተፈጠረ አዋጁ ከመውጣቱ ውጪ ተግባራዊነቱ እጅግ ከባድ እንደሚሆን የአዋጁን ይዘት በመመልት በቀላሉ መናገር ይቻላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ጽሑፍ ስለአዋጁ እና በባንኮች እንደት ሊፈጸም እንደሚችል እንዲሁም የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሲባል ምን ምንን ያካትታል፤ በዚህ አዋጅ ተጠቃሚ ለመሆን ምን ምን ጉዳዮችን ማማላት ያስፈልጋል፤ የአዋጁ ዋነኛ ትኩረት ምንድን ነው የሚሉና ሌሎች መሰረታዊ ነጥቦችን ጠቅለል ባለ መልኩ ዳሰሳ ተደርጎባቸዋል፡፡

Continue reading
  8035 Hits