የፍርድ ቤት ወይስ የችሎት ስልጣን? (Jurisdiction of Courts or Divisions)

 

ይህን ለመጻፍ ያስገደዱኝን እና የገጠመኙን ሁኔታዎች በቅድሚያ ላብራራ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ሰራተኛ አሰሪው በነበረው ድርጅት ላይ ህገ-ወጥ የስራ ውል መቋረጥ ተፈጽሞብኛል በማለት ላቀረበው ክስ አሰሪው ድርጅት በተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠኝ ሰራተኛው የስራ ውሉን ስላቋረጠ ካሳ እንዲከፍለኝ የሚልና ሰራተኛው ስራ ላይ በነበረ ጊዜ ለስራው አገልግሎት የተሰጠውን ላፕቶፕ ኮምፒውተር ሳይመልስ በመቅረቱ ንብረቱን እንዲመልስ ወይም የንብረቱን ግምት ብር 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ) እንዲከፍለኝ በማለት ክስ አቀረበ፡፡ ጉዳዩን ሲያይ የነበረው የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የስራ-ክርክር ችሎትም በድርጅቱ የላፕቶፕ ንብረትን በተመለከተ የቀረበውን የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ይህ ችሎት (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የማየት ስልጣን ስለሌለው ጉዳዩን በዚሁ ፍ/ቤት በፍትሐብሄር ችሎት ክስ የማቅረብ መብታቸውን ጠብቄ አቤቱታውን ውድቅ አድርጌዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም ተከራይ ከአከራዩ ድርጅት ሶስት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችን በተለያየ ጊዜ የተከራየ ሲሆን በቅድሚያ ለተከራያቸው ሁለት ክፍሎች የውል ሰነድ ያለው ሲሆን ለሶስተኛው ክፍል ግን ከቃል ስምምነት ባለፈ በጽሁፍ የተደረገ ውል የለም፡፡ ነገር ግን ለሶስተኛው ክፍልም ቢሆን ለአራት ወራት ያህል በየወሩ ከተከራይ የኪራይ ገንዘብ የተቀበለበትን ደረሰኝ በማስረጃ አያይዟል፡፡ ይህንንም የኪራይ ውልና የኪራይ ክፍያ ደረሰኝ መሰረት በማድረግ አከራይ ላልተከፈለው እና ተከራይ ለተገለገለበት ጊዜ የኪራዩ ክፍያ ይከፈለኝ በማለት በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ክስ ያቀረበ ሲሆን ጉዳዩን ሲመረምር የነበረው የፍ/ቤቱ የኪራይ ችሎትም (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የኪራይ ውል ሰነድ ያላቸውን  ክፍሎች አስመልክቶ ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለኝ ሲሆን የኪራይ ውል የሌለውን ሶስተኛውን የቢሮ ኪራይ ክፍያ ክስ በተመለከተ ግን ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለው በዚሁ ፍ/ቤት የንግድና ልዩ ልዩ ችሎት ስለሆነ በዚህ ችሎት ክስ የማቅረብ መብታችሁን ጠብቄ በሶስተኛው ቢሮ ላይ ያቀረባችሁትን ክስ ዘግቼዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

ለመሆኑ በአዎጅ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች እንጂ ችሎቶች ይህን መሰሉ ስልጣን አላቸው? የፍትሐብሔር የሥነ-ሥርዓት ሕጉ ዓላማስ ከዚህ አኳያ እንዴት ይመዘናል የሚለውን በጥቂቱ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡- የፌደራል ፍ/ቤቶችን ያቋቋመው አዎጅ ቀ. 25/88 በፌደራል ደረጃ የሚኖሩት ፍ/ቤቶች የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት፣ ከፍተኛ ፍ/ቤት እና ጠቅላይ ፍ/ቤት መሆናቸውን ሲገልጽ የእነዚህ ፍ/ቤቶችም በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣንም ሆነ በይግባኝ ደረጃ ጉዳዮችን ተቀብለው አይተው እና አከራክረው ወሳኔ ሊሰጡ የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በዝርዝር ደንግጓል፡፡

ይህ አዎጅ ይህንንም ሲገልጽ እነዚህ የፌደራል ፍ/ቤቶች ጉዳየን ለማየት እንዳለቸው ስልጣን የተፋጠነ ፍትህን ለመስጠት እንዲያስችል እያንዳንዱ ፍ/ቤት ቢያንሰ ሶስት ችሎቶች እነዚህም የፍትሐብሄር፣ የወንጀል እና የስራ-ክርክር ችሎቶች ሊኖሩት እንደሚገባ (በፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 25/88 አ.ቁ 20(1) ፣23(1)) ሲደነግግ እንደሚቀርቡለት የጉዳዮች ብዛትና ዓይነት በስሩ እንደ ነገሩ ሁኔታ ሊይዛቸው የሚችሉ ችሎቶችን ፍ/ቤቱ በራሱ አስተዳደራዊ ውሳኔ የማብዛት መብት አለው (በተሻሻለው ፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 454/97 አ.ቁ 23(1))፡፡

Continue reading
  14508 Hits

ሰበር በአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ሥልጣን ላይ ያሰመረው ቀጭን መስመር

 

የአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣናቸውን የተመለከቱ የተለያዩ ክርክሮች ተነስተዋል፡፡ ዋናው ክርክር በተቋቋመበት ወቅት የተነሳው የሕገ መንግሥታዊነት ጭብጥ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 78 እስከ 80 የዳኝነት አካሉን ሲያዋቅር በተለያዩ ደረጃዎች ያሉት የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚቋቋሙ በመግለጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚወሰዱ ጊዜያዊና ልዩ ፍርድ ቤቶች እንደማይቋቋሙ ደንግጓል፡፡

ይህን መሠረት አድርገው አንዳንዶች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የተቋቋመው የከተማ ነክ ፍርድ ቤት (አሁን የከተማ ፍርድ ቤት) ሕገ መንግሥታዊ አይደለም ሲሉ ሞግተዋል፡፡ የፍርድ ቤቱን ሕገ መንግሥታዊነት የሚደግፉ ወገኖች ደግሞ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 49 በአዲስ አበባ የራስ አስተዳደር ስለፈቀደ አዲስ አበባ እንቅስቃሴዎቿን ለመከታተል የሕግ አውጭ፣ የሕግ አስፈጻሚ እንዲሁም የሕግ ተርጓሚ አካላትን ማቋቋም ትችላለች ብለዋል፡፡ የግራ ቀኙን የሕገ መንግሥታዊነት ለመደገፍ ሌሎችም ምክንያቶች ተጠቅሰዋል፡፡ ያም ሆኖ የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት በአዋጅ ተቋቁሞ መደበኛ የፍርድ ቤት ሥራዎችን መሥራት ከጀመረ ሁለት አሠርት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ሥልጣኖች ተሰጥተውታል፡፡ በተቋቋመበት ወቅት በዋናነት የከተማ አስተዳደሩ የሚያከናውናቸው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ የአስተዳደርና የቁጥጥር ሥልጣኖችን ከማስፈጸም ጋር የተያያዙ ክርክሮችን ይመለከት ነበር፡፡ ሁከት ይወገድልኝ፣ ደንብ መተላለፍ፣ ከቀበሌ ቤቶች ጋር የተያያዙ ክርክሮች፣ ከመሬት ጋር የተያያዙ ክርክሮችን ተቀብሎ እንዲያስተናግድ ተፈቀደለት፡፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ ደግሞ ከመሬት ጋር የተያያዙት ጉዳዮች በአስተዳደሩ ስም ለተቋቋመ ቦርድ የተሰጠ ሲሆን፣ በምትኩ ጊዜ ቀጠሮ፣ እስከ አምስት ሺሕ ብር የሚደርሱ የፍትሐ ብሔር ክርክሮች፣ የስም ለውጥ፣ የወራሽነት የምስክር ወረቀት፣ የመጥፋት ውሳኔ፣ የባልና የሚስትነት፣ የሞግዚትነት የምስክር ወረቀት የመስጠት ሥልጣን በተሻሻሉ አዋጆች እንዲሠራ ተደርጓል፡፡

ለፍርድ ቤቱ በተለያዩ ጊዜያት ከተሰጡት ሥልጣኖች ለመረዳት የሚቻለው ፍርድ ቤቱ እንዲሠራቸው የተፈለጉት ክርክሮች ውስብስብነት የሌላቸው፣ በአጭር ጊዜ ሊጠናቀቁ የሚገባቸው፣ የገንዘብ መጠናቸው አነስተኛና ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን (Municipality activities) መሠረት አድርገው የሚነሱ ክርክሮችን ነው፡፡

Continue reading
  11766 Hits

የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ስልጣን ከአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ አንፃር

 

በአሁን ሰዓት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ማለትም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም የከተማ አስተዳደሮች ህጋዊ ጥንስሳቸው የአዲስ አበባ ከተማ ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያለው ሲሆን የድሬዳዋ ከተማ ደግሞ የቻርተር መሰረት ያለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት በኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 49 (1) መሰረት የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ነው በማለት ለከተማው እውቅና ሰጥቷል፡፡ የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 49 (2) የአዲስ አበባ ከተማ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለውም ደንግጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 የድሬዳዋ ከተማን በማቋቋም እራሱን በራሱ እንደሚያስተዳድር ደንግጓል፡፡

ማንኛውም የከተማ አስተዳደር እራሱን በራሱ ሲያስተዳድር በህግ አግባብ የተቋቋሙ ሶስቱ የመንግስት አካላት ማለትም ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈፃሚና ህግ ተርጓሚ አካላት ይኖራቸዋል፡፡ በዚህም አግባብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቻርተር አዋጅ ቁጥር 361/95 እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 መሰረት የራሳቸውን የከተማ ፍርድ ቤቶች አቋቋመው በስራ ላይ ይገኛሉ፡፡ የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ማለት የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ማለት እንደሆነ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2 (10) በግልፅ አመላክቷል፡፡

እነዚህ የከተማ ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በስራ ላይ ሲውል ስልጣንና ሀላፊነታቸውን በማሻሻል ብቅ ብሏል፡፡ እነዚህ የከተማ ፍርድ ቤቶች ምን አይነት አዲስ ስልጣን ተጨመረላቸው?፣ በፍትሐብሄር እና በወንጀል ጉዳዮች ስልጣናቸው እስከምን ድረስ ነው? እና በተጨመረላቸው ስልጣን ምክንያት የስራ ጫና ሊኖር ስለሚችል ምን አይነት ዝግጅት ማድረግና በህዝብና በተገልጋዩ ማህበረሰብ አመኔታ ያላቸው ፍርድ ቤቶች ለመሆን ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል የሚሉትን እንደሚከተለው በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡

 

Continue reading
  10018 Hits