በሀገራችን እጅግ አሳሳቢ እና አነጋጋሪ ከሆኑት የወንጀል ድርጊቶች መካከል በአሽከርካሪዎች የሚፈጸመው ወንጀል ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል ለማለት ይቻላል፡፡ ከትራፊክ ፖሊስ ዕለታዊ ሪፖርት በየዕለቱ እንደምንሰማው በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ እንኳን ያለበትን ሁኔታ ብንመለከት በንብረትና በሰው ላይ፣ ቢያንስ በአንደኛው ላይ አደጋ ሳይደርስ የዋለበት ቀን የለም ለማለት ይቻላል፡፡ የአደጋ ዜናው በ24 ሰዓት፣ በወርና በዓመት ስሌት ሲነገር ስንሰማው እጅግ አሳሳቢ ነገር ነው፡፡ በትርፊክ ፖሊስ የዘወትር ሪፖርት እንደምንሰማውም ብዙውን ጊዜ አደጋው የደረሰው ለእግረኛ ቅድሚያ መከልከል በአሽከርካሪ ጥፋት መሆኑን መዘገቡ የተለመደ ነው፡፡
መጠይቅ ደግ ነው፡፡ የአስፈጻሚ አካላት ሥልጣንና ተግባራትን ለመደንገግ የወጣው አዋጅ ቁጥር 691/2003 አንቀጽ 16(6) ፍትሕ ሚኒስቴር በቂ ምክንያት ሲኖር በሕግ መሠረት ሂደት ላይ ያለን ክስ ያነሳል በሚል ይደነግጋል፡፡ ፍትሕ ሚኒስቴር የተሰጠው ክስ የማንሳት ሥልጣን እስከምን ድረስ ነው? ክስ ማንሳት በማንኛውም ጊዜ ይቻላል? ክሱን ሲያነሳስ በቂ ምክንያቱን ለፍርድ ቤቱ ያቀርባል? በቂ ምክንያትስ የምንለው ምንድን ነው? የክስ መነሳትስ ተከሳሾች ላይ ያለው ውጤት ምንድን ነው? በዚህ ሂደት የፍርድ ቤቶች ሚና ምን መሆን ይገባዋል? የሚለው ጥያቄ ሊመለስ የሚገባው ነው፡፡
የቅርብ ጓደኛው ጋር ተጠግቶ ይኖር የነበረ ግለሰብ፣ ጓደኛው በሌለበት አሳቻ ሰዓት 10000 ብር የሚገመት ቶሺባ ላፕቶፕ ወስዶ ለግል ጥቅሙ አውሏል በሚል የወንጀል ሕግ አንቀጽ 665(1)በመተላለፍ በስረቆት ወንጀል ተከሶ፣ ክሱን በዝርዝር በማመኑ ጥፋተኛ ይባላል::
It is an inevitable fact today that one criminal act can inflict upon several victims harm of a certain nature. In doing so, the criminal act flowing from the same criminal intention or negligence and violating the same criminal provision may cause the same harm against the rights or interests of more than one person. In such instances the law dictates the liability to be equalled with the numbers of victims though the practice shows divergence among courts and prosecutors.
በአሁኑ ወቅት በስፋት ተቀባይነት ካገኙ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች በወንጀል ተከሰው ለጠበቃ የመክፈል አቅም ለሌላቸው ሰዎች የሕግ ድጋፍ መስጠት አንዱ ነው። በመሆኑም ተከላካይ ጠበቃ የማግኘት መብት የተከሰሱ ሰዎች ካሏቸው ሕገ-መንግስታዊ መብቶች ቀዳሚው ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ለምን ቢሉ በዓለማቀፋዊም ይሁን በአሕጉራዊ ስምምነቶች እንዲሁም በዝርዝር ብሄራዊ ሕጎች እውቅና የተሰጣቸውና ጥበቃ የሚደረግላቸው የተከሰሱ ሰዎች መብቶች የሚከበሩበት በመሆኑ ነው።
Staling public money hurts the poor disproportionately by diverting funds intended for development, undermining a Government’s ability to provide basic services, feeding inequality and injustice, discouraging foreign aid and investment, fundamentally distorts public policy and leads to the misallocation of resources. What makes things worse is that the offence is usually committed by political parties. Political parties are often seen as actors who abuse their powerful position to extort bribes, to supply members and followers with lucrative positions in the public sector, or to channel public resources into the hands of party leaders or supporters. In this regard, the 2016 Republican Presidential candidate Dr. Ben Carson once made a statement, “We have been conditioned to think that only politicians can solve our problems. But at some point, maybe we will wake up and recognize that it was politicians who created our problems.”
በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር ሥርአት ውስጥ የወንጀል ምርመራ አላማ ስለ ወንጀል የማወቅ፣ ወንጀል እንዳይፈፀም የማስቆም፣ ወንጀሉ ከተፈፀመ ጉዳቶችን የመቀነስ፣ የወንጀል ኢላማ የሆኑትን ሰዎች፣ ንብረቶች ወይም ጥቅሞችን የመከላከል፣ ወንጀል ፈፃሚዎችን ለሕግ የማቅረብ ወይም የወንጀል ተጎጂዎችን መብቶችና ጥቅሞችን ማስከበር እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጀል ፍትሕ ፖሊሲ ይገልፃል፡፡
A Review of Williams and Beare in their article ‘The Business of Bribery: Globalisation, Economic Liberalisation, and the ‘Problem’ of Corruption’, present both sides of the story.
በልደታ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሺሻ በማስጨስ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ግለሰቦች እና የማስጨሻ ቤቶች መኖራቸውን የተረዳው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በሥሩ የሚገኙ የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች የሺሻ ማስጨሻ ዕቃዎችን እና ሺሻ ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ ሺሻን ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦች ላይም የወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው ሲሆን በምርመራ መዛግብቱ ላይ በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በኩል ተገቢውን የሕግ አስተያየትና ውሳኔ መስጠት ይጠበቃል፡፡ ሆኖም ጉዳዩ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ፍርድ ቤቶችና በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ሲታይ ያልነበረ በአንፃሩ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶችና በከተማ ነክ ፍትሕ ጽ/ቤቶች የአቤቱታ ምርመራና የክስ አቀራረብ ንዑስ የሥራ ሂደት ሲታዩ የነበረና ሺሻን አስመልክቶ በቂ መረጃና የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በተጣሩት የምርመራ መዛግብት ላይ ተገቢውን የሕግ አስተያየት እና ውሳኔ ለመስጠት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጣልያንን ለዘጠኝ ዓመታት የመሩት የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንትና ባለቤት እንዲሁም ቢሊየነሩ ሲልቪዮ ቤርሎስኮኒ በተከሰሱበት የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሚላን ከተማ የሚገኘው ፍርድ ቤት ቤርሎስኮኒ የአራት ዓመታት እስራት ቢፈረድባቸውም የእስራት ቅጣቱ በተለያዩ ምክንያቶች ቀርቶ በተቃራኒው ቤርሎስኮኒ በአረጋውያን ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ እ.ኤ.አ. በ2013 መወሰኑ ይታወቃል፡፡ በውሳኔው መሠረትም ቤርሎስኮኒ ሴሴኖ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና ከ2000 በላይ በእድሜያቸው የገፉ፣ የአእምሮና የአካል ጉዳተኛ የሆኑ አረጋውያን በሚገኙበት ማዕከል ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በሳምንት ለአራት ሠዓታት በማዕከሉ እየተገኙ አረጋውያኑን እንዲመግቡ፣ እንዲንከባከቡ፣ እንዲያንሸራሽሩ እንደ አጠቃላይም በማንኛውም መልኩ ከአረጋውያኑ ጎን እንዲሆኑ ተወስኖባቸው ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱን ፈፅመው አጠናቀዋል፡፡