In recent years, crypto-currencies have gained popularity across the globe, including in Ethiopia. People use them for various purposes — sending money as gifts, purchasing goods and services, or more commonly, as speculative investments hoping for financial returns. However, while crypto might seem like the future of finance, it comes with real risks — especially for consumers.
Introduction
In January 2018, African states gathered in Addis Ababa to adopt the Protocol to the African Charter on Human and Peoples' Rights on the Rights of Persons with Disabilities in Africa (African Disability Rights Protocol). This groundbreaking instrument aims to protect and promote the human rights of persons with disabilities (PWDs) across the continent, aligning with—yet going beyond—the scope of the UN Convention on the Rights of Persons with Disabilities (CRPD).
Although the Protocol came into force on June 5, 2024, Ethiopia has yet to sign or ratify it. This article reflects on the key potential benefits of ratifying the Protocol for Ethiopia and its disability community.
ማስታዎሻ፡- ውደ አንባቢያን ይህ ጽሑፍ የተወሰደው በፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ የመጀመሪያ ደረጃ መቃዎሚያዎች በሚል ከታተመው በ2017 ዓ.ም ተሻሻሎ በቀረበው መጽሐፌ ላይ ሲሆን የግርጌ ማስታዎሻዎቹ እና ማጣቀሻዎቹ ለዚህ ጽሑፍ ሲባል ለንባብ በሚመች አግባብ እንደገና ተቀናጅተው ተሰርተዋል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የተካተቱት አብዛኛዎቹ ነጥቦች አወዛጋቢ ሆኖም በሕግ ባለሙያው ብዥታ እና ልዩነት የሚፈጥሩ ነጥቦች በመጽሐፉ የመጀመሪያ ዕትም ያልነበሩ አሁን ላይ በችሎት በሚገጥሙ ክርክሮች ሰበር ጭምር መፍትሔ የሰጣቸውን እና ሰበር መፍትሔ ያልሰጠባቸውን ደግሞ የመጽሐፉ አዘጋጅም የራሱን ምልከታ እና መፍትሔ የሚላቸውን ሃሳቦች ያሰቀመጠባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡
"In Claris non fit interpretation." (When the text is clear, no interpretation is needed.")
መግቢያ
በዚህ አጭር መነሻ የሆነ የሕግ ማስታወሻ ላይ በተሻሻለው የጸረ ሙስና ልዩ የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ አዋጅን ለማሻሻል የወጣው አዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ 3(1) ድንጋጌ ዙርያ የቀረበ ሲሆን፤ በተለይም በዚህ ድንጋጌ ስር ስለተመለከተው የዋስትና መብት እና የዋስትና ክልከላ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ያልተያዙ ሰዎችና የተያዙ ሰዎች ላይ የሚተገበርበትን ሁኔታ የመጀመሪያ ምልከታ ለማድረግ ተሞክሯል። ይህንን የሕግ ማስታወሻ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ዋና ጉዳይ አንድ ደንበኛዬ የሆነ ሰው በሙስና ወንጀል ክስ የቀረበበት መሆኑን ከሌላ ሰው ከሰማ በኋላ ጉዳዩን አጣርቶ የሙስና ወንጀል ክሱ የቀረበበት የሙስና ወንጀል ችሎት ዘንድ ባልተያዘበት ሁኔታ በገዛ ፍቃዱ በቀረበ ጊዜ ችሎቱ የአዋጅ ቁጥር 882/2007 አንቀጽ 3(1) ድንጋጌን መሠረት በማድረግ በቂሊንጦ ማረፍያ ቤት ሆኖ ጉዳዩን እንዲከታተል ሲል በቅርቡ የሰጠው ትእዛዝ ነው።
አዋጅ ቁጥር 1237/2013 የግልግል ዳኝነትና የእርቅ አሠራር አዋጅ የሚል ርዕስ ተሰጥቶታል፡፡ የአዋጁን ሰፊ ድርሻ የሚወስደው በግልግል ዳኝነት ሂደት ላይ ስላሉ ነገሮች ድንጋጌዎችን በማውጣት ነው፡፡ ቀሪው ደግሞ ስለ ዕርቅ /conciliation/ ይናገራል፡፡ የዚህ ጽሑፍ ዓላማ በግልግል ዳኝነት ሂደት ስለሚሰጡ የዕግድ ትእዛዞች በተለይ አፈጻጸማቸውን ከአዋጁ አንጻር መመልከት ነው፡፡
ይህ ጽሑፍ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከውርስ ሕጉ አጠቃላይ አወቃቀር እና አደረጃጀት ወጥተው በአንደኛው የውርስ ሕግ ክፍል የተደነገገን ድንጋጌ አግባብነት ለሌለው ሌላ የውርስ ሕግ ክፍል ተግባራዊ በማድረግ አንዳንዴም በጉዳዩ ላይ ተፈጻሚነት ያላቸዉን የውርስ ሕግ ድንጋጌዎች በመተዉ አጠቃላይ የዉል ሕግ ድንጋጌዎችን መሠረት በማድረግ ገዥ ትርጉም መስጠታቸውን እና ይህም ሕጉን የተከተለ አለመሆኑን ይከራከራል፡፡ እንዲሁም በዚህ ምክንየት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በራሱ ተቃራኒ እና ምክንየታዊ ያልሆኑ ውሳኔዎች እየተሰጡ መሆኑን በማሳየት የውርስ ሕጉ ሊተረጎም እና ተግባራዊ ሊሆን የሚችልበትን መንገድ ይጠቁማል፡፡
በሀገራችን የፍትሕ ሥርዓት ውስጥ ራሳቸውን በተለየ መልኩ የፍትሕ አካላት በማለት በየዓመቱ ሚያዝያ/ግንቦት ወር የፍትሕ ሣምንት የሚያከብሩ የፖሊስ፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ ዐቃቤ ሕግ እና ፍ/ቤቶችን እንመለከታለን፡፡ በየዓመቱም በአዲስ አበባ ከተማችን በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ቅጥር ገቢ ድንኳን እየተተከለ ሥራዎቻቸውን በፎቶ ግራፎች፣ በጽሑፎችና በውይይት በተደገፈ ለሕዝብ በተለይም ለፍ/ቤቱ ባለጉዳዮች ያስጎበኛሉ፡፡ ነገር ግን ፍትሕ ተቋሞቻችን በመሠረታዊነት ከሚመዘኑበት የሥራዎቻቸው ቅልጥፍና፣ ውጤታማነትና ተገማችነት ባሻገር በአካል ለሚመለከታቸው ህንፃዎቻቸው፣ ግቢያቸው፣ የችሎት አዳራሾቻቸው/ክፍሎቻቸው፣ ቢሮዎቻቸው፣ መጸዳጃ ቤቶቻቸው ቢጎበኙ በተለይም ለጤና ተስማሚነታቸው ምን ይመስላሉ? የሚለው ጉዳይ ለዚህ ጽሁፍ ዐብይ መነሻ ምክንያት ነው፡፡
የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 27 ስር ያለ ማስጠንቀቂያ የስራ ውል የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች ተጠቅሰዋል፡፡ በዚህም ጽሁፍ በአንቀጽ 27 ስር ከተመለከተቱት ዝርዝር ሁኔታዎች የተወሰኑት በመጥቀስ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ጋር በማገናዘብ አጭር ዳሰሳ ለማደረግ ተሞክሯል፡፡
በአንድ አገር የገበያ ሥርዓት ውስጥ ክፍያ የሚካሄድበት ደንብ አለ፡፡ የክፍያ ሥርዓቱም በዓይነት፣ በጥሬ ገንዘብ፣ በሰነድ ወይም በኤሌክትሮኒክስ ሊሆን ይችላል፡፡ በዓይነት ወይም በጥሬ ገንዘብ የሚደረጉ ግብይቶች በአብዛኛው ተጨማሪ ወጭ የሚጠይቁ፣ ለአያያዝ የማይመቹ እና የደህንነት ሥጋት ያለባቸው የክፍያ መፈፀሚያ ዓይነቶች ናቸው፡፡ እነዚህን ሥጋቶች ለመቅረፍ እና የክፍያ ሥርዓቱን የበለጠ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ለማድረግ ክፍያ በቀላሉ ሊፈፀምባቸው የሚችሉ ተላላፊ የንግድ ሰነዶች ተፈጥረዋል፡፡ በኢትዮጵያ የንግድ ህግ አራተኛ መፅሃፍ ሥርም ከአንቀጽ 715-895 ስለ ተላላፊ የገንዘብ ሰነዶች ዓይነት፣ አጠቃቀም እና ኃላፊነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ በንግድ ህጋችን እውቅና የተሰጣቸው ተላላፊ የሆኑ የክፍያ መፈፀሚያ ሥርዓቶች አራት ናቸው፡፡
Several individuals or groups known as parties to the crime may play a distinct role in committing international crimes. The involvement of some of them in the commission of the crime is so close, direct, and active. These persons impose greater danger to society as a whole. The participation of others in the commission of international crime may be indirect by incitement and conspiracy. It supports and legitimizes acts of violence and Persecutory measures against victims. A review of mass crimes, both from the past and the present reveals that incitement and conspiracy generally precede and accompany mass crimes such as genocide, persecution, and extermination.