ተደራሽ ግን ርካሽ ዳኝነት - የኦሮሚያ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ምልከታ



በዳኛው ገጠመኝ እንጀምር። የአንዱ የኦሮሚያ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ ለተዘዋዋሪ ችሎት በሕዝብ ትራንስፖርት እየሄደ ነበር። መኪናው ውስጡ ሞልቶ ረዳቱ ከላይ ለመጫን ይቃጣዋል። መኪናው ላይ የተፃፉ ጥቅሶች እንቅጩን ይናገራሉ።

"ታሪፍ እንጂ ትራፊክ የለም፣ ጠጋ ጠጋ በሉ" 
"የሰው ልጅ ክቡር ነው፣ ትርፍ ሰው የለም ግቡ"
"ሞላ የሰው ስም ነው፣ገባ ገባ በሉ"

ወዘተ። 

እና ዳኙዬ ተጣብቆ ቆሞ ከቦታው ደረሰና ችሎት ስራውን ይጀምራል። መኪና ውስጥ ወንበር ላይ ተቀምጦ የነበረ ባለ ጉዳይ ውጭ ቆሞ ከጓደኛው ጋር "ቆሞ የመጣው ሶዳ (አማቻችን) እዚህ ደርሶ ወንበር አገኘ" እያለ ይሳለቃል። ችሎት ተደፈረ? ፖሊስ የለም። የቀበሌ ታጣቂ እንኳን የለም።

 
ሰውየው ተራ ደርሶት ተጠራና ይገባል። ዳኛው ከንግግሩ ላይ ንዴት ይነበባል። ሰውየው ግን ቀላል ፎጋሪ አይደለም "ቅድም እኮ ዳኛ መሆንህን ባውቅ እነሳልህ ነበር" ብሎ ፈገግ አለ። ከፈገግታው ጥፊ ይሻላል። ችሎት ተደፈረ? የለም የለም! ይህ የዳኛው እውነተኛ ገጠመኝ ነው።

Continue reading
  8376 Hits

በኮሮና ወረርሽኝ ፍርድ ቤቶችን እንዴት ማስቀጠል ይቻላል?

 

እርግጥ ነው አሁን ያለንበት የኮሮና ቫይርስ ወረርሽኝ ወቅት እጅግ ፈታኝ፣ ፈጣን አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመስጠት የሚከብድበት የቱ ትክክልየቱ ስህተት እንደሆነ ለማመዛዘን የሚቸግር ጊዜ ነው፡፡ በተለይም በወረርሽኙ ምክንያት የሰዎች ህይወት አደጋ ላይ መውደቁ ሲታይ አሳሳቢና አስጨናቂ ነው፡፡

በዛው መጠን ደግሞ በማዕበሉ ወቅትም ቢሆን ህዝብና የመንግሥት አስተዳደር ይቀጥላል፡፡ ፍርድ ቤቶች ደግሞ እጅግ በጣም አስፈላጊና ወሳኝየህዝብ አገልግሎት ሰጪ አካላት መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ሐቅነው፡፡ ፍ/ቤቶች ከሶስቱ የመንግሥት አካላት (the three organs of Government/state) አንደኛው ቅርንጫፍ/አካል ናቸው፡፡ ሌሎቹ የመንግሥት አካላት(አስፈፃሚውና ሕግ አውጪው) ሥራቸውን እያስኬዱ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በወረርሽኙ ምክንያት የሰውን ህይወት ለአደጋ በማያጋልጥና በጥንቃቄ ሥራቸውን የሚያስኬዱበት መንገድ ሊፈተሸ ይገባል፡፡

በጣም የሚያስደነግጠው ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ‹‹የኮሮና ቫይረስ ለማጥፋት በርካታ ዓመታት ሊወስድ ይችላል፡፡ የሚጠፋበት ጊዜ ቅርብ አይደለም እንደውም እንደ ኤች.አይ.ቪ ላይጠፋ ይችላል›› የሚል መግለጫን አውጥቷል፡፡

ስለዚህ ፍርድ ቤቶችም ሆኑ ሌሎች ወሳኝ አገልግሎት ሰጪ አካላት በቀጣይ ከቫይረሱ ጋር በጥንቃቄ ህይወት የሚቀጥልበትን መንገድ ሊያስቡበት ግድ ይላቸዋል ማለት ነው፡፡ እጅን አጣጥፎ ‹‹ጥሩ ቀን ቶሎ ና›› እያሉ ብቻ መጠበቅ አያስኬድም አያዋጣም፡፡

Continue reading
  4436 Hits

የፍርድ ቤቶች የእግድ ትእዛዝ ተፈፃሚነት እስከየት ድረስ ነው?

 

 

ለአንድ ሀገር ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ መረጋገጥ እንዲሁም ሰብዓዊ መብቶች መከበር በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ገለልተኛ፣ ነፃ፣ ተጠያቂነት ያለባቸው እና በሕዝብ ዘንድ አመኔታን ያተረፉ ፍርድ ቤቶች ሚና የጎላ እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ ያለሕግ እና ያለፍርድ ቤቶች ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ በአንድ ሀገር ውስጥ ይኖራል ብሎ መገመት አይቻልም፡፡

እነዚህ ፍርድ ቤቶች አሁን ባለው የሀገራችን ሕገ-መንግሥት ነፃ ሆነው መቋቋማቸውን እና በሀገሪቱ ውስጥ በፌዴራልም ሆነ በክልል ግዛቶች ሥር ብቸኛው የዳኝነት አካል እንደሆኑ ሕገ-መንግሥታዊ ማረጋገጫ አግኝተዋል፡፡ በዚህም አግባብ ሥራቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡

በሰዎችም መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በሰላማዊ መንገድ በስምምነት፣ በድርድር ወይም በሽምግልና ወይም በእርቅ ለመፍታት ካልቻሉ ሥልጣን ወዳላቸው መደበኛ ወይም ሕጋዊ እውቅና ወደተሰጣቸው ፍርድ ቤቶች እንደሚሔዱ ይታወቃል፡፡

Continue reading
  10307 Hits

የሰበር ዓላማ ወጥነትን ማስፈን ወይስ ሕገ-ወጥነትን ማስፋፋት?

 

ጊዜው እ.ኤ.አ 1954 ነው፡፡ ለአለም ሀገራት የዲሞክራሲ አርአያና መምህር ነኝ ብላ በምትደሰኩር በአሜሪካ ሀገር ነጭና ጥቁር ተማሪ በአንድ ላይ አይማርም ነበር አሉ፤ ምክንያቱም ጥቁር ተማሪ ከነጭ ተማሪ ጋር በአንድ ላይ እንዲማር መፍቀድ ማለት በነጭ ተማሪዎች ሞራልና ክብር መቀለድ ነው ብላ ታምን ነበር፤ አሜሪካ፡፡ በመሆኑም ጥቁሮችና ነጮች ተለያይተው ይማሩ ነበር ማለት ነው፡፡ በዚሁ አይን ያወጣ አድልዎ የተበሳጨው ብራውን የተባለው ግለሰብ በአሜሪካ ሀገር የካንሳስ ክልል የትምህርት ጉዳይ ቦርድን በፍርድ ቤት ገተረው፡፡ ሚስተር ብራውን ለጥቁሮች ሽንጡን ገትሮ ከተከራከረ በኃላ ጥቁሮችን አንገት የሚያቀና ፍርድ አስፈረደ፡፡ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጥቁርና ነጭ ተማሪዎች ተለያይተው እንዲማሩ ማድረግ የሰው ልጆች በተፈጥሮ እኩል ሆኖው የመፈጠር መብትን የሚቃረን በተለይም ደግሞ የጥቁሮች ክብርና ሞራል የሚነካ እኩል የትምህርት እድል የሚነፍግ ህገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ ከተፈጥሮ ሕግና የአሜሪካ ህገ መንግስት ጋር የሚጣረስ ነው ሲል ለሰው ልጆች እኩልነት የሚያረጋግጥ ፍርድ ሰጠ፡፡ ጥቁሮች ከነጮች ጋር ያለአድልዎና ልዩነት ሳይደረግባቸው እኩል የትምህርት እድል የማግኘትና የመማር መብት አላቸው የሚል መደምደሚያ ላይ ተደረሰ፡፡ በዚሁ ውሳኔ የተበሳጨው "ጆርጅያ ኩሪዬር" የተባለ ጋዜጣ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ዳኞችን እንዲህ ሲል ገለፃቸው፡፡

“No man knows today what his rights are in this country. No man today has any liberties left. His rights and his liberties are in the laps of the nine crazy men who sit on the Supreme Court bench. And the lord only knows what these crazy men will do next. Today they are most dangerous tyrants that ever existed. Like Hitler, Mussolini, and the other modern day tyrants, they are mentally deranged. They are crazed with a desire to serve a minority for political purposes. Their insanity has made them unscrupulous in the methods they have employed to do the bidding of this minority. They are mentally deranged tyrants ruling as unscrupulously as any tyrant in all of history. The members of this court must be curbed or they must be removed from the bench.”

ትችቱ ወደ አማርኛ ስንመልሰው በዚች ሀገር መብቱን እና ነፃነቱን የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ ነፃነቱንና መብቱን በጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንበር ቁጭ ባሉ በእነዚህ  ዘጠኝ ያበዱ ዳኞች እጅ ላይ ነው፤በቀጣይም እነዚህ እብድ ዳኞች የሚሰሩት ነገር ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ አሁን በዘመናችን አይተነው በማናውቅ ሁኔታ እነዚህ ዳኞች አደገኛ አምባገነኖች ናቸው፤እንደ እነ ሂትለር፣ሙሶሎኒና ሌሎች ዘመናዊ አምባገነኖች በጭካኔ ያበዱ ናቸው፤ለፖሊቲካ አላማ ሲባል አናሳ ማህበረሰብን ለማገልገል አብደዋል፡፡ እብደታቸውን አናሳውን ለማገልገል ይሉኝታ እንኳን ሊገድበው አልቻለም፤እነዚህ ሰዎች ሊወገዱ ይገባል ለማለት ነው፡፡ (ትርጉም የራሴ)

እኔ ደግሞ እላለሁኝ፡፡ ያበዱት ዳኞቹ ሳይሆን ጋዜጣውን ያወጣው ፀኃፊ ራሱ ነው፡፡ ይህ ጋዜጣ በወቅቱ ይዞት የወጣ ትችት ብሽቅ እና በዘረኝነት የተነዳ ከአንድ ዲሞክራሲያዊት ሀገር ፈፅሞ የማይጠበቅ ነው፡፡ የእብደት እብደት፡፡ ይህ ማለት ከፍትህ እና ከእኩልነት አንፃር የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ ከትክክልም በላይ ነበር፡፡

Continue reading
  7595 Hits