በ1995 የወጣው የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ ሰዎች በርካታ የሕግ ጥበቃዎችን ያደርጋል። እነዚህ ጥበቃዎች በዋናነት በሕግ ፊት በእኩል የመታየት፣ በሕግ አግባብ የመዳኘት፣ አላግባብ ቤታቸውና አካላቸው ከመበርበር የመጠበቅ፣ ከሕግ አግባብ ውጭ ያለመያዝ፣ በጠበቃ የመወከል፣ ንፁህ ሆኖ የመገመት፣ የፍርድ ሂደታቸው በግልፅ ችሎት ፈጣን በሆነ መልኩ እንዲካሄድ የማድረግ፣ የሚቀርብባቸውን ማስረጃ የመመልከትና መስቀለኛ ጥያቄ የመጠየቅ፣ ኢሰብአዊ ከሆነና ጭካኔ ከተሞላበት ቅጣት የመጠበቅ እና በአንድ ወንጀል ሁለት ጊዜ ያለመቀጣት መብት ናቸው። እነዚህ መብቶች በአብዛኛው እድሜያቸው ከ18 አመት በላይ በሆኑ ወይም ለአካለመጠን በደረሱ ወጣቶች ላይ የሚተገበሩ ሲሆን አካለመጠን ባልደረሱ ሰዎች ላይ ሁኔታው የተለየ ሆኖ ይገኛል። በወንጀል ለተጠረጠሩና ለተከሰሱ አዋቂ ሰዎች በሕግ የተቀመጡ ጥበቃዎች አካለመጠን ላልደረሱ ሰዎች ሲከለከሉ ወይም በዝምታ ሲታለፉ ይስተዋላል።
Corruption is becoming a major threat to the world. All countries of the globe are running the risks associated with it. Corrupt practices such as bribery and other abuses of public functions for private gain have been criminalised in almost all legal systems. The criminalisation of acts of corruption constitutes one of the major dimensions of the international anti-corruption instruments.
“I CAN’T DEFINE TAX EVASION, BUT I KNOW IT WHEN I SEE IT.”
— FRED T. GOLDBERG JR.
የታክስ ሥርዓት ከመንግስታዊ ስርዓት ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ሲሆን መንግስት እንደ መንግስት ለመቀጠል ታክስ መጣልና መሰብሰብ እንዲሁም የሰበሰበውን ታክስ ለዜጎች ማህበራዊ አገልግሎት ማዋል ይኖርበታል፡፡ ታክስ የመጣልና የመሰብሰብ ስልጣን የህግ መሰረት ሊኖረው የሚገባ ተግብር ሲሆን በዴሞክራሲያዊ ማህበረሰብ የዚህ ስልጣን ምንጭ በማህበራዊ ውል (social contract) መሰረት ዜጎች ለመንግስት የሚሰጡት ይሁንታ ነው፡፡
ኢትዮጵያውን የሚሳተፉባቸውን የማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሚጠቀምና ሌሎች ተጠቃሚዎች የሚጽፏቸውን ወይንም የሚጭኗቸውን ጽሑፎች፣ ምሥሎችና ድምፆች ለሚከታተል ሰው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንድ ግልጽ የሆነ አዝማሚያ እያደገ መምጣቱን ያስተውላል፡፡ ይኼውም ጥላቻን ያዘሉ ንግግሮች መበራከታቸውን ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር እጅግ ብዙ የሆኑ በጎ እሴቶችን የመናጃ መንደርደሪያ ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር ጥላቻ ላይ የተመሠረቱ ወንጀሎችን መጥሪያ ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር አድልኦና መገለልን ያመጣል፡፡ የጥላቻ ንግግር የአንድን ብሔር አባላት፣ የሃይማኖት ተከታዮች፣ ስደተኞችንና ሌሎች ቡድኖችን እንበለ ምክንያት በጭፍኑ እንዲጠሉ መንገድ ያለሰልሳል፡፡ የከፋው ደግሞ የዘር ማጥፋትን ወይንም ቡድን ጠረጋን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በበርካታ አገሮችም ተከስቶ ነበር፡፡
“In the Judgment alone is to be found the law in its living form.”
“ሕግ ህያው በሆነ ቅርጹ የሚገኘው በፍርዶች ውስጥ ብቻ ነው” Marcel Planiol
This post was originally prepared for use in the internal publications of the Ethiopian Human Rights Commission in an effort to strengthen the engagement of the Commission in protecting and promoting the rights of victims of sexual offences while at the same time ensuring the due process rights of the accused. However, it never got to see the light of day for reasons unrelated to its content. Now that we are done with the adoption of a criminal justice administration policy and taking up the revision of the criminal procedure code, it may be time to give it another try.
በአንድ ወቅት በፌደራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በታየ የስርቆት ወንጀል ጉዳይ ተከሳሹ ድርጊቱን መፈፀሙ ተረጋግጦ ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ፣ የቅጣት አስተያየቱን እንዲሰጥ የተጠየቀው ዐቃቤ ሕግ ‹‹…ተከሳሽ ድርጊቱን የፈፀመው መጥፎ አመልን በሚያሳይ ሁኔታ በወስላታነት…›› መሆኑን ለፍርድ ቤት በማስታወስ ቅጣቱ ከብዶ እንዲወሰን ይጠይቃል፡፡ ይሄንን የሰማው ተከሣሽም ዐቃቤ ሕጉን አቋርጦ ‹‹ኧረ የተከበረው ፍርድ ቤት ዐቃቤ ሕጉ ራሱ ወስላታ ነው፣ መቀጣቴ ካልቀረ መሰደቤ ለምን?›› ብሎ መከራከሩን ሰምቻለሁ፡፡
በእኛ ሀገር የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል? ተከሳሽ ምስክር መሆን አለመሆን ጥቅምና ጉዳቱ ምንድነው?
በአንድ ወቅት አንድ አስታጥቄ የሚባል ሰው ማረሚያ ቤት ልንጠይቀው ሔደን የተናገረውን አልረሳውም፡፡ ይኼው ጓደኛችን በስድብና ማዋረድ፣ ዛቻና የእጅ እልፊት ወንጀሎች ስድስት ወር ቀላል እስራት ተወስኖበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከወረደ በኋላ፤ በክርከሩ ሂደት መመስከርና ምስክር መሆን አትችልም መባሉ እንዳሳዘነው ሲነገረን ተደንቄ ነበር፡፡
በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145 ላይ አንድ ምስክር በፖሊስ ምርመራ ወቅት የሰጠው ቃል ዓቃቤ ሕግ ወይም ተከሳሹ ባመለከተ ጊዜ የተሰጠውን ምስክርነት ፍርድ ቤቱ ሊመለከተው እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ ይህ መብት የተሰጠው ለዓቃቤ ሕግ እና ለተከሳሽ በእኩል ደረጃ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ በሚባል አኳኋን እየተጠቀመበት ያለው ዓቃቤ ሕግ ነው፡፡ ዓቃቤ ሕግ በማስረጃነት የቆጠረው ምስክር በማንኛውም ምክንያት በችሎት ቀርቦ መመስከር ባልቻለ ጊዜ ሁሉ ዓቃቤ ሕግ የሚጠቅሰው ሥነ ሥርዓት የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 145ን ነው፡፡ በችሎት የቀረቡ ምስክሮች አጠራጣሪ ወይም የቀረበውን ክስ በሚገባ የማያስረዱ ሲሆን ዓቃቤ ሕግ ፊቱን ወደ 145 ያዞራል፡፡ 145 የዓቃቤ ሕግ የማስረጃ ክፍተት ማሟያ እየሆነ መጥቷል፡፡ ፍርድ ቤቶችም ይህንንኑ ለፖሊስ የተሰጠ የምስክርነት ቃል በአብዛኛው ተቀብለው በማስረጃት ሲጠቀሙበት ይሰተዋላል፡፡
በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡