በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

Continue reading
  13344 Hits

የውርስ ጉዳይን የተመለከቱ የይርጋ ገደቦች

መግቢያ

ማንኛውም ሰው አንድ የፍርድ ውሰኔ ሊያገኝ የሚገባ ጉዳይ ያለው እንደሆነ ጉዳዩን ለማየት በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ሊያቀርብ ሚችልበት የጊዜ ገደብ በልዩ ልዩ የሕግ ድንጋጌዎች ላይ ተመልክቶ ይገኛል፡፡ ይህን መሰል የጊዜ ገደብ በሕግ አጠራር ይርጋ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ትርጓሜውም በሕግ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ባለመብት የሆነ ወገን መብቱን ለመጠየቅ ተገቢውን ትጋት ማድረግና የመብት ጥያቄውን ማቅረብ ያለበት ሲሆን ይሄን ሳያደርግ ቢቀር ግን መብቱ በይርጋ (በጊዜ ገደብ) ቀሪ የሚሆን ይሆናል የሚል ነው፡፡

Continue reading
  20926 Hits

የሽያጭ ውልን የተመለከቱ አንዳንድ ነጥቦች ከሰበር ውሳኔ ጋር ተገናዝቦ የቀረበ

 

መግቢያ

በዚህ ጽሑፍ የሽያጭ ውል ምንነት፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ስላለው መብትና ገዥው ስለሚኖርበት ግዴታ፣ የሽያጭ ውልን መሰረት አድርገው የሚቀርቡ ክርክሮች ይዘታቸው እና  የይርጋ ገደባቸው ምን እንደሚመስል እንዲሁም የማይንቀሳቀስ ንብረት የገዛ ሰው ንብረቱን ሊለቅ የሚችልባቸው የሕግ አግባብ ምን ምን እንደሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ እና ከሰበር ውሳኔዎች አንጻር ዳሰሳ ለማድረግ ተሞክሯል፡፡   

Continue reading
  6964 Hits

እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል?  

 

ጥያቄው?

በዚህ ጽሁፍ መመለስ የምፈልገው ጥያቄ ቀላል ይመስላል፤ እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል የሚለውን ነው፡፡ ቀጥታ ጥያቄውን ወደ መመለሱ ከመሄዴ በፊት፤ ጥያቄው የሚመለከታቸው ሁኔታዎች ምን አይነቶቹን እንደሆነ ግልጽ ላድርግ፡፡

ያለ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ሲባል?

እንደሚታወቀው ንብረትን (የማይንቀሳቀስም ይሁን ልዩ ወይም ተራ የማይንቀሳቀስ) ለሌላ ሰው ውልን መሰረት አድርጎ ለማስተላለፍ የባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሰጥቷል ነገር ግን ፈቃዱ ሙሉ እና ነጻ አልነበረም የሚባለው የባለቤቱ ፈቃድ በስህተት ወይም በማታለል ወይም በሃይል ተግባር ምክኒያት የተሰጠና በሕጉም መሰረት ውሉ ፈራሽ ውል ሲባል ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን የገለጸው ራሱ ወይም በወኪሉ በኩል ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ሁኔታ የባለቤቱ ፈቃድ ጉድለት አለበት፤ ነገር ግን ንብረቱ ተላልፎ ሊሆን ይችላል ወይም የመብት ገደብ ተቋቁሞ ሊሆን ይችላልና እንዴት ባለቤቱ ንብረቱን ማስመለስ ገደቡን ማስነሳት ይችላል የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

ባለቤቱ በምንም አይነት መልኩ ፈቃዱን ሳይገልጽ ከሆነስ?

በሁለተኛ ደረጃ የንብረት ማስመለሱና የመብት ገደቡን የማስመለስ ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው ከመጀመሪያውኑ ባለቤቱ በምንም መልኩ ፈቃዱን ያልገለጸ ከሆነ ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሳይገልጽ እንዴት ንብረት ይተላለፋል ወይም መብት ይገደባል ለሚል ጥያቄ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሁኔታዎች መልስ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

1. አንድ ሰው ህጋዊ ባለቤት ሳይሆን ባለቤት እንደሆነ በማስመሰል ከሌላ ሰው ጋር በመዋዋል ንብረቱን ሊያስተላልፍ ወይም የመብት ገደብ ሊያቋቁም ይችላል፡፡ ንብረቱ ተራ የሚንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ይህን ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ ንበረቱ የማይንቀሳቀስ ወይም ልዩ ተንቀሳቃሽ ቢሆንም ይህን ለማደድረግ ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን ሰነዶችን ፎርጅድ ማድረግ ሊጠይቅ ወይም የሌላ አካል ትብብርን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እነዚህ ሰነዶች ይህ ሰው ባለቤት መሆኑን የሚያሳዩ ወይም ንብረቱን አስመልክቶ በባለቤቱ ስም ውል የመዋዋል ስልጣን አንዳለው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  20708 Hits

ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል?

መግቢያ

ይህ አጭር ጽሁፍ በቅርብ ጊዜ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር መዝገብ ቁጥር 76248 ላይ፤ በኦሮሚያ ጠቅላይና በአዳማ ልዮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተሰርቷል ማለት አይቻልም በሚል፤ በሶስት ዳኞች ጥቅምት 6 2005 የተዘጋን ጉዳይ መሰረት አደርጎ የቀረበ ነዉ፡፡ የምንዳስሰዉ ጥያቄ በጽሁፉ ርእስ ላይ የተመለከተዉን ነዉ፤ ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል? ለጽሁፉ አላማ የተከራካሪ ወገኖችን ስም መጥቀስ አስፈላጊ ስላልሆነ አበዳሪ፤ ከሳሽ፤ ተበዳሪ፤ እና የተበዳሪ ልጅ የሚሉትን እንጠቀማለን፡፡ በአጭሩ ፍርድ ቤቶቹ የወሰኑት ባለእዳዉ ሳይሆን ሌላ ሰዉ (የጽሁፍ ዉክልና ሳይሰጠዉ በፊት) በባለእዳዉ ስም ያደረገዉ የእዳ አከፋፈል እንዳልተደረገ ስለሚቆጠር ይርጋን አያቋርጥም በማለት ወስነዋል፡፡

የጉዳዩ መነሻ

ተበዳሪዋ ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ አዳማ ቅርንጫፍ ለንግድ ማስፋፊያ በሚልና ንብረት በማስያዝ በየወሩ ተከፍሎ በአንድ አመት ዉስጥ የሚያልቅ ብድር ወስደዋል፡፡ ነገር ግን አንድም ወር የተስማሙትን ወርሀዊ ክፍያ ሳይፈጽሙ በብድር ዉሉ ላይ የተጠቀሰዉ የእዳ መክፈያ ጊዜ ያልፋል፡፡ የብድር ዉሉ የተፈረመዉ በ25/11/1987 ሲሆን በ24/11/1988 ተከፍሎ ማለቅ ነበረበት፡፡ የተበዳሪዋ ልጅ የመጀመሪያዉን የ28000 ብር ክፍያ በተበዳሪዋ ስም የፈጸሙት በ24/11/1989 ነበር፡፡ ከዛ በመቀጠል በ15/8/1994 በዚሁ ልጅ በተዳሪዋ ስም የ2000 ብር ክፍያ ተፈጽሟል፡፡ ክሱ በቀረበበት ወቅት ከመጀመያዉ ክፍያ ጀምሮ ሲሰላ ከአስር አመት በላይ አልፎታል፡፡ ነገር ግን ከሁለተኛዉ ክፍያ ጀምሮ ከተሰላ አስር አመት አልሞላም፡፡

ተበዳሪዋ ለቀረበባቸዉ ክስ የይርጋ መቃወሚያ አንስተዋል፤ ክሱ በአስር አመት የይርጋ ጊዜ ዉስጥ ስላልቀረበ ይታገዳል በሚል፡፡ ሁለተኛዉን ክፍያ በተመለከተ፤ አልከፈልኩም በክፍያ ሰነዱም ላይ ያለዉ ፊርማ የኔ ፊርማ አይደለም ብለዋል፡፡ ይህንን እኔ ያልከፈልኩትን የሁለተኛ ክፍያ ሰነድ ያቀረበዉ ከሳሽ በይርጋ ቀሪ የሆነዉን የብድር ገንዘብ በፍርድ ቤት ክስ መስርቶ ለማስመለስ እንዲያመቸዉ ነዉ የሚል ነዉ፡፡  

Continue reading
  10826 Hits

የተሻሻለው የአማራ ክልል የገጠር መሬት አዋጅ እና አከራካሪው የይርጋ ድንጋጌ

የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 133/98 የተካው የተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 ቀደም ሲል በሕግ ደረጃ ሽፋን ያላገኙ አዲስ ነገሮችን ይዞ እንደወጣ ይታወቃል፡፡ አዲስ ከሚባሉ ነገሮች አንዱ በገጠር መሬት ላይ በሚነሱ ክርክሮች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚ ሊሆን እንደማይችል ያስቀመጠው ነገር ነው፡፡ ይህ የይርጋ ድንጋጌ በሕጉ የተካተተ አዲስ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ገና ከጅምሩ አከራካሪ ጉዳይ እየሆነ መጥቷል፡፡ አከራካሪነቱም በባለሙያዎች መካከል ሁለት ጫፍ የያዙ አቋም እንዲኖር ከማድረግ አልፎ አዲስ የክርክር ምክንያትም እየሆነ ነው፡፡ አዋጁ ስራ ላይ ከዋለ ጀምሮም የገጠር መሬትን ተከትሎ የሚቀርቡ ክሶች ላይ የይርጋ መቃወሚያ ተፈፃሚነት የለውም በሚል  ብዙ ዶሴዎች ከተዳፈኑበት አቧራቸውን እያራገፉ በክስ መልክ  እየቀረቡ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በባለሙያዎች መካከል በይርጋው ተፈፃሚነት ላይ  ባለ ሁለት ጫፍ የያዘ አቋም ምክንያት ከወዲሁ ተገማችነታቸውና ወጥነታቸው አደጋ ላይ እየወደቀ ነው፡፡ ስለዚህም በጉዳዩ ዙሪያ  የሚነሱ አቋሞችን እና ምክንያቶችን በማየት ሃሳቡን መመልከቱ አስፈላጊ እና ትኩረት የሚያስፈልገው ነው፡፡ የፁሁፉ ዋና ትኩረትም በተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ላይ የተቀመጠጠው የይርጋ ድንጋጌ ወሰን አለው ወይስ የለውም የሚል ይሆናል፡፡

በቅድሚያ የተሻሻለው የገጠር መሬት አዋጅ ቁጥር 252/2009 አንቀፅ 55 ስለይርጋ ያስቀመጠውን የድንጋጌውን ሙሉ ይዘት መመልከት ተገቢ ነው፡፡

አንቀፅ 55 ስለይርጋ

የገጠር መሬትን በወረራ ወይም በሌላ በማናቸውም ህገ ወጥ መንገድ ይዞ በመገልገል ላይ የሚገኝ ማንኛውም ሰው መሬቱን እንዲለቅ በማንኛውም ሌላ ሰው ወይም ሥልጣን ባለው የመንግሥት አስተዳደር አካል ሲጠየቅ ወይም በመደበኛ ፍርድ ቤት ሲከሰስ የይርጋ ጊዜ ገደብን በሥነ ስርዓት መቃወሚያነት ሊያነሳ አይችልም፡፡

የድንጋጌው ይዘት በተጠቀሰው መልኩ የቀረበ ሲሆን አንደኛው አቋም ይህ የይርጋ ድንጋጌ  በማንኛውም ከገጠር መሬት ላይ የሚነሳ ክርክርን የይርጋ መቃወሚያ እንዳይቀርበበት እና ይርጋን መቃወሚያ ማድረግ እንደማይቻል ተደርጎ እንደተደነገገ የሚገልፅ ነው፡፡ እንደዚህ አቋም አራማጆች ሕጉ በግልፅ የገጠር መሬትን በወረራ ወይም በማናቸውም ሕገ ወጥ መንገድ የያዘ ሰው የይርጋ መቃወሚያ ሊያነሳ እንደማይችል ስለሚናገር በመሬት ክርክር ይርጋ ተፈፃሚ ሊሆን አይገባም በማለት ይገልፃሉ፡፡  በድንጋጌው “በማናቸውም ሕገ ወጥ መንገድ መያዝ” የሚለው ሃረግ  የሚያመለክተው የገጠር መሬት ሊያዝ ከሚችልባቸው መንገዶች ማለትም (በድልድል፣ በስጦታ፣ በውርስ፣ በኪራይ) ውጪ የገጠር መሬትን ይዞ መገኘት እንደሆነ ተደርጎ የተቀመጠ ነው፡፡ በተሻሻለው አዋጅ አንቀፅ 2(39) በተቀመጠው የትርጓሜ ክፍል “ህገ ወጥ ይዞታ” ማለት ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የተያዘና አግባብ ባለው አካል እውቅና ያልተሰጠው ማናቸውም የገጠር መሬት ይዞታ ስለመሆኑ ይናገራል፡፡  ይሕ የትርጓሜ ክፍል በሕጉ መሬት ከሚገኝባቸው መንገዶች ወይም ሥርዓት ውጪ የሚያዙና አግባብ ባለው አካል እውቅና ያልተሰጠው የገጠር መሬት እንደ ሕገ ወጥ ይዞታ የሚቆጠር ስለሆነ የይርጋው ድንጋጌም ሕገ ወጥ ይዞታ ከሚለው ትርጉም ጋር ተናዝቦ ሊታይ የሚገባ ነው፡፡ በይርጋ ድንጋጌውም የተቀመጠው በማናቸውም መንገድ በሕገ ወጥ መንገድ መያዝ የሚለው በሕግ ከተቀመጠው መሬት ከሚያዝበት ውጪ መያዝ ስለሆነ ከሕግ ውጪ የገጠር መሬትን ይዞ ይርጋን መከራከሪያ ማድረግ አይቻልም፡፡ በማናቸውም ሕገ ወጥ መንገድ የሚለውም ሁሉንም ከሕግ ውጪ የሚያዙበትን መንገዶች ክፍተት እንዳኖራቸው ዝግ አድርጎ ያስቀመጠ ስለሆነ የይርጋ መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፡፡ በተጨማሪም የመሬት ክርክር ይርጋ ሊያግደው እንደማይገባ የፌደሬሽን ምክር ቤት ሳይቀር ውሳኔ የሰጠ ስለሆነ በመሬት ክርክር በሁሉም ጉዳዮች ይርጋ ተፈፃሚነት ሊኖረው አይገባም በማለት መከራከሪያቸውን ያቀርባሉ፡፡

Continue reading
  42928 Hits

አላግባብ/በስህተት የተከፈለን የጡረታ አበል ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የሚያስቀረዉ የይርጋ ዘመን ምን ያህል ነዉ?

መግቢያ

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በሰበር ችሎት ዉሳኔዎች ቅጽ 14 መግቢያ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፤ “ለተመሣሣይ ጉዳዮች በጣም የተራራቁ ዉሣኔዎችን በመስጠት ይታይ የነበረዉን ችግር በመቅረፍና የዉሣኔዎችን ተገማችነት በማረጋገጥ ረገድ የሰበር ዉሣኔዎች አስገዳጅ መሆን ከፍተኛ ዉጤት አስገኝቷል ማለት ይቻላል፡፡ አልፎ አልፎ በዉሣኔዎች ጥራትና ስርጭት ሊታዩ የሚችሉ ችግሮች ሥርዓቱ እየተጠናከረ ሲሄድ የሚፈቱ ሲሆን አነዚህን ችግሮች ለማቃለል እኛም ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ጥረታችን ሊሳካ የሚችለዉ በዉሣኔዎቹ ላይ በሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ገንቢ የሆኑ ትችቶችና አስተያየቶች ሲቀርቡ ነዉ”፡፡ እኔም ይህን ግብዣ በመቀበል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት ሕዳር 21 ቀን 2005 ዓ.ም. በሰጠዉ ዉሳኔ ላይ ትችቴን ከዚህ በመቀጠል አቀርባለሁ፡፡ ዉሳኔዉ የተሰጠዉ በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ እና ታዬ አበራ መካከል ባለዉ ክርክር በሰበር መዝገብ ቁጥር 72341 ነዉ፡፡ በዚህ መዝገብ ከተነሱት ዋነኛ ጉዳዮች ዉስጥ፤ አላግባብ የተከፈለ ጡረታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይ፤ ከታገደስ የይርጋ ዘመኑ ምን ያህል ነዉ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

የጉዳዩ መነሻ

አቶ ታዬ አበራ ከግንቦት 01 ቀን 1984 ዓ.ም. ጀምሮ በየወሩ የጡረታ አበል ይወስዱ ነበር፡፡ ከሰኔ 01 ቀን 1989 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ በመንግስት መስሪያ ቤት ተቀጥረዉ ደመዎዝ ተከፍሏቸዋል፡፡ አቶ ታዬ የጡረታ አበላቸዉን መዉሰዳቸዉንም እንደቀጠሉበት ነዉ፡፡ የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 209/1955 አንቀጽ 30(2) እና በመንግስት ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 345/1995 አንቀጽ 46(1) መሰረት፡ የአገልግሎት የጡረታ አበል በመቀበል ላይ ያለ ባለመብት እንደገና በመንግስት መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ ደመዎዝ ማግኘት ከጀመረ አበሉ ይቋረጣል፡፡ በመሆኑም በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ የተጠየቀዉ ዳኝነት እነዚህን ያጠቃልላል፡፡ 1) ከሰኔ 01 ቀን 1989 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 1995 ዓ.ም. ድረስ በየወሩ ብር 105.00 የወሰዱት ለሰባ አምስት ወራት ያህል ተባዝቶ የሚመጣዉን ዉጤት ብር 7575.00፤ 2) ከሐምሌ 01 ቀን 1996 ዓ.ም. እስከ ሀምሌ 01 ቀን 1998 ድረስ በየወሩ ብር 115.50 የወሰዱት ታስቦ የሚመጣዉን ድምር ብር 4045.50፤ 3) ወጪና ኪሳራ እንዲሁም ከሕጋዊ ወለዱ ጋር እንዲከፍሉ፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ለመጀመሪያ ጊዜ ክስ የተመሰረተዉ በጥቅምት 18 ቀን 2003 ዓ.ም. ነዉ፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዉሳኔ

Continue reading
  10201 Hits

ስለ ይርጋ ጥቂት ነጥቦች

 

 

ይርጋ ምንድን ነው? ይርጋ ዓላማው (ጠቀሜታው) ምንድን ነው? ይርጋ ጉዳቱስ ምንድን ነው? ይርጋ የሚያስጠብቀው የማንን መብት ነው? የይርጋ መሠረታዊ መርሆዎች ምንድን ናቸው? ይርጋን የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች ምን ይመስላሉ? በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ጽሑፍ ይዳሰሳሉ፡፡  

የይርጋ ምንነት

ይርጋ የሚለው ቃል መነሻውረጋከሚለው የአማርኛ ቃል ጋር የተያያዘ ሲሆንረጋየሚለውን ቃል ደራሲ ተሠማ ኃብተ ሚካኤልከሠቴ ብርሀን ተሰማበተሰኘውና 2002 .. በድጋሚ ባሳተሙት የአማርኛ መዝገበ ቃላት ላይየሰው ሀሳቡ ከመውጣት ከመውረድ በሀሳብ ከመዞር ከመባከን ከመናወጥ ጠጥ (ፀጥ) አለበሚል ትርጓሜ ተሠጥቶታል፡፡ ከዚህ በመነሳትም ይርጋ የሚለውን ቃል በአንድ ጉዳይ ላይ ክስ የማቅረብ ወይም መብት የመጠየቅ ጉዳይን አስመልክቶ በጉዳዩ ላይ ክስ የሚያቀርብበት ሰው ስለጉዳዩ ያለውን ሀሳብ ከመውጣት ከመውረድ በሀሳብ ከመዞርና ከመባከን ከመናወጥ ከረጋ (ፀጥ) ካለ በኋላ ሊከሰስ ወይም ሊጠየቅ እንደማይገባ ያመለክታል በሚል ልንወስደው እንችላለን፡፡ በሌሎች ፅሁፎች ላይም ይርጋ ማለት አንድ መብቱ ወይም ጥቅሙ የተነካበት ሰው በሌላ ሰው ላይ ክስ፣ አቤቱታ ወይም የይገባኛል ጥያቄ እንዲያቀርብ በሕግ ተለይቶ የተቀመጠ የክስ (አቤቱታ) ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በሕግ የተቀመጠው የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላም በዚያው ጉዳይ ላይ በጣም በውስንና ጥቂት ምክንያቶች ካልሆነ በስተቀር ክስ የማቅረብ መብት ቀሪ ይሆናል፡፡

Continue reading
  35636 Hits

Period of Limitation, Lapse of a Morgage Vs Art 3058 of the Civil code

In 2002, when I was doing my undergraduate degree, our contract law teacher started talking about period of limitation and its effect. I neither had a concept nor an argument about period of limitation under art 1845 of the civil code. I attended the whole class, tried to understand arguments, justifications and ration d’être of the period of limitation. Mulugeta Mengist, in his monograph says that period of limitation is used to ensure certainty and predictability in transactions.

Now, with some years of working experience and exposure, I feel like I have understood what period of limitation in a private contractual relationship. To restate what Mulugeta wrote unless there is a time limit after the lapse of which the right cannot be enforced, people do not feel secure to do whatever they like with respect to their property.

A limitation period is the period of time within which a party to a contract must bring a claim. Limitation period starts counting when the contract is breached, or when the damage is suffered. Period of limitation is a period of time, the expiry of which extinguishes parties’ legal remedies and also parties’ legal right. This is an absolute defense beneficial to the debtor but the burden of proof of the statute of limitation is with the debtor.

However, one court decision still perplexes me: Development Bank of Ethiopia v. Mr. Tigabu Teferra, Cassation No 78444/2005, found in vol 14. In order to give a glimpse of the case, the respondent, Mr Tigabu, borrowed money from the bank against collateral, in which the immovable property was registered in Megabit 23, 1989 E.C. After 14 years, it renewed the registration of the immovable property in the local registrar office, Merab Wolega Registration Office. The respondent argued that the renewal of the registration is against article 3058(2) of the civil code. On the other hand, the bank said that it had already given notice based on article 3 of proclamation 97/90.

At last, the cassation decided that art 3058(1) & (2) are not concerned with period of limitation but lapse of mortgage. Citing a precedent, Cassation Decision 44800/2002, Vol 10, it concluded that

Continue reading
  9059 Hits