Immediate appeal in Ethiopian Arbitration Law?

An interesting article, published on Jimma University Journal of Law, entitled “the immediate appealability of a court order against arbitration: it should be allowed and even made compulsory”, argues that an immediate appeal against a court order which is against arbitration must be allowed; article 320/3/ of the Civil Procedure Code should be amended to take the special nature of arbitration into account.

  15789 Hits

በወንጀል ጉዳይ በዋስትና እንዲፈታ ፍርድ ቤት ያዘዘውን ሰው ፖሊስ ይግባኝ ልል ነው በማለት ግለሰቡን ያለመፍታት የህግ ስልጣን አለው?

የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 19 (6) ስለተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት እንዳላቸው ሆኖም በህግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ እንደሚችል በግልፅ ተመልክቷል፡፡ ከዚህ ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ መረዳት የሚቻለው የዋስትና መብት መርህ (Principle) ሲሆን በዋስ አለመፈታት ደግሞ ልዩ ሁኔታ (Exception) መሆኑን ነው፡፡ ይህንን ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ ለማስፈፀም ተግባር ላይ ያለው የወ/መ/ስ/ስ/ህግ ምዕራፍ 3 ላይ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ስለመልቀቅ የሚል ርዕስ ያለው ሲሆን በቁጥር 63 ላይ የዋስትና ወረቀት የሚያሰጡ መሰረታዊ ፍሬነገሮችን ይዘረዝራል፡፡ እነዚህ ፍሬነገሮች ዋስትና የሚያሰጡ ሁኔታዎችን የሚያስረዱ ቢሆንም በተቃራኒው በህግ አተረጓጎም መሰረት ዋስትና የሚያስከለክሉ ሁኔታዎችንም በውስጡ አካቶ ይዟል፡፡

  4659 Hits