ስም ሰዎችን ለመለየት የምንጠቀምበት ሁነኛ ዘዴ ነው፡፡ ይህም አንድን ሰው ከሌላ ሰው ለመለየት ለሰዎቹ ስያሜ በመስጠት በቀላሉ መለየት ይቻላል፡፡ የአገራችን ሕገ መንግሥት በአንቀጽ 36 (1) (ለ) ስምን የመሰየም የሁሉም ህጻናት መብት ነው ሲል ያትታል፡፡ በተጨማሪም ICCPR አንቀጽ 24 (2) እንደሚደነግገው ሁሉም ህጻናት እንደተወለዱ ወዲያውኑ እንዲመዘገቡ እና ስም እንዲወጣላቸው ያዛል፡፡
አፈፃፀም ፍርድ ቤት የሰጠውን ፍርድ በእራሱ አማካኝነት ወደ ተግባር የሚለውጥበት ሥርዓት ነው፡፡ ስለፍርድ አፈፃፀም የተደነገጉትን ድንጋጌዎች በመከተል ፍርድን በተግባር መተርጎም እንደመሆኑ መጠን የማስፈፀሚያ ሥርዓቱ በጥቅሉ የፍ/ብ/ሥ/ሥ ህጉን መሠረታዊ ዓላማ ተከትሎ በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲፈፀም በሚያስችል አኳኋን የተዋቀረ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በተግባር እንደሚታየው ክስ አቅርቦ ለማስፈረድ ከሚወሰደው ውጭ ጊዜና ጉልበት ባልተናነሰ ሁኔታ የተፈረደን ፍርድ ለማስፈፀም የሚጠይቀው ወጭና ጊዜ በልጦ የሚታይበት ጊዜ ይከሰታል፡፡ ምክንያቶቹ በርካታ ናቸው፡፡
"ችሎት መድፈር" ወይም Contempt of Court በአብዛኛው ሃገራት የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ግልጋሎት ላይ እየዋሉ ካሉ የሕግ ፅንሰ ሃሳቦች አንዱ ነው። ይህ የሕግ ፅንሰ ሃሳብ በእኛ ሃገር በሰፊው ሥራ ላይ እየዋለ ቢሆንም ከሕጉ መንፈስ ውጭ አተገባበሩ ላይ የሚታየው የሕግ አተረጓጎም ክፍተትና ልዩነት የተለያዩ የዜጎች መብት ጥሰቶችን ሲያስከትል ይታያል።
የፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 53 መሠረት በተቋቋመ ወዲህ ላለፉት 24 ዓመታት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከ1100 በላይ አዋጆችን ያወጣ ሲሆን ከእነዚህም አዋጆች ውስጥ በምክር ቤቱ በሚገኙ የገዢው ፓርቲ አባላት መካከል ሞቅ ያሉ ክርክሮችና የልዩነት ሃሳቦች ያስተናገዱ በጣት የሚቆጠሩ አዋጆች መሆናቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ሞቅ ያሉ ንትርክ አዘልና የልዩነት ሃሳቦች ከተንፀባረቁባቸው ሕጎች መካከል ለአብነት ያህል በሚንስትሮች ምክር ቤት ከየካቲት 06 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ተፈፃሚነት የነበረውንና ለሁለተኛ ጊዜ በሚኒስትሮች ምክር ቤት አዋጅ ቁጥር 2/2010 የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተቀባይነት እንዲያገኝ በቀረበ ወቅት የተደረገው እልህ አስጨራሽ ክርክር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡
ቤተሰብ የአንድ ማኅበረሰብ በጣም ጠቃሚ እና መሠረት የሆነ አካል ነው፡፡ ቤተሰብ አንድ ግለሰብን ከአጠቃላይ ማኅበረሰብ ጋር የሚያገናኝ ታላቅ ድልድይ ነው፡፡ እንዲሁም ተፈጥሮዊ ኢኮነሚያዊ እና ማኅበረሰባዊ ጥቅም አለው፡፡ በእርግጥ ቤተሰብ በቁጥር ትንሽ ሊሆን ይችላል ነገረግን የአንድ ቤተሰብ መፍረስ አጠቃላይ ማኅበረሰቡን ይጎዳል፡፡ ቤተሰብ በጋብቻ እንደሚመሠረት ሁሉ በፍቺ ይፈርሳል፡፡ በተለምዶ በቤተሰብ ሕጋችን ከተቀመጡት ጋብቻ ከሚፈርስባቸው መንገዶች በተጨማሪ ተጋቢዎች ለተለያዩ ምክንያቶች ሲሉ ህጋዊ ፍቺ ሳይፈፅሙ የሚያደርጉት መለያየት አንዱ ሲሆን ሳይፋቱ ፍቺ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ሳይፋቱ ፍቺ ምንም እንኳን በሕግ አግባብ የሚደረግ ፍቺ ባይሆንም እንኳን ውርስ ላይ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ አሉት፡፡
As I write this term paper, stream of demonstrations across Ethiopia has continued owing to human rights violations. Human rights and social movements have constitutive relationship. An Ethiopian scholar of human rights focuses on policy outcomes and legal decisions. Scholarship that examines this link in Ethiopia is relatively slow to develop.
ባለፈው ሳምንት መጨረሻ መንግሥት የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽንን የሚያቋቁም አዋጅ ማፅደቁ ይታወቃል፡፡ አዋጁ በተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ የጦፈ ክርክርን አስነስቶ በ33 ተቃውሞ እና በ4 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ ቢፀድቅም በፓርላማ ውስጥ ለአዋጁ ድምፅ ከነፈጉ የሕዝብ ተወካዮች ጀምሮ እስከ ክልል መንግሥታት ድረስ ሰፊ ተቃውሞን አስተናግዷል፡፡ ለተቃውሞው መነሻ የሆነው ዋነው ጉዳይ የማንነትም ሆነ በክልሎች መካከል የሚነሱ አለመግባባቶችን መፍታት የፌዴሬሽን ምክር ቤት እና የክልሎች ሥልጣን ሆኖ ሳለ ሌላ ተቋም የማቋቋም አስፈላጊነት እና ሕገ መንግሥታዊነት ጥያቄ ነው፡፡
ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ለዲሞክራሲያዊ ማህብረሰብ መፈጠር የመሰረት ድንጋይ ነው፡፡ ይህ መብት በጣም ረጅም ጊዜ ያስቆጥረ የሰው ልጅ መብት ሲሆን በዘመናት መካከል በፈላጭቆራጭ ነገስታት እና መሪዎች ጫና ተደርጎበታል፡፡ ለአብነት ያህልም በጥንታዊ ባቢሎናዊያን የልዩነት ሃሳብ (being dissenter) መያዝ ወደ እቶን እሳት ያስጨምር እንደነበር ከመጽሃፈ ዳንኤል ምዕራፍ 3 ንባብ መረዳት እንችላለን፡፡
Staling public money hurts the poor disproportionately by diverting funds intended for development, undermining a Government’s ability to provide basic services, feeding inequality and injustice, discouraging foreign aid and investment, fundamentally distorts public policy and leads to the misallocation of resources. What makes things worse is that the offence is usually committed by political parties. Political parties are often seen as actors who abuse their powerful position to extort bribes, to supply members and followers with lucrative positions in the public sector, or to channel public resources into the hands of party leaders or supporters. In this regard, the 2016 Republican Presidential candidate Dr. Ben Carson once made a statement, “We have been conditioned to think that only politicians can solve our problems. But at some point, maybe we will wake up and recognize that it was politicians who created our problems.”
መግቢያ
በታክስ ሥርዓት ላይ ጥናታቸውን የሰሩ ባለሙያወች “the tax system must be dynamic with in the dynamic world ” - ተለዋዋጭ በሆነው ዓለም ውስጥ የታክስ ሥርዓቱ ተለዋዋጭ ካልሆነና ዓለም በፈጠረው ቴክኖሎጅ የሚደረገውን የታክስ ስወራ ተግባር መከላከል፣ መቆጣጠር እንድሁም ድርጊቱ ተፈፅሞ ከተገኘ ሊቀጣ የሚችል ሥርዓት ካልዘረጋ የአንድ ሀገር ህልውና አደጋ ላይ ይወድቃል ይላሉ፡፡ እኔም ይህንን ሀሳብ ከሚጋሩ ባለሙያዎች አንዱ ነኝ፡፡ በመሆኑም አንድት ጠንካራ ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት ዘመናዊ ዓለምን ያማከለ ዘመናዊ የታክስ ሥርዓት መዘርጋት ስፈልጋል፡፡ ይህ ተግባር ደግሞ ገቢን በግልፅነትና ተጠያቂነት፣ በፍትሃዊነትና እኩልነት እንድሁም በዘላቂነት መሰብሰብና ማሳደግ የሚችል ሕግ ከማውጣት ይጀምራል፡፡ ሕግ ማውጣት ብቻ ሳይሆን የወጣውን ሕግ ማስፈፀም የሚችል ተቋም እና ሠራተኛ መገንባት ያስፈልጋል፡፡ ተቋሙ እና እያንዳንዱ ሠራተኛ ደግሞ በየደረጃው የወጡ ሕጎችን ለግብር ከፋዩ ማህበረሰብ የማሳወቅ ሞራላዊ ግደታ አለበት፡፡ ሆኖም ከቅርብ ጊዜ ወድህ በግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና በፍ/ቤቶች ቅሬታ እያስነሳያለው የግብር ዓይነት ተቀንሶ የሚያዝ ታክስ/ዊዝሆልድንግ ታክስ ሲሆን ለዚህ ጽሑፍ ዓላማ ከእነዚህ ታክሶች አንዱ የሆነውን እና በንግድ ማህበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና በተግባር የአፈፃፀም ችግር የሚታይበትን በገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/08 አንቀፅ 92 ላይ የተቀመጠውን በሀገር ውስጥ ከሚፈፀሙ ክፍያወች ላይ ተቀንሶ የሚያዝ ግብርን በዝርዝር ለመዳሰስ እምክራለሁ፡፡ ወደ ጉዳዩ ከመግባቴ በፊት ግን ዊዝሆልድንግ ታክስ ምን ማለት እንደሆነ ትርጉም ሰጥቼ ማለፍ እፈልጋለሁ፡፡