‘ኮማንድ ፖስት’ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተሰጠ ልዋጭ ስም?

በሀገራችን ኢትዮጵያ የፀጥታ ችግር በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች ሲከሰት መንግሥት በሕግ የተቀመጠለትን መደበኛውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጠቀም ፈንታ በስም የተለየ ነገር ግን በአተገባበር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር ተመሳሳይነት ያለውን የሕግ ማስከበር መንገድ ‘ኮማንድ ፖስት’ በሚል ስያሜ እያዘወተረ እየተጠቀመ ይገኛል፡፡ ከዚህም በመነሳት ህብረተሰቡም ይህንኑ ኮማንድ ፖስት የተባለውን ስያሜ እኩል ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር አገናኝቶ ሲጠቀም ይስተዋላል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ኮማንድ ፖስት መንግሥት በመደበኛ የሕግ ማስከበር መንገድ ሕግን ማስከበር ሲቸገር እየተጠቀመው የሚገኝና በተግባርም የግለሰቦችን መብት የሚገድቡ ክልከላዎችን ጭምር በማውጣት በተግባር ተጠያቂ እያደረገ በመስተዋሉ ነው፡፡ ብዙን ጊዜ ይህንን አዋጅ ሲያውጅ የሚስተዋለው በፌደራል ደረጃ የተዋቀረ ‘ብሔራዊ የፀጥታ ም/ቤት’ የሚባል አካል እነደሆነ ይደመጣል፡፡ ይህ አካል አዋጁን ያውጅ ዘንድ በሕገ-መንግሥቱ ሥልጣን የተሰጠው አካል እንዳይደለ መረዳትም ይቻላል፡፡

  10915 Hits

ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት

 . ወደኋላ ሄዶ ተግባራዊ የሚያደርጉ የታክስና ጉምሩክ ሕግ ድንጋጌዎች ሕገ መንግሥታዊነት 

የታክስና የጉምሩክ ሕጎች ስንል ምን ማለታችን ነው? ከሕገ መንግሥቱ ጋር ያላቸው ዝምድናስ ምን ይመስላል ?

በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 አንቀጽ 2(36) መሠረት የታክስ ሕግ ማለት የጉምሩክ ሕግን ሳይጨምር የታክስ አስተዳደር አዋጅ፣ የፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ፣ የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ፣ የቴምብርና የተርን ኦቨር ታክስ አዋጅ፣ ታክስ/ቀረጥ/ክፍያ ለመጣል የሚወጣ ሕግ እንድሁም እነዚህን አዋጆች መሠረት በማድረግ የሚወጡ ደንብና መመሪያዎችን ያካትታል፡፡ የጉምሩክ ሕግ ማለት ደግሞ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/06 አንቀጽ 2(39) መሠረት የጉምሩክ አዋጁን፣ አዋጁን ተከትለው የሚወጡ የጉምሩክ ደንብና መመሪያዎችን እንድሁም የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን /የአሁኑ ገቢዎች ሚኒሰቴር/ የሚያስፈፀማቸውን ሌሎች ሕጎች ያካትታል፡፡

  12648 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

  13931 Hits
Tags:

ጋብቻ ሳይፈፀም እንደባልና ሚስት አብሮ መኖር፤ አንድምታዎቹ እና ተግዳሮቶቹ

በተሻሻለው የኢትዮጲያ የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 1 መሰረት ህጋዊ ጋብቻ በተለያዩ ሰነ-ስረዓቶች ሊፈፀም ይችላል፡፡ እነሱም በክብር መዝገብ ሹም ፊት፣በሐይማኖት እና በባህል መሰረት የሚፈፀሙ የጋብቻ አይነቶች ናቸው፡፡ በተጨማሪም ጋብቻ ከላይ በተጠቀሱት በአንዳቸው ስነ-ስርዓቶች ቢፈፀም እንኳን ውጤቱም አንድ መሆኑን የዚሁ ህግ አንቀፅ 40 ያትታል፡፡ ህጋዊ ጋብቻ በተጋቢዎቹ ላይ ሁለት ዓይነት ውጤት ይኖረዋል፡፡ የመጀመሪያው በተጋቢዎች ግለዊ ግንኙነት ላይ የሚኖረው ውጤት ሲሆን፤ በስሩም የመከባበር ፣ የመተጋገዝና የመደጋገፍ ግዴታ ፣ ቤተሰብን በጋራ የመስተዳደር እና በጋራ አንድ ላይ የመኖር ግዴታዎችን ያቅፋል፡፡ ሁለተኛው ውጤት ደግሞ ጋብቻ በተጋቢዎች ንብረት ላይ የሚኖረው ውጤት ነው፡፡ ይህም ተጋቢዎች  ጋብቻቸውን በሚፈፅሙበት ጊዜ በግል የነበሯቸው ንብረቶች ወይም ከጋብቻ በኋላ በውርስ እና በስጦታ በየግላቸው ያገኙዋቸው ንብረቶች የግል ንበረታቸው ሆነው ሲቀሩ ከዚህ ውጪ ያሉ ንብረቶች በሙሉ የጋራ  ንብረት ይሆናሉ፡፡

  19759 Hits

በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

  15885 Hits

ቀለብ የመስጠጥ ግዴታ ፅንሰ ሀሳብ በተሻሻለው የኢትዮጵያ የቤተሰብ ሕግ

ግዴታ ህጋዊ ግንኙነት ሲሆን መሰረታዊ መርሁም የሚያካተው አንድ ዕዳ ያለበት ሰው ወይም ባለዕዳ ለአበዳሪው ዕዳውን የሚፈጽምበት ሂደት ነው፡፡ በዚህ ግንኙነት ውስጥ ባለዕዳው ለአበዳሪው አንድን ነገር ለማድረግ ፣ ለመስጠት ወይም ላለማድረግና ላለመስጠት የሚያደርገው ህጋዊ ግዴታ ነው፤ በተቃራኒው ደግሞ አበዳሪው ከባለዕዳው የሚገባውን እና በሕግ የተፈቀደለትን ጥቅም የሚያገኝበት ሁነት ነው፡፡ ግዴታዎች ከሁለት ምንጮች ይቀዳሉ፤ የመጀመሪያው ከውል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ከሕግ ነው፡፡ ከውል የሚመነጭ የግዴታ አይነት በተዋዋይ ወገኖች ስምምነት ላይ የሚመሰረት ሲሆን ስምምነቱም በተዋዋይ ወገኖቹ ላይ እንደ ሕግ እንደሚያገለግል የፍትሐብሔር ህጉ አንቀጽ 1731 ያትታል፡፡ ሁለተኛው የግዴታ ምንጭ ደግሞ ከሕግ የሚመዘዝ ነው፤ የዚህ አይነት ግዴታዎች በቀጥታ ከሕግ  የሚመነጩ ሲሆን ግዴታውም በባለዕዳው እና አበዳሪ ሰዎች ሊቀየር ፣ ሊሻሻል እንዲሁም ሊቀር አይችልም፡፡

  16554 Hits

ስምና ድንጋጌዎቹ በኢትዮጵያ የፍትሐብሔር ሕግ

ስም ሰዎችን ለመለየት የምንጠቀምበት ሁነኛ ዘዴ ነው፡፡ ይህም አንድን ሰው ከሌላ ሰው ለመለየት ለሰዎቹ ስያሜ በመስጠት በቀላሉ መለየት ይቻላል፡፡ የአገራችን ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 36 (1) (ለ) ስምን የመሰየም የሁሉም ህጻናት መብት ነው ሲል ያትታል፡፡ በተጨማሪም ICCPR አንቀጽ 24 (2) እንደሚደነግገው ሁሉም ህጻናት እንደተወለዱ ወዲያውኑ እንዲመዘገቡ እና ስም እንዲወጣላቸው ያዛል፡፡

  15233 Hits

የፍርድ አፈፃፀም መሠረታዊ ታሳቢዎችና ያጋጠሙ ችግሮች

አፈፃፀም ፍርድ ቤት የሰጠውን ፍርድ በእራሱ አማካኝነት ወደ ተግባር የሚለውጥበት ሥርዓት ነው፡፡ ስለፍርድ አፈፃፀም የተደነገጉትን ድንጋጌዎች በመከተል ፍርድን በተግባር መተርጎም እንደመሆኑ መጠን የማስፈፀሚያ ሥርዓቱ በጥቅሉ የፍ/ብ/ሥ/ሥ ህጉን መሠረታዊ ዓላማ ተከትሎ በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲፈፀም በሚያስችል አኳኋን የተዋቀረ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተግባር እንደሚታየው ክስ አቅርቦ ለማስፈረድ ከሚወሰደው ውጭ ጊዜና ጉልበት ባልተናነሰ ሁኔታ የተፈረደን ፍርድ ለማስፈፀም የሚጠይቀው ወጭና ጊዜ በልጦ የሚታይበት ጊዜ ይከሰታል፡፡ ምክንያቶቹ በርካታ ናቸው፡፡

  21042 Hits

ችሎት መድፈር በኢትዮጵያ ሕግ: ሕጉና አተገባበር

"ችሎት መድፈር" ወይም Contempt of Court በአብዛኛው ሃገራት የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ግልጋሎት ላይ እየዋሉ ካሉ የሕግ ፅንሰ ሃሳቦች አንዱ ነው። ይህ የሕግ ፅንሰ ሃሳብ በእኛ ሃገር በሰፊው ሥራ ላይ እየዋለ ቢሆንም ከሕጉ መንፈስ ውጭ አተገባበሩ ላይ የሚታየው የሕግ አተረጓጎም ክፍተትና ልዩነት የተለያዩ የዜጎች መብት ጥሰቶችን ሲያስከትል ይታያል። 

  11102 Hits

የፌዴሬሽኑ አባል ክልሎች የፌዴራሉን መንግሥት ሕጎች አልፈፅምም ማለት ይችሉ ይሆን?

የፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 53 መሠረት በተቋቋመ ወዲህ ላለፉት 24 ዓመታት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከ1100 በላይ አዋጆችን ያወጣ ሲሆን ከእነዚህም አዋጆች ውስጥ በምክር ቤቱ በሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባላት መካከል ሞቅ ያሉ ክርክሮችና የልዩነት ሃሳቦች ያስተናገዱ በጣት የሚቆጠሩ አዋጆች መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ሞቅ ያሉ ንትርክ አዘልና የልዩነት ሃሳቦች ከተንፀባረቁባቸው ሕጎች መካከል ለአብነት ያህል በሚንስትሮች ምክር ቤት ከየካቲት 06 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ተፈፃሚነት የነበረውንና ለሁለተኛ ጊዜ በሚኒስትሮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 2/2010 የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቀባይነት እንዲያገኝ በቀረበ ወቅት የተደረገው እልህ አስጨራሽ ክርክር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡

  14263 Hits