ጸሐፊዋ በሕግ ጉዳዮች የዘጠኝ ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው ሲሆን በአሁን ሰዓት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዳኝነት እየሠሩ ይገኛሉ። ጸሐፊዋ ከጂማ ዩኒቨርሲቲ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን በ2004 ዓ.ም ያገኙ ሲሆን አሁን 2ኛ ዲግሪያቸውን በኮንስትራክሽን ሕግ እያጠኑ ይገኛሉ።

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን - የሴቶች ጥቃት ችግር - ሴቶች

እንኳን ለአለማቀፍ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ። ዛሬ የመጣሁበት ዋነኛ ምክንያት ከዚህ ቀን ማለትም ከአለማቀፍ ሴቶች ቀን እና አለማቀፍ ነጭ ሪቫን ቀን አከባበር ጋር በተያያዘ ሁል ግዜም በአይምሮዬ የሚመላለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ እነሱን ለማንሳት እና ከጉዳዩም ጋር ተያይዞ ከስራ እና በሕይወት የተረዳኋቸውን አንዳንድ ነጥቦች ለማካፈል ነው።

  4399 Hits

ተገዶ የመያዝን ሕጋዊነት ለማጣራት የሚቀርብ ክስ (Habeas corpus) እና የፍትሐብሔር እንድምታው

የአካል ነጻነት መብት በኢፌዲሪ ህገ መንግስት እውቅና ከተሰጣቸው የሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ እና ዋነኛው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይኸውም የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 17 ድንጋጌ በግልጽ ማንም ሰው በህግ ከተደነገገው ስርአት ውጪ ሊያዝ እንዲሁም ክስ ሳይቀርብበት እና ሳይፈረድበት ሊታሰር የማይችል ስለመሆኑ ያስቀምጣል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት በዚሁ ሕገ መንግስት መሰረት የሀገሪቱ የህግ አካል የሆኑ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ስምምነነት ሰነዶችም ቢሆን እውቅና ከተሰጧቸው የሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ ስለመሆኑ እሙን ነው፡፡ 

  8121 Hits