ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here)

The arbitration agreement is an indispensable precondition for domestic and international commercial arbitration.  This is due to the fact that an arbitration contract is a process through which parties in dispute freely appoint their own private judge in lieu of a state judge to settle their dispute.  Nonetheless, whether the parties are at liberty to set all matters as they like, including the law(s) that will be applied to their case, is an issue. On the other hand, whether the arbitrators could settle as per the principle of laws or according to law and whether they have full autonomy to revise or rewrite the arbitration agreement to settle the parties’ dispute is also an issue. Seyoum’s article examines Ethiopian laws from hereinabove mentioned issues’ perspective. 

Continue reading
  1710 Hits

የሕግ ሙያ አገልግሎትን መቆጣጠር፣ የሕዝብ ጥቅም፣ የግለሰብ ፍላጎትና የውድድር ሕግ

በተለምዶ የሕግ ባለሙያዎች በንግዱ ዘርፍ ለሚንቀሳቀሱት ተወዳዳሪ ኃይሎች የተጋለጡ አልነበሩም፡፡ ይህ በሲቪል ሎው የሕግ ሥርዓት ተከታይ ሃገራት በአድቮኬቶችና ላቲን ኖታሪዎች እንዲሁም በኮመን ሎው የሕግ ሥርዓት ተከታይ ሃገራት በባሪስተሮች፣ ሎሊሳይቶሮች እና ኮንቬሮች መካከል ተመሳሳይ እውነታ ነበር፡፡ በእነዚህ በሁለቱ ሥርዓት የሕግ ሙያ ቁጥጥር የሚተገበረው በቀጥተኛ የመንግሥት ቁጥጥርና በላቀ ሁኔታ ደግሞ በራስ አስተዳደር (self regulation) ባለሙያዎች በተቀረፁ ሕጎች በመተዳደር ነው፡፡ ይህ የሕግ ሙያ ቁጥጥር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በእነዚህ ሥርዓቶች በፈጠረው የፀረ-ውድድር ተፅዕኖ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ እየተተቸ ይገኛል፡፡ 

Continue reading
  14168 Hits

ጠበቆች ሊለይዋቸው የሚገቡ አራት የደንበኛ ዓይነቶች - “ጀማሪ” ደንበኛ

 

ጠበቆች ከደንበኞቻቸው፣ ከፍርድ ቤት፣ ከፍትሕ ሥርዓት እና ከሌሎች የሥራ ባልደረቦች(ጠበቆች) ጋር ያላቸው ግንኙነት ለጥብቅና ሙያ ሥነ-ምግባር መሠረት ሲሆኑ እነዚህን ግንኙነቶች ጠንቅቆ መረዳት የጥብቅና ሙያ ኃላፊነትን በአግባቡ ለመረዳት ይረዳል።

ይህ ጽሑፍ ጠበቆች ከደንበኞቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለመረዳት የሚያስችል ስለደንበኞች ዓይነቶች ለመጠቆም የተዘጋጀ ነው። በዚህ ጽሑፍ የምድብ አንድ የደንበኛ ዓይነት “ጀማሪ ደንበኛ/ባለጉዳይ” የሚለውን ለማየት እንሞክራለን። ምንም እንኳን ሁሉም ደንበኞች ከዚህ በታች በተዘረዘሩት አራት ምድቦች ውስጥ በትክክል የሚገጣጠሙ ባይሆንም ደንበኞች ከሚያሳዩት ጸባይ እና ተነሳሽነት ደንበኞችን በአራት መመደብ ይችላል።

Continue reading
  3521 Hits

የፍርድ ቤት ወይስ የችሎት ስልጣን? (Jurisdiction of Courts or Divisions)

 

ይህን ለመጻፍ ያስገደዱኝን እና የገጠመኙን ሁኔታዎች በቅድሚያ ላብራራ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ሰራተኛ አሰሪው በነበረው ድርጅት ላይ ህገ-ወጥ የስራ ውል መቋረጥ ተፈጽሞብኛል በማለት ላቀረበው ክስ አሰሪው ድርጅት በተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠኝ ሰራተኛው የስራ ውሉን ስላቋረጠ ካሳ እንዲከፍለኝ የሚልና ሰራተኛው ስራ ላይ በነበረ ጊዜ ለስራው አገልግሎት የተሰጠውን ላፕቶፕ ኮምፒውተር ሳይመልስ በመቅረቱ ንብረቱን እንዲመልስ ወይም የንብረቱን ግምት ብር 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ) እንዲከፍለኝ በማለት ክስ አቀረበ፡፡ ጉዳዩን ሲያይ የነበረው የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የስራ-ክርክር ችሎትም በድርጅቱ የላፕቶፕ ንብረትን በተመለከተ የቀረበውን የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ይህ ችሎት (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የማየት ስልጣን ስለሌለው ጉዳዩን በዚሁ ፍ/ቤት በፍትሐብሄር ችሎት ክስ የማቅረብ መብታቸውን ጠብቄ አቤቱታውን ውድቅ አድርጌዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም ተከራይ ከአከራዩ ድርጅት ሶስት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችን በተለያየ ጊዜ የተከራየ ሲሆን በቅድሚያ ለተከራያቸው ሁለት ክፍሎች የውል ሰነድ ያለው ሲሆን ለሶስተኛው ክፍል ግን ከቃል ስምምነት ባለፈ በጽሁፍ የተደረገ ውል የለም፡፡ ነገር ግን ለሶስተኛው ክፍልም ቢሆን ለአራት ወራት ያህል በየወሩ ከተከራይ የኪራይ ገንዘብ የተቀበለበትን ደረሰኝ በማስረጃ አያይዟል፡፡ ይህንንም የኪራይ ውልና የኪራይ ክፍያ ደረሰኝ መሰረት በማድረግ አከራይ ላልተከፈለው እና ተከራይ ለተገለገለበት ጊዜ የኪራዩ ክፍያ ይከፈለኝ በማለት በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ክስ ያቀረበ ሲሆን ጉዳዩን ሲመረምር የነበረው የፍ/ቤቱ የኪራይ ችሎትም (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የኪራይ ውል ሰነድ ያላቸውን  ክፍሎች አስመልክቶ ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለኝ ሲሆን የኪራይ ውል የሌለውን ሶስተኛውን የቢሮ ኪራይ ክፍያ ክስ በተመለከተ ግን ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለው በዚሁ ፍ/ቤት የንግድና ልዩ ልዩ ችሎት ስለሆነ በዚህ ችሎት ክስ የማቅረብ መብታችሁን ጠብቄ በሶስተኛው ቢሮ ላይ ያቀረባችሁትን ክስ ዘግቼዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

ለመሆኑ በአዎጅ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች እንጂ ችሎቶች ይህን መሰሉ ስልጣን አላቸው? የፍትሐብሔር የሥነ-ሥርዓት ሕጉ ዓላማስ ከዚህ አኳያ እንዴት ይመዘናል የሚለውን በጥቂቱ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡- የፌደራል ፍ/ቤቶችን ያቋቋመው አዎጅ ቀ. 25/88 በፌደራል ደረጃ የሚኖሩት ፍ/ቤቶች የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት፣ ከፍተኛ ፍ/ቤት እና ጠቅላይ ፍ/ቤት መሆናቸውን ሲገልጽ የእነዚህ ፍ/ቤቶችም በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣንም ሆነ በይግባኝ ደረጃ ጉዳዮችን ተቀብለው አይተው እና አከራክረው ወሳኔ ሊሰጡ የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በዝርዝር ደንግጓል፡፡

ይህ አዎጅ ይህንንም ሲገልጽ እነዚህ የፌደራል ፍ/ቤቶች ጉዳየን ለማየት እንዳለቸው ስልጣን የተፋጠነ ፍትህን ለመስጠት እንዲያስችል እያንዳንዱ ፍ/ቤት ቢያንሰ ሶስት ችሎቶች እነዚህም የፍትሐብሄር፣ የወንጀል እና የስራ-ክርክር ችሎቶች ሊኖሩት እንደሚገባ (በፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 25/88 አ.ቁ 20(1) ፣23(1)) ሲደነግግ እንደሚቀርቡለት የጉዳዮች ብዛትና ዓይነት በስሩ እንደ ነገሩ ሁኔታ ሊይዛቸው የሚችሉ ችሎቶችን ፍ/ቤቱ በራሱ አስተዳደራዊ ውሳኔ የማብዛት መብት አለው (በተሻሻለው ፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 454/97 አ.ቁ 23(1))፡፡

Continue reading
  14590 Hits

ተደራሽ ግን ርካሽ ዳኝነት - የኦሮሚያ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ምልከታ



በዳኛው ገጠመኝ እንጀምር። የአንዱ የኦሮሚያ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ ለተዘዋዋሪ ችሎት በሕዝብ ትራንስፖርት እየሄደ ነበር። መኪናው ውስጡ ሞልቶ ረዳቱ ከላይ ለመጫን ይቃጣዋል። መኪናው ላይ የተፃፉ ጥቅሶች እንቅጩን ይናገራሉ።

"ታሪፍ እንጂ ትራፊክ የለም፣ ጠጋ ጠጋ በሉ" 
"የሰው ልጅ ክቡር ነው፣ ትርፍ ሰው የለም ግቡ"
"ሞላ የሰው ስም ነው፣ገባ ገባ በሉ"

ወዘተ። 

እና ዳኙዬ ተጣብቆ ቆሞ ከቦታው ደረሰና ችሎት ስራውን ይጀምራል። መኪና ውስጥ ወንበር ላይ ተቀምጦ የነበረ ባለ ጉዳይ ውጭ ቆሞ ከጓደኛው ጋር "ቆሞ የመጣው ሶዳ (አማቻችን) እዚህ ደርሶ ወንበር አገኘ" እያለ ይሳለቃል። ችሎት ተደፈረ? ፖሊስ የለም። የቀበሌ ታጣቂ እንኳን የለም።

 
ሰውየው ተራ ደርሶት ተጠራና ይገባል። ዳኛው ከንግግሩ ላይ ንዴት ይነበባል። ሰውየው ግን ቀላል ፎጋሪ አይደለም "ቅድም እኮ ዳኛ መሆንህን ባውቅ እነሳልህ ነበር" ብሎ ፈገግ አለ። ከፈገግታው ጥፊ ይሻላል። ችሎት ተደፈረ? የለም የለም! ይህ የዳኛው እውነተኛ ገጠመኝ ነው።

Continue reading
  8622 Hits

በሕግ አምላክ!

 

አገሬው ስለ ሕግ ሃያልነት ሲናገር "በሕግ አምላክ ሲባል እንኳን ሰው ወራጅ ውሃ ይቆማል" ይል ነበር፡፡ ሕግ ተፈጥሮንም እስከማቆም ሃይል እንዳለው አድርጎ ለመግለፅ ምን ዓይነት በሕግ የፀና እምነት ቢኖር ነበር ያስብላል፡፡ በሕግና ፍትሕ ላይ እምነት ያለው ሕዝብ ያለማንም አስገዳጅነት ለሕግ ተገዢ ነው፡፡ ክስተቶችንም ተከትሎ ለሕግ ያለውንም እምነት በተለያዬ መንገድ ይገልፃል፡፡ ግጭቶችን በጉልበት ከመፍታት በሕግ መፍታት ተመራጭ እንደሆነም ያምናል፡፡ በጉልበቱ አዳሪ ሲገጥመው ሰይፍን በሰይፍ ከመመለስ በሕግ አምላክ ቢል ይመርጣል፡፡ ከማትረባ ጉልበት በሕግ አምላክ ይሻላል የሚለውም ለዚህ ይመስላል፡፡ ስለዚህ የሕግ መከበር ሕበረተሰቡ ስለሕግና ፍትሕ ባለው አመለካከት ይወሰናል ማለት ነው፡፡ ሕግ በሕበረተሰቡ ውስጥ በሚፈለገው ደረጃ ለውጥ እንዲያመጣ ከተፈለገ እያንዳንዱ ሰው ስለሕግ ያለው አመለካከት አብሮ መመለወጥና ማደግ ይኖርበታል፡፡ ሕበረተሰቡ ለሕግና ፍትሕ ያለው አመለካከት ሁለት ነገሮችን ይገልፅልናል፡፡ በአንድ  በኩል ሕብረተሰቡ ስለሕግ ያለውን እምነት ሲገልፅልን በሌላ በኩል ደግሞ የሕግ መከበር ያለበትን ደረጃ ያሳየናል፡፡

ዘመናዊ የፍትሕ ሥርዓት ሳይዋቀር በፊት አገሬው ስለሕግ የበላይነት የፀና እምነት ነበረው ማለት እንችላለን፡፡ አስገዳጅ ነገር ሳይኖር በአገር ደንብ ብቻ መንገድ ላይ ባላጋራውን ሲያገኘው በሕግ አምላክ ብሎ ተላላፊው መንገደኛ ጉዳዩን እንዲመለከትለት ያደርግ ነበር፡፡ ተላላፊው መንገደኛም ዳኝነቱን ተቀብሎ የግራ ቀኙን ጉዳይ ሰምቶ ይፈርዳል፡፡ ውሳኔው ከተስማማቸው ይፈጽማሉ ካልተስማቸው በአካባቢው ወዳለው ጭቃ ሹም ተያይዞ መሄድ ነው፡፡ ይህን ተላላፊ መንገደኛ ዳኛ የሕግ ሙሁር አበራ ጀንበሬ የመንገድ ዳሩ ፍርድ ቤት(የመንገድ ዳር ዳኛ) በማለት ሲገልፁት ከሳቴ ብርሃን የአማርኛ መዝገበ ቃላት ደግሞ "ዳኛ የውሃ ወራጅ ዳኛ" በማለት ይገልፀዋል፡፡ ስያሜው ምንም ይሁን ተላላፊውን መንገደኛ ዳኛ፣ ባላጋራዎችን ተከራካሪ አድርጎ ሲያቆማቸው የነበረው ያገር ደንብና ልማድ፣ፈቃደኝነትና ለሕግና ፍትሕ የፀና እምነት መኖር  እንጅ ሌላ አስገዳጅ ሃይል አልነበረም፡፡

ሕዝብ ስለሕግና ፍትሕ ባለው የፀና እምነት ብቻ አገር ይዳኝ እንደነበር ሌላ ምሳሌ እንመልከት፡፡ በአዶልፍ ፓርለሳክ ተፅፎ ተጫኔ ጆብሬ መኮንን በተረጎመው የሃበሻ ጀብዱ መፃፍ የተገለፀ ነገር ነው፤ ታሪኩ 1928 ዓ.ም  አካባቢ አዲስ አበባ ገበያ ላይ የተመለከተው ነበር፡፡ ለአንባቢ እንዲመችና የነገሩን ሥር እንዳልስተው ቢረዝምም ተርጓሚው እንደፃፈው ሙሉ ታሪኩን ላስቀምጠው፡-

"በጨርቅ ተራ ሁለት ገበያተኞች ይጨቃጨቃሉ፤ጨርቁን የሚገዛው ሰውየ እጅግ በጣም ረጅም ሲሆን ሻጩ ደግሞ በጣም አጭር ነው፡፡ እናም ገዥ በሚችለው መልኩ ክንዱን ዘርግቶ፣ጣቶችን ወጥሮ አስር ክንድ ለካና ምልክት አደረገ፡፡ ሻጩ ደግሞ በሚችለው ሁሉ ጣቶችን ወጥሮ አስር ክንድ ለካና እሱም ምልክት አደረገ፡፡ ሁለቱ በለኩት መካከል ከአንድ ክንድ የሚበልጥ ልዩነት መጣ፡፡ ገዥው ሻጩን አውቆ ክንዱን ሳይወጥር ይለካል ሲል አመረረ፡፡ ሻጩ በምኒልክ እየማለ ሃቀኛ ነጋዴ መሆኑን እግዚአብሔርን ምስክርነት ጠራ፡፡ በዚህ መሀል ብዙ ወሬኛ ገበያተኞች ከበቧቸው፡፡ በነዚህ ወረኞች ፊት ሁለቱም ደጋግመው ቢለኩም ልዩነቱ ተመሳሳይ ነበር፡፡ እናም መግባባት ባለመቻላቸው ያላቸው ብቸኛ አማራጭ ዳኛ ፍለጋ መሄድ ነበርና ሸማቸውን አያይዘውና አቆላልፈው፣ ጎን ለጎን ግራና ቀኝ እጃቸውን በነጠላቸው ጫፎች ሸብ አድርገው አስረው ከቋጠሩ በኋላ ወደ ገበያው ሽምጋይ ዳኛ በብዙ ወረኞች ታጅበው ሄዱ፡፡

Continue reading
  8439 Hits
Tags:

The Right to Liberty and Privacy Right in Europe and the UK: Case Comment

The case originated by the application of two British nationals, Mr Kevin Gillan and Ms Pennie Quinton, against the United Kingdom of Great Britain and Northern Ireland alleging that the powers of stop and search used against them by the police breached their rights under arts 5, 8, 10 and 11 of the ECHR. The applicants were stopped and searched by police officers On 9 September 2003 near the site of an arms fair in east London, which was the subject of protests and demonstrations. The police officers told the applicants that they were searched under s 44 of the Terrorism Act 2000.  The 1st applicant, a doctoral student, was riding a bicycle and carrying a rucksack near the arms fair, on his way to attend the protest against the arms fair. He was told that he was being stopped for articles which could be used for acts of terrorism and handed a notice to this effect. He claimed that what the police officers responded for his inquiry about the reason he was stopped was that a lot of protesters were about and the police were concerned that they would cause trouble. Despite the seized computer printouts that give information about the protest, nothing incriminating was found on the 1st claimant and he was allowed to go after around 20 minutes of detention. The second applicant, a freelance journalist, holding a camera, wearing a photographer's jacket and carrying a small bag was stopped near the arms fair after she had apparently emerged from some bushes to film the protests. She was searched and told to stop filming by a police officer notwithstanding that she showed her press cards to show who she was. She was allowed to go on her way as nothing incriminating was found. She claimed that her intention to make a documentary or sell footage of it was disrupted as she did not feel able to return to the demonstration, due to the feeling of intimidation and distress.

The claimants sought to challenge the legality of the power of the executive (the police) to stop and search that was used against them, through judicial review. First, they argued that the authorisation and confirmation in question (under section 44 of the 2000 Act) were ultra vires and unlawful on the grounds of their geographical (which covered the entire London area) and temporal (which formed part of a rolling programme for over 8 years) coverage. They claimed that the authorization is unlawful as it was not made under the ground of necessity, rather on expediency. Secondly, they complained that the deployment of the s 44 authorisation by the police to stop and search them was unlawful and against the legislative intention and that the direction given to officers was either non-existent or intentionally left to cause the abuse of the power by the officers. Thirdly, the applicants argued that the power of authorisations under s 44 and its exercise infringed their ECHR rights under article 5, 8, 10 and 11.

On 31 October 2003, the Divisional Court rejected their claims on all grounds, and declared the powers as lawful and proportionate. The court, however, accepted the lack of guidance for police officers as to how to exercise their power to stop and search and suggested the police institute to have proper training and briefing procedures for Section 44. The applicants appealed to the Court of Appeal. On 29 July 2004, the Court of Appeal held that s 44 and 45 of the Act did not contradict with the provisions of the ECHR. The court recognized the exceptional nature of the power under s 44, but it said that the power is under a number of safeguards. The court of appeal, like the divisional court, however, pointed a suggestion for the police institute to have proper training and briefing procedures for Section 44. The applicants appealed to the House of Lords. On 8 March 2006, The House of Lords dismissed the applicants' further appeals holding that the authorisation under s 44, as well as its confirmation by the Home secretary were lawful and both the geographical scope and the duration of the authorisation were justified. The court also found that the authorisation for the use of stop and search powers to be compatible with ECHR.

Having exhausted their domestic remedies, the applicants applied to the ECtHR alleging that the police’s act of stop and search against the applicants under s 44 to 47 violated their rights under arts 5, 8, 10 and 11 of the ECHR. The ECtHR held that there had been a violation of art 8 of the Convention. The court also, while declining to rule on art 5(1), stated that the coercion happened on the appellants was indicative of a deprivation of liberty within the meaning of art 5(1). The following pages will try to give explanation on article 5 and 8 and evaluate the court’s approach and reasoning on the case.

The first legal issue the court analysed relates to article 5 of the convention which provides for right of liberty of a person. The right to liberty regulates state powers of detention and provides safeguards against ill treatment of detainees. It seeks to prevent the arbitrary use of executive power and create a climate conducive to the realization of human rights.. The ECHR, rather than simply protecting individuals against illegal and arbitrary detention, on its article 5(1), provides for an exhaustive list of grounds upon which detention is justified. If the detention is based on grounds other than listed under article 5(1), it is not justifiable and not permitted. For example, in A and Others v United Kingdom case, which involved the law that authorise the detention of alien terror suspects, the ECtHR held that this power of detention would fall foul of the principle that paras (a) to (f) amount to an exhaustive list of exceptions and that only a narrow interpretation of these exceptions is compatible with the aims of Article 5. The fulfilment of the grounds listed under article 5(1) by itself does not justify detention. Rather the detention should also be lawful and not arbitrary.

Continue reading
  8518 Hits

የዜግነት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ የቅድመ ሁኔታዎቹ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ:- ለአቶ ግዛው ለገሰ የተሰጠ ምላሽ

 

 

ስለ ዜግነት አዎጁ በፃፍኩት ጽሑፍ ላይ አቶ ግዛዉ ለገሰ የተባሉ የሕግ ባለሙያ የፃፉት ምላሽ ደርሶኝ ተመለከትኩት፡፡ (የአቶ ግዛው ለገሰ ጽሑፍን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ፡፡ ) በመጀመሪያ ጸሐፊው የሕግ ባለሙያ እንደመሆናቸውም ብሎም ጽሑፉን ያወጡት እሳቸው ስላልተስማሙበት የሕግ ጽሑፍ ምላሽ ለመስጠት እንደ መሆኑ አቶ ጀዋር መሐመድን ለመደገፍ አልፃፍኩትም ለማለት አቶ ጀዋር የራሱ ጉዳይ ብለው ጽሑፉን መጀመራቸው፤ በጽሑፉ ውስጥ ለተነሱ እያንዳንዱ ክርክሮች ተገቢውን የሕግ ክርክር ከማንሳት ይልቅ በአመዛኙ በተራ የአዋቃለሁ ባይነት ጉራ ተሞልተው እኩይ ሴራ የሚሉ ያልተገቡ ቃላቶች መጠቀማቸው ብሎም በጽሑፉ ውስጥ  ለድምዳሜቸው ማስረጃ አድርገው ስላቀረቡት የሕግ ግምት (presumption of law) ምንነት ያሉት ነገር አለመኖሩ እና ሃሳባቸው ልክ ስለመሆኑ የሚደግፍ የሕግ አስተምሮ ሳይጠቅሱ በደፈናው የሕግ ግምት ያልገባው የሚል የወረደ ምላሽ መስጠታቸው ከሙያ ሥነ-ምግባር የወጣ ተራ ብሽሽቅ የመሰለ መውረድ ሆኖ አግንቼዋለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ የመጀመሪየው ጽሑፍ በግልፅ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት ላይ ብቻ አተኮሮ እንደተፃፈ በተገለፀበት ሁኔታ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ስለሌላቸው እንደ በሕግ ዜግነት ስለማግኘት የመሳሰሉ ለምላሹ ፋይዳ በሌላቸው ዝርዝሮች ላይ ማተኮራቸውም አስቀድመው ላልተስማሙበት ጽሑፍ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በቂ እድል ነፍጓቸዋል ጊዜያቸው አጥንቱን በመጋጥ ላይ መዋል ሲገባው መረቅ ለመጠጣት ውሏል፡፡

እንግዲህ ከዚህ ቀጥየ የአቶ ግዛው የክርክር ነጥቦችን በእኔ መረዳት በሕግ እና በክርክር መርሆች አይን ስሁት መሆናቸውን እንደሚከተለው አሰረዳለሁ፡፡ ትክክለኛው እና አሳማኙ ክርክር የማን ነው የሚለው መዳረሻ የአንባቢ እንጂ የጸሐፊዎች ባለመሆኑ እንደ አቶ ግዛው የኔ ሃሳብ የጉዳዩ ዳርቻ ነው የሚል ትዕቢት አይዳዳኝም፡፡ በጉዳዩ ላይ ስፅፍም የጉዳዩ ትኩረት ማግኘት ትኩረት ከመሳቡ ውጭ የተለየ አትኩሮት ለጉዳዩ እንደሌለኝ በቅንነት ስገልፅ ይህን ማመን ወይም መጠራጠር በእጃችሁ ነው፡፡

የአቶ ግዛው ጽሑፍ አልፋ እና ኦሜጋ በዜግነት አዋጁ ላይ የተጠቀሱት ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች የሕግ ግምት በመሆናቸው ያለምንም የተለየ ሥርዓት ዜግነት ያሰጣሉ ቅድመ ሁኔታዎቹ አልተሟሉም ካለ ማስረጃ የማቅረብ ሃላፊነት (የማስረዳት ሸክም) የኮሚቴው ነው የሚል ነው፡፡

Continue reading
  7547 Hits
Tags:

በኮሮና ወረርሽኝ ፍርድ ቤቶችን እንዴት ማስቀጠል ይቻላል?

 

እርግጥ ነው አሁን ያለንበት የኮሮና ቫይርስ ወረርሽኝ ወቅት እጅግ ፈታኝ፣ ፈጣን አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመስጠት የሚከብድበት የቱ ትክክልየቱ ስህተት እንደሆነ ለማመዛዘን የሚቸግር ጊዜ ነው፡፡ በተለይም በወረርሽኙ ምክንያት የሰዎች ህይወት አደጋ ላይ መውደቁ ሲታይ አሳሳቢና አስጨናቂ ነው፡፡

በዛው መጠን ደግሞ በማዕበሉ ወቅትም ቢሆን ህዝብና የመንግሥት አስተዳደር ይቀጥላል፡፡ ፍርድ ቤቶች ደግሞ እጅግ በጣም አስፈላጊና ወሳኝየህዝብ አገልግሎት ሰጪ አካላት መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ሐቅነው፡፡ ፍ/ቤቶች ከሶስቱ የመንግሥት አካላት (the three organs of Government/state) አንደኛው ቅርንጫፍ/አካል ናቸው፡፡ ሌሎቹ የመንግሥት አካላት(አስፈፃሚውና ሕግ አውጪው) ሥራቸውን እያስኬዱ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በወረርሽኙ ምክንያት የሰውን ህይወት ለአደጋ በማያጋልጥና በጥንቃቄ ሥራቸውን የሚያስኬዱበት መንገድ ሊፈተሸ ይገባል፡፡

በጣም የሚያስደነግጠው ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ‹‹የኮሮና ቫይረስ ለማጥፋት በርካታ ዓመታት ሊወስድ ይችላል፡፡ የሚጠፋበት ጊዜ ቅርብ አይደለም እንደውም እንደ ኤች.አይ.ቪ ላይጠፋ ይችላል›› የሚል መግለጫን አውጥቷል፡፡

ስለዚህ ፍርድ ቤቶችም ሆኑ ሌሎች ወሳኝ አገልግሎት ሰጪ አካላት በቀጣይ ከቫይረሱ ጋር በጥንቃቄ ህይወት የሚቀጥልበትን መንገድ ሊያስቡበት ግድ ይላቸዋል ማለት ነው፡፡ እጅን አጣጥፎ ‹‹ጥሩ ቀን ቶሎ ና›› እያሉ ብቻ መጠበቅ አያስኬድም አያዋጣም፡፡

Continue reading
  4671 Hits

የፍርድ ቤቶች በከፊል መዘጋት በማረምያ ቤት ከሚገኙ እስረኞች መብት አንጻር

 

 

የኮሮና (COVID-19) በሽታ አለም አቀፍ ችግር ሆኗል፡፡ በአለም ላይ ያሉ ሳይንቲስቶች በደረሱበት የምርምር ደረጃም በትክክል የሚተላለፍባቸው መንገዶች በሙሉ ተለይተው አይታወቁም፡፡ ነገር ግን በሽታው በሰዎች መካከል በሚኖር ቀጥተኝ (መጨባበጥ፤ መተቃቀፍ..) እና ቀጥተኛ ያልሆነ (አንድ ሰው የነካውን ግኡዝ ነገር ሌላ ሰው በመንካት …) አካላዊ ንክኪ እና የትንፋሽ ግንኙነት በቀላሉ የሚተላለፍ መሆኑ በትክክል ይታወቃል፡፡ ይህ ከሰዎች ባሕሪ ጋር በቀጥታ የተገናኘ የመተላለፍያ መንገዱ በሽታውን እጅግ አደገኛ እና አስፈሪ አድርጎታል፡፡ በሽታው ምንም አይነት ፈዋሽ መድሀኒት የሌለው መሆኑ እና ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍበት እና የሚሰራጭበት ፍጥነት በድምር ሲታይ ብሔራዊ ስጋት ተደርጎ እንዲወሰድ አድርጎታል፡፡ በበሽታው የተፈጠረው ብሔራዊ ስጋት ተራ ስጋት ሳይሆን ከፍተኛ እና ከባድ ስጋት ነው፡፡   

በሽታው ምንም አይነት ፈዋሽ መድሀኒት የሌለው ከመሆኑ አንፃር ያለው ብቸኛ መዳኛ መንገድ በበሽታው ላለመያዝ አስቀድሞ የሚደረግ የመከላከል ተግባራትን መፈፀም ብቻ ነው፡፡ የሕክምና ባለሙያዎች ከበሽታው አስቀድሞ መከላከያ መንገዶች አድርገው በዋናነት የሚጠቅሷቸው ዘዴዎች አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና ንፅህናን መጠበቅ ናቸው፡፡

አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የሚለው የመከላከያ ዘዴ ሰዎች በቤታቸው ተቀምጠው ራሳቸውን ከሌላው ሕብረተሰብ ከልለው እንዲቀመጡ ከማድረግ ጀምሮ በስራ፤ በትራንስፖርት እና በሌሎች አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥም ቢያንስ የሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ርቀትን በማስጠበቅ እንዲንቀሳቀሱ እና አገልግሎት እንዲገኙ ማድረግን የግድ ይላል፡፡ ይህን በከተማ ብሎም በሀገር ደረጃ ተግባራዊ ማድረግ እና ተግባራዊነቱን መከታተል እና መቆጣጠር ቀላል ተግባር አይደለም፡፡ በዚሕ መሀከል የሚፈፀም ትንሽ ስህተት ተቆጥሮ የማያልቅ የብዙ ሰዎችን ሕይወት የሚቀጥፍ ወይም አደጋ ላይ የሚጥል ውጤት ሊያስከትል ይችላል፡፡

Continue reading
  5134 Hits