Criminal Reinstatement in Ethiopia: Exploring the Factors Behind its Limited Application

Introduction

Criminal reinstatement (simply reinstatement) also known as “Expungement” or “Expunction” in the common law legal system is a legal process that allows individuals with criminal records to have their convictions removed from public records. This means that the records are destroyed; making them inaccessible to organizations that may conduct background checks. Reinstatement is a concept included in our criminal code and criminal procedure code, but the law and its details are hardly known in our society. As a result, it is not widely used. This paper explores the concept of reinstatement, its difference from pardon, the eligibility criteria, the process involved, its relevance in helping individuals reestablish their lives following a conviction, and the impact it has on individuals and society as a whole. It also highlights the gaps in the current practice of criminal reinstatement and concludes with recommendations for improvements. 

  1494 Hits

Criminalizing and Prosecuting Illicit Enrichment in Corruption Cases

Corruption is becoming a major threat to the world. All countries of the globe are running the risks associated with it. Corrupt practices such as bribery and other abuses of public functions for private gain have been criminalised in almost all legal systems. The criminalisation of acts of corruption constitutes one of the major dimensions of the international anti-corruption instruments.

  15032 Hits

ወስላትነት በኢትዮጵያ ሕግ ምን ማለት ነው

በአንድ ወቅት በፌደራሉ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በታየ የስርቆት ወንጀል ጉዳይ ተከሳሹ ድርጊቱን መፈፀሙ ተረጋግጦ ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ፣ የቅጣት አስተያየቱን እንዲሰጥ የተጠየቀው ዐቃቤ ሕግ ‹‹…ተከሳሽ ድርጊቱን የፈፀመው መጥፎ አመልን በሚያሳይ ሁኔታ በወስላታነት…›› መሆኑን ለፍርድ ቤት በማስታወስ ቅጣቱ ከብዶ እንዲወሰን ይጠይቃል፡፡ ይሄንን የሰማው ተከሣሽም ዐቃቤ ሕጉን አቋርጦ ‹‹ኧረ የተከበረው ፍርድ ቤት ዐቃቤ ሕጉ ራሱ ወስላታ ነው፣ መቀጣቴ ካልቀረ መሰደቤ ለምን?›› ብሎ መከራከሩን ሰምቻለሁ፡፡

  14677 Hits

ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል?

በእኛ ሀገር የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ተከሳሽ ምስክር መሆን ይችላል? ተከሳሽ ምስክር መሆን አለመሆን ጥቅምና ጉዳቱ ምንድነው?

በአንድ ወቅት አንድ አስታጥቄ የሚባል ሰው ማረሚያ ቤት ልንጠይቀው ሔደን የተናገረውን አልረሳውም፡፡ ይኼው ጓደኛችን በስድብና ማዋረድ፣ ዛቻና የእጅ እልፊት ወንጀሎች ስድስት ወር ቀላል እስራት ተወስኖበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከወረደ በኋላ፤ በክርከሩ ሂደት መመስከርና ምስክር መሆን አትችልም መባሉ እንዳሳዘነው ሲነገረን ተደንቄ ነበር፡፡

  13443 Hits

ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፍርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር

በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡

  16282 Hits

ስለ “የታሰሩ ሰዎች መብቶች” አንዳንድ ነጥቦች

በማያ ጋዜጣ ሐምሌ የታተመ በሰሞኑ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የችሎት ውሎዎች በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የጋራ የወንጀል ሕጉን የማስፈጸም ተግባር ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የተለያዩ መንግስታዊ መሥሪያ ቤቶች ዳይሬክተሮችን ጨምሮ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪነት ተይዘው የጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀባቸው የሚገኙት እስከ ሣምንቱ አጋማሽ ድረስ ቁራቸው 45 የደረሱ ተጠርጣሪዎች በእሥር ላይ የሚገኙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የሕግ እርምጃው ቀጣይነት ያለው መሆኑንም በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በኢቢሲ መግለጫ ተነግሯል፡፡ የተጠርጣሪዎችን በእሥር ላይ መዋል ተከትሎ በመንግስትም ሆነ በግል መገናኛ ብዙሃን ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመውታል ተብሎ ስለተጠረጠሩበት ወንጀል ዝርዝር የገንዘቡን መጠን ጨምሮ በስፋት ሲዘገብ እየተመለከትንና በጋዜጦች እያነበብን ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎቹን በሕግ መሠረት በቁጥጥር ሥር አውሎ፣ ክስ አቅርቦ ጥፋተኝነታቸው በማስረጃ የተረጋገጠባቸውን በህጉ መሠረት እንዲቀጡ ማድረግ መሰረታዊ የህግ ዓላማ እንዲሁም አንደኛው የሕግ አስፈጻሚዎች ሥልጣንና ተግባር ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በእሥር ላይ የሚገኙት ተጠርጣሪ እሥረኞችን ሕገመንግሥታዊ መብቶችን የማክበሩ ጉዳይም ከተጠያቂነቱና የወንጀል ህጉን ከማስፈጸሙ እኩል ጎን ለጎን ትኩረትን የሚሻ ነው፡፡ የሰዎች መብቶችና ግዴታዎች ሁል ጊዜ ጎን ለጎን በትይዩ የሚፈጸሙ መሆናቸው መሠረታዊ የህግ መርህ ነው፡፡ 

  15750 Hits

እያመለጠ ያለን የጊዜ ቀጠሮ እስረኛ ተኩሶ መግደል በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ

አንድ ሰው ወንጀል በመስራት በመጠርጠሩና የተጠረጠረበት ወንጀል በሕጉ ዋስትና የማያስፈቅድ በመሆኑ ወይም በዋስትና ለመውጣት አስፈላጊ የሆኑት ነገሮች እስኪከናወኑ ጊዜ ድረስ በእስር ላይ ሊቆይ ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ እስረኛው በሕጉ የተፈቀደለት የሰብአዊ ክብር እንክብካቤና በሕይወት ለመቆየት አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች በሙሉ እየተሟሉለት የፍርድ ሂደቱን የመከታተል መብት አለው፡፡ እስረኛው በፍ/ቤት ወንጀለኛ ተብሎ ያልተፈረጀ ይልቁንስ በህገመንግስቱ አንቀፅ 20/3/ መሠረት ንፁህ ሆኖ የመገመት መብት ያለው በመሆኑ ተገቢው ክብርና እንክብካቤ የሚገባው ነዉ፡፡

  28595 Hits

ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ ስለመስማት (Trial in absentia)

1.  ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ ስለመስማት (Trial in absentia) ፅንሰ ሃሳብ

ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት (Trial in absentia) ማለት ተከሳሹ በወንጀል ክሱ በፍርድ ቤት ጉዳዩ በመታየት ላይ የሚገኝ ቢሆንም ተከሳሹ ግን በአካል በፍርድ ቤት ሳይገኝ ጉዳዩ በሌለበት በመታየት ላይ የሚገኝ ማለት ነው፡፡ ይህ አይነቱ የህግ ስረዓት በተለያዩ ሃገሮች የሚተገበር ሲሆን በእኛም ሃገር በወንጀል ሥነሥርዓት ህጉ እና በመገናኛ ብዙሃን የመረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 ላይ በልዩ ሁኔታ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክስ መስማት ተገቢነቱ መታየት ያለበት ከወንጀል ህጉ አላማ፤ ከፍትህ እና ከሰብዓዊ መብት አንፃር ነው፡፡

  14537 Hits

በአደባባይ የሚፈጸም ብልግና እና የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ

የዛሬው ጽሑፍ የሚያጠነጥነው በወንጀል ሕግ ዙሪያ ነው፡፡ የወንጀል ሕግና የኅብረተሰቡ የሞራል አስተሳሰብ የጠበቀ ቁርኝት አላቸው፡፡ በአብዛኛው በኅብረተሰቡ እንደ ኃጢያት ወይም ነውር የሚቆጠሩ ድርጊቶች በወንጀል ሕግም የሚያስጠይቁ ናቸው፡፡ አመንዝራነት፣ ስርቆት፣ ስድብ፣ ግብረሰዶም ወዘተ. ኃጢያት ወይም ነው ብቻ ሳይሆኑ ወንጀልም ተደርገው በወንጀል ሕጉ እንደሚያስቀጡ ተመልክቶ እናገኛለን፡፡ ይሁን እንጂ ኃጢያት ወይም ነውር የሆነ ድርጊት ሁሉ ግን ወንጀል ላይሆን ይችላል፡፡ ዝሙት አዳሪነት ለዓብነት ብንመለከት ድርጊቱ ኃጢያት ወይም ነውር መሆኑ ባያጠያይቅም፣ በወንጀል ሕጋችን በመርህ ደረጃ የወንጀል ኃላፊነት የማያስከትል ድርጊት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡

  12124 Hits
Tags:

በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት ወንጀለኛን (ተጠርጣሪን) የመያዝ አጠቃላይ አካሔድ

በዚህ ጽሑፍ በኢትዮጵያ የወንጅል ፍትሕ ሥርዓት ውስጥ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር ስለመዋል ወይም ስለመያዝ የሚመለከቱ መሠረታዊ ጉዳዮችን ለማብራራት ጥረት ተደርጓል፡፡ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠውን የሰዎች የነፃነት መብትና በፖሊስ በወንጀል ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር ስለመዋል መካከል ስላለስ ግንኙነት በትንሹ ገለፃ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡ በተጨማሪም ተጠርጣሪዎች የሚያዙባቸውን መንገዶችና እንዴት በቁጥጥር ሥር እንደሚውሉ የሚደነግገውን የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ክፍል በጥልቀት ለመርመር ሙከራ ተደርጓል፡፡

  14505 Hits