The blogger worked as a legal expert at the Ethiopian food, medicine, and healthcare administration and control authority and Ethiopian Construction Works Corporation. The blogger is currently working as a qualified and licensed lawyer.

በወንጀል ጉዳይ በዋስትና እንዲፈታ ፍርድ ቤት ያዘዘውን ሰው ፖሊስ ይግባኝ ልል ነው በማለት ግለሰቡን ያለመፍታት የህግ ስልጣን አለው?

የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 19 (6) ስለተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት እንዳላቸው ሆኖም በህግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ እንደሚችል በግልፅ ተመልክቷል፡፡ ከዚህ ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ መረዳት የሚቻለው የዋስትና መብት መርህ (Principle) ሲሆን በዋስ አለመፈታት ደግሞ ልዩ ሁኔታ (Exception) መሆኑን ነው፡፡ ይህንን ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ ለማስፈፀም ተግባር ላይ ያለው የወ/መ/ስ/ስ/ህግ ምዕራፍ 3 ላይ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ስለመልቀቅ የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን በቁጥር 63 ላይ የዋስትና ወረቀት የሚያሰጡ መሰረታዊ ፍሬነገሮችን ይዘረዝራል፡፡ እነዚህ ፍሬነገሮች ዋስትና የሚያሰጡ ሁኔታዎችን የሚያስረዱ ቢሆንም በተቃራኒው በህግ አተረጓጎም መሰረት ዋስትና የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችንም በውስጡ አካቶ ይዟል፡፡

  4751 Hits

በኢትዮጵያ ስላሉ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች አንዳንድ ጉዳዮች

በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች የተለያዩ የከፉ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች (Genocide)፣ በሰው ልጆች ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች (Crimes against Humanity)፣ የጦር ወንጀሎች (War Crimes) እና የወረራ ወንጀሎች (Crime of aggression)፣ በሰላም ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች (Crime against Peace) እንዲሁም ወታደራዊ ወንጀሎች በተለያዩ ሰዎች አማካኝነት በተለያዩ የሰው ልጆች እና ተቋማት ላይ ሲፈፀሙ እንደነበር ታሪክ ይነግረናል፡፡ በአሁን ሰዓትም እነዚህ ወንጀሎች ከመሰራት አልቦዘኑም፡፡ የአንድ ሀገር የመከላከያ ሰራዊት አባል ወይም እንደአግባቡ ማንኛውም ሰው ለሚፈፅሙት የወንጀል ተግባር የሚቀርብባቸውን የወንጀል ጉዳዮች የሚመለከቱ ሀገር አቀፍ ወይም አለምዓቀፍ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች አሉ፡፡ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ወታደራዊ ፍርድ ቤት (Military Court) ወይም (Court-Martial) በመባል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው የሲቪል ፍርድ ቤቶች የተለዩ እና ቋሚ ወይም ጊዜያዊ ሆነው-ለተወሰነ ዓላማ እና ጊዜ የሚቋቋሙ ፍርድ ቤቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

  4430 Hits

የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ስልጣን ከአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ አንፃር

በአሁን ሰዓት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ማለትም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም የከተማ አስተዳደሮች ህጋዊ ጥንስሳቸው የአዲስ አበባ ከተማ ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያለው ሲሆን የድሬዳዋ ከተማ ደግሞ የቻርተር መሰረት ያለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት በኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 49 (1) መሰረት የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ነው በማለት ለከተማው እውቅና ሰጥቷል፡፡ የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 49 (2) የአዲስ አበባ ከተማ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለውም ደንግጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 የድሬዳዋ ከተማን በማቋቋም እራሱን በራሱ እንደሚያስተዳድር ደንግጓል፡፡

  13973 Hits

የፍርድ ቤቶች የእግድ ትእዛዝ ተፈፃሚነት እስከየት ድረስ ነው?

ለአንድ ሀገር ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ መረጋገጥ እንዲሁም ሰብዓዊ መብቶች መከበር በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ገለልተኛ፣ ነፃ፣ ተጠያቂነት ያለባቸው እና በሕዝብ ዘንድ አመኔታን ያተረፉ ፍርድ ቤቶች ሚና የጎላ እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ ያለሕግ እና ያለፍርድ ቤቶች ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ በአንድ ሀገር ውስጥ ይኖራል ብሎ መገመት አይቻልም፡፡

  13024 Hits

ስለወለድ እና የወለድ ወለድ አስተሳሰብ ደንቦች በጨረፍታ

ሰዎች ንብረታቸውን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድን ግዴታ ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸው ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል ስምምነት ሲፈፅሙ ውል እንዳደረጉ ከኢትዮጵያ የፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 1675 መረዳት ይቻላል፡፡ አንድ ውል ከተደረገ በኋላ በአንደኛው ወይም በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ላይ ግዴታን ይጥላል፡፡ ይህንን ግዴታ በተባለው ጊዜ አለመፈፀም ወይም ጊዜ ካልተቀመጠ ደግሞ ማዘግየት የሚያስከትለውን ኪሳራ በተመለከተ ተዋዋይ ወገኖች ገደብ ወይም ቅጣት ወይም አንድ የተወሰነ ወለድ ግዴታውን ያልፈፀመ ተዋዋይ ወገን ውሉን ላከበረው ወገን እንዲከፍል ሲዋዋሉ መመልከት ወይም በፍርድ ቤቶች ሲወሰን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ወለድና የወለድ ወለድ (Interest on interest or compound interest) አስተሳሰብ ደንቦችን በተመለከተ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የኢትዩጵያ ህጎች ላይ ተመስርተን በጨረፍታ እንደሚከተለው እንዳስሳለን፡፡

  26506 Hits
Tags:

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አንዳንድ ጉዳዮች

ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

  97823 Hits