Labor is the most important activates of a human being crate both material productivity and social values. Now a day it is not a point of disagreement that the development of any given country is highly dependent upon high level of labor productivity, quality and efficiency. This being said, legally speaking labor right is one of the most fundamental human rights recognizing under various international instrument to which Ethiopia is a party. Furthermore, labor right is one of rights which patronizing to constitutional protection. The draft labor proclamation brought untold roaring from Ethiopia Workers Confederation Union (EWCU) and others stakeholders. This mini-article is meant to summarized and explore the draft labor proclamation.
ሀገሮች የዜጎቻቸውን የንብረት፣ የህይወት በአጠቃላይ የስብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ የተለያየ ሕጎችን ያወጣሉ፡፡ እነዚህም ሕጎች ከሕገ-መንግስቱ (የየሃገሩ የበላይ ህግ) ጨምሮ አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ በእነዚህ ሕጎች የተደነገጉት መብቶችን ማራመድ አንዳንድ ጊዜ የሌላውን ሰው መብትና ደህንነት አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል፡፡ በእንደዚህ ሁኔታ ላይ ሲሆን ሕግ እነዚህ መብቶች ላይ ገደብ (limitation) ያስቀምጣል፡፡ ይህ የመብት ገደብ ዘለቄታና በቋሚነት የሚፀና ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል በሕገ- መንግስታችን አንቀፅ 29 ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ተደንግጓል ፡፡ ነገር ግን በተመሳሳይ አንቀፅ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ወጣት ዜጎችን እና የሌሎች ሰዎች መብትና ክብር ለመጠበቅ ሲባል በህግ ሊገደብ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡ ይህ የመብት ገደብ ሲሆን ተፈፃሚነቱም በዘለቄታዊነት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመብት ገደብ ነገሮች ተፈጥሮዊና በተለመደው ሥርዓት ላይ እያሉ የሚተገበር ነው፡፡
Taxation is as old as history of early state formation. As tax remains essential source of public finance, states used to collect taxes for public funding. Apart from its extant condemnation by modern governments, one can strongly argue that tax evasion remains persistent challenge from the very inception of state. Nowadays, following the advancement of public finance the concept of tax evasion get emphasis by tax scholars. It is now condemned and categorized as anti-social behaviors as well as criminal act.
The case involves the failure to comply with the formality requirements more specifically the failure of witnesses and parties to the contract to put signature on insurance policy as ground for non-existence of contract of insurance. Asosa Zonal court upheld that there is no insurance contract because signature is missed. The Higher Court confirms the decision of the Zonal court. Then Ethiopia Insurance Company appeal against this judgment by alleging that there is fundamental error of law.
የዚህ ጽሑፍ መነሻ የቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ መከልከል ሲሆን ጽሑፉ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት በማንኛውም ምክንያት መሰብሰብ አድማሱ እስከምን ነው? የሚለውን መሠረታዊ ነጥብ የሚዳስስ ሲሆን የአልበም ምርቃቱን መከልከል ምክንያቶች በተመለከተ ግን ጸሐፊው በሁለቱም ወገኖች በኩል ያለውን እውነት በማስረጃ ባለማረጋገጡ አቋም ከመያዝ ተቆጥቧል፡፡ ይሁን እንጂ አጋጣሚው በአስፈፃሚውም ይሁን በስብሰባ አዝጋጆቹ ብሎም በማህበረስቡ ላይ ያለውን መደናገር የመሰብሰብ መብትን አድማስ ለማብራራት ምቹ በመሆኑ ጸሐፊው በርግጥ ለቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ ፈቃድ ያስፈልግ ነበር? ፈቃድ ካስፈለገውስ መከልከል ይቻል ነበር? የመከልከል ተግባሩ የሚጥሳቸው መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችና መብቶችስ ምንምን ናቸው? ለሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ይሞክራል፡፡
በክፍል 1 ላይ ጸሐፊው ስለ አጠቃላይ የዋስትና የሕግ ማዕቀፍ በአጭሩ ለማቅረብ ሞክሯል፡፡ በዚህ ክፍል ደግሞ ስለ ኮንስትራክሽን ዋስትና ምንነት፣ ዓይነቶች እንዲሁም በተግባር የሚታዩ ክፍተቶች ይዳስሳል፡፡
1. የኮንስትራክሽን ዋስትና (Construction security)
በኮንስትራክሽን ውል አፈጻጸም ወቅት በርካታ የዋስትና ዓይነቶች ሲተገበሩ ይታያል፡፡ ከቅድመ ግንባታ ጀምሮ በግንባታ ወቅት አንዳንዴም ከግንባታ በኋላ ለሚከሰቱ ችግሮች ዋስትና ጥቅም ላይ ሲውል ይሰተዋላል፡፡ በተለይም የህንጻ አሰሪዎች (Clients) ግንባታው በፈለጉት ጊዜና ዕቅድ መሰረት እንዲካናወንላቸው ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የተነሳ ውሉ እንዲፈጸምላቸው አሰፈላጊ ከለላ እንዲኖራቸው ይሻሉ፡፡
ይህ ጹሑፍ በ6ኛው የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንቨስትመንት ፎረም ላይ “የኮንስትራክሽን ዋስትና ሕጎች እና የገንዘብ ተቋማት አሰራር” በሚል አውደ ጥናት ላይ ለውይይት የቀረበ ነው፡፡ ዋስትና በውል አፈጻጸም ወቅት እንደተጨማሪ ግዴታ የሚቆጠር በሕግ ፊት ሊጸና የሚችል (juridical act) ተግባር ነው፡፡ በአለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ በአለማችን ከኢኮኖሚያዊ እድገት ጋር ታያይዞ ዋስትና (security) የመጠቀም ልማድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጧል፡፡
ሕግና ኅብረተሰብ ጠንካራ ቁርኝት አላቸው፡፡ ኅብረተሰብ በሌለበት ሕግን ማሰብ፣ ሕግ በሌለበት በሥርዓት የሚኖር ኅብረተሰብን ማሰብ አስቸጋሪ ነው፡፡ ይህ ግንኙነት አንዳንድ ጊዜ በመቀዳደም ሊፈጸም ይችላል፡፡ ሕግ ኅብረተሰብን ዘመናዊ ለማድረግና ለመለወጥ እንደ መሳሪያነት ሊያገለግል ይችላል፡፡ በእንዲህ ዓይነት ጊዜ የሕጉ ዓላማ ኅብረተሰቡ ያልደረሰበትን ለውጥ ማስገኘት ነው፡፡ በተቃራኒው ከኅብረተሰቡ የሚወጡ እሴቶችና ባህሎችን ወደ ሕግ ደረጃ በማሳደግም የኅብረተሰቡን ሕልውና ማስቀጠል ይቻላል፡፡ እነዚህ የተሳሰሩ ግንኙነቶች ኅብረተሰቡ ከሕግ መጠቀም የሚቻልበትን ሁኔታ የሚያሰፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ በሆነ መልኩ ሕጉ ከኅብረተሰቡ ዕድገት ወደ ጓላ ከቀረ ሕጉ ከወረቀት ያለፈ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡ ይህን ችግር በአገራችን የተወሰኑ ሕግጋት እናስተውለዋለን፡፡
በማያ ጋዜጣ ሐምሌ የታተመ በሰሞኑ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የችሎት ውሎዎች በፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ እና በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የጋራ የወንጀል ሕጉን የማስፈጸም ተግባር ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የተለያዩ መንግስታዊ መሥሪያ ቤቶች ዳይሬክተሮችን ጨምሮ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪነት ተይዘው የጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀባቸው የሚገኙት እስከ ሣምንቱ አጋማሽ ድረስ ቁራቸው 45 የደረሱ ተጠርጣሪዎች በእሥር ላይ የሚገኙ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የሕግ እርምጃው ቀጣይነት ያለው መሆኑንም በመንግስት መገናኛ ብዙሃን በኢቢሲ መግለጫ ተነግሯል፡፡ የተጠርጣሪዎችን በእሥር ላይ መዋል ተከትሎ በመንግስትም ሆነ በግል መገናኛ ብዙሃን ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመውታል ተብሎ ስለተጠረጠሩበት ወንጀል ዝርዝር የገንዘቡን መጠን ጨምሮ በስፋት ሲዘገብ እየተመለከትንና በጋዜጦች እያነበብን ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎቹን በሕግ መሠረት በቁጥጥር ሥር አውሎ፣ ክስ አቅርቦ ጥፋተኝነታቸው በማስረጃ የተረጋገጠባቸውን በህጉ መሠረት እንዲቀጡ ማድረግ መሰረታዊ የህግ ዓላማ እንዲሁም አንደኛው የሕግ አስፈጻሚዎች ሥልጣንና ተግባር ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በእሥር ላይ የሚገኙት ተጠርጣሪ እሥረኞችን ሕገመንግሥታዊ መብቶችን የማክበሩ ጉዳይም ከተጠያቂነቱና የወንጀል ህጉን ከማስፈጸሙ እኩል ጎን ለጎን ትኩረትን የሚሻ ነው፡፡ የሰዎች መብቶችና ግዴታዎች ሁል ጊዜ ጎን ለጎን በትይዩ የሚፈጸሙ መሆናቸው መሠረታዊ የህግ መርህ ነው፡፡
በኅብረተሰብ ጤና ዘርፍ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሚባል ለውጥ ካስመዘገቡ አገሮች ተርታ ትመደባለች፡፡ የጤና አገልግሎትን በቀበሌ ደረጃ ለማስፋፋት፣ በተለይም በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የኅብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገና በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተቸረውን የጤና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብር ተግባራዊ በማድረግ፣ የዓለም መንግሥታት ድርጅትን የጤና የሚሊኒየም ግቦችን ለማሳካት ችላለች፡፡ እንደ አብዛኛው ታዳጊ አገሮች ሁሉ ባለፉት ዓመታት የመንግሥት የጤና ፕሮግራሞችና የአጋር ድርጅት ትኩረቶች ውስጥ ወባ፣ ኤችአይቪ/ኤድስና ሳንባ ነቀርሳ የመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች የመከላከልና ቁጥጥር ሥራ፣ እንዲሁም የሕፃናትና እናቶች ጤናን ማሻሻል በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ የአገሪቱ የበሽታዎች ሥርጭት ሁኔታ በለውጥ ሒደት ላይ ያለ ሲሆን፣ በተለይም በከተማዎችና በዙሪያቸው ባሉ ሥፍራዎች በመስፋፋት ላይ የሚገኙት የልብ፣ የመተንፈሻ አካላት፣ ስኳርና ካንሰርን የመሳሰሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ይጠቀሳሉ፡፡