ለተዋጣለት ወንጀል ምርመራ የሚጠቅሙ ቀዳሚ ነገሮች

የተዋጣለት የወንጀል ምርመራ ሥራ ለወንጀል ፍትሕ ሥርዓት መስፈን ቁልፍ የሆነ ሚና እንደሚጫወት በርካታ በወንጀል ምርመራ ሥራ ላይ የታተኮሩ መጽሐፍት የሚገልጹት ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን፡፡ በወንጀል ምርመራ ወቀት የተፈጸመ ወንጀልን ለማግኘት እና ጥፋተኛውን ለይቶ ለማውጣት ከሚጠቅሙ ቀዳሚ ነገሮች መካከል የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡

Continue reading
  21570 Hits
Tags:

Legal updates on federal court establishment proclamation, proclamation number 1234/2021

 

Introduction

The federal court proclamation no 25/96 its amendment, which has been in force for many years, is repealed and replaced by the federal courts' proclamation number 1234/2021.  When we see in view of the existing proclamation, the new law introduced new elements. In these short notes, we will briefly explore the new features of the proclamation and the reason behind the improvements of the proclamation to its current content.

Continue reading
  6309 Hits
Tags:

በፍርድ የተከለከለ ሰው ሞግዚት ፍቺ የመጠየቅ ሥልጣን አለው ወይ? በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በተሰጠ ውሳኔ ላይ የቀረበ ትችት

ከሰሞኑ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፍቺን በተመለከተ ለየት ያለ ውሳኔ ተሰጥቷል፡: ይህን ውሳኔ ለሕዝብ ይፋ ቢደረግ ጠቃሚ ሃሳብ እንዲሸራሸር ሊረዳ የሚችል ከመሆኑም በላይ ሕጉንም ለመፈተሸ ይረዳል በሚል አስተያየት ለአንባብያን ለማድረስ እሞክራለሁ፡፡ ጉዳዩ ይፋ ቢሆንም ይግባኝ ሊቀርብበት የሚችል በመሆኑ ለጊዜው የግለሰቦችን ስም ተቀይሯል፡፡ የጉዳዩ ዝርዝር ሁኔታውም ከዚህ በታች ባለው መልኩ ተቀምጧል፡፡

አቶ ሀ እና ወ/ሮ ለ 42 ዓመታት በትዳር ቆይተዋል፡፡ ትዳራቸውም የተደላደለ ነበር፡፡ በዚህ ትዳራቸው ጊዜ ውስጥ ልጅ ያልወለዱ ሲሆን አቶ ሀ ግን ከሌላ የወለዱት  አንድ ወንድ ልጅ አላቸው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አቶ ሀ በእድሜ መግፋት (እድሜያቸው 90 ይሆናል) ምክንያት አእምሮአቸው ላይ ከፍተኛ ችግር የተከሰተ በመሆኑ የሚሰሩትን አያውቁም፡፡ የአእምሮ ችግሩን መሰረት በማድረግም የአቶ ሀ ልጅ ወላጅ አባቴ በአእምሮ ችግር የተነሳ የሚሰሩትን አያውቁም በማለት በፍርድ ይከልከሉ፤ የሞግዚትነት ስልጣንም ይሰጠኝ ሲል ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመለከቱ፡፡ ፍርድ ቤቱም የግለሰቡን የጤና ሁኔታ የሚያሳይ የሕክምና ማስረጃ እንዲቀርብ እና ግለሰቡም በችሎት ቀርበው ሁኔታቸው እንዲታይ በማድረግ ፍርድ ቤቱ ግለሰቡ በራሳቸው ራሳቸውንና ንብረታቸውን ለመቆጣጠር የማይችሉ መሆኑን ተገንዝቧል፡፡ ይህን ተከትሎም ፍርድ ቤቱ አቶ ሀ ላይ የክልከላ (Judicial Interdiction) ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ በመቀጠልም የአቶ ሀ ልጅ አሳዳሪና ሞግዚት አድርጎ ሾሟቸዋል፡፡

የአቶ ሀ ልጅም ሞግዚትና አሳዳሪ የሚለውን ሹመት ካገኘ በኋላም ይህንን ሥልጣን መሰረት በማድረግ፣ ሞግዚት አድራጊዬ በእድሜ መግፋት ምክንያት በአእምሮአቸው ላይ የጤና መታወክ የተከሰተ ቢሆንም ተጠሪ ሊንከባከቧቸው አልቻሉም፤ ተለያይተው መኖር ከጀመሩም ረጅም ጊዜ ተቆጥሯል፡፡ ስለዚህ የሞግዚት አድራጊዬና የተጠሪ ጋብቻ እንዲፈርስ ይወሰንልኝ በማለት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልክተዋል፡፡ ወ/ሮ ለ ሞግዚቱ የፍቺ ጥያቄ ይወሰንልኝ ጥያቄ ለማቅረብም ሆነ ፍርድ ቤት ቀርቦ ለመከራከር አይችሉም፣ ለፍቺ የሚያበቃም ምክንያት የለም ሲሉ መቃወሚያና መልስ ሰጥተዋል፡፡

የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤትም፣ ሞግዚቱ ጋብቻ እንዲፈርስ ለመጠየቅ ስልጣን አላቸው ወይስ የላቸውም? የግራ ቀኙ ጋብቻ ሊፈርስ ይገባል ወይስ አይገባም? የሚል ጭብጥ በመያዝ ጉዳዩን መርምሮታል፡፡ አንደኛውን ጭብጥ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ ሲተነትን

“… በፍ/ብ/ሕ/ቁ. 370(1) መሰረት ሞግዚት አድራጊ ጋብቻ እንዲፈርስ ለመጠየቅ የሚችል መሆኑ ተመልክቷል፡፡ ስለዚህ የአቶ ሀ ሞግዚት የሆኑት ልጃቸው ጋብቻው እንዲፈርስ ለመጠየቅ በሕግ ሥልጣን አላቻው ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በወ/ሮ ለ የቀረበውን ሞግዚት አድራጊው ጋብቻ እንዲፈርስ ለመጠየቅ አይችሉም የሚል ክርክርን አልተቀበለውም፡፡” 

Continue reading
  9903 Hits

የፍርድ ቤት ወይስ የችሎት ስልጣን? (Jurisdiction of Courts or Divisions)

 

ይህን ለመጻፍ ያስገደዱኝን እና የገጠመኙን ሁኔታዎች በቅድሚያ ላብራራ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው አንድ ሰራተኛ አሰሪው በነበረው ድርጅት ላይ ህገ-ወጥ የስራ ውል መቋረጥ ተፈጽሞብኛል በማለት ላቀረበው ክስ አሰሪው ድርጅት በተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠኝ ሰራተኛው የስራ ውሉን ስላቋረጠ ካሳ እንዲከፍለኝ የሚልና ሰራተኛው ስራ ላይ በነበረ ጊዜ ለስራው አገልግሎት የተሰጠውን ላፕቶፕ ኮምፒውተር ሳይመልስ በመቅረቱ ንብረቱን እንዲመልስ ወይም የንብረቱን ግምት ብር 23,000 (ሃያ ሶስት ሺ) እንዲከፍለኝ በማለት ክስ አቀረበ፡፡ ጉዳዩን ሲያይ የነበረው የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የስራ-ክርክር ችሎትም በድርጅቱ የላፕቶፕ ንብረትን በተመለከተ የቀረበውን የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ይህ ችሎት (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የማየት ስልጣን ስለሌለው ጉዳዩን በዚሁ ፍ/ቤት በፍትሐብሄር ችሎት ክስ የማቅረብ መብታቸውን ጠብቄ አቤቱታውን ውድቅ አድርጌዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታም ተከራይ ከአከራዩ ድርጅት ሶስት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችን በተለያየ ጊዜ የተከራየ ሲሆን በቅድሚያ ለተከራያቸው ሁለት ክፍሎች የውል ሰነድ ያለው ሲሆን ለሶስተኛው ክፍል ግን ከቃል ስምምነት ባለፈ በጽሁፍ የተደረገ ውል የለም፡፡ ነገር ግን ለሶስተኛው ክፍልም ቢሆን ለአራት ወራት ያህል በየወሩ ከተከራይ የኪራይ ገንዘብ የተቀበለበትን ደረሰኝ በማስረጃ አያይዟል፡፡ ይህንንም የኪራይ ውልና የኪራይ ክፍያ ደረሰኝ መሰረት በማድረግ አከራይ ላልተከፈለው እና ተከራይ ለተገለገለበት ጊዜ የኪራዩ ክፍያ ይከፈለኝ በማለት በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት ክስ ያቀረበ ሲሆን ጉዳዩን ሲመረምር የነበረው የፍ/ቤቱ የኪራይ ችሎትም (ልብ በሉ ፍ/ቤቱ አይደለም) የኪራይ ውል ሰነድ ያላቸውን  ክፍሎች አስመልክቶ ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለኝ ሲሆን የኪራይ ውል የሌለውን ሶስተኛውን የቢሮ ኪራይ ክፍያ ክስ በተመለከተ ግን ጉዳዩን የማየት ስልጣን ያለው በዚሁ ፍ/ቤት የንግድና ልዩ ልዩ ችሎት ስለሆነ በዚህ ችሎት ክስ የማቅረብ መብታችሁን ጠብቄ በሶስተኛው ቢሮ ላይ ያቀረባችሁትን ክስ ዘግቼዋለሁ በማለት ብይን ሰጥቷል፡፡

ለመሆኑ በአዎጅ የተቋቋሙ ፍ/ቤቶች እንጂ ችሎቶች ይህን መሰሉ ስልጣን አላቸው? የፍትሐብሔር የሥነ-ሥርዓት ሕጉ ዓላማስ ከዚህ አኳያ እንዴት ይመዘናል የሚለውን በጥቂቱ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡- የፌደራል ፍ/ቤቶችን ያቋቋመው አዎጅ ቀ. 25/88 በፌደራል ደረጃ የሚኖሩት ፍ/ቤቶች የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት፣ ከፍተኛ ፍ/ቤት እና ጠቅላይ ፍ/ቤት መሆናቸውን ሲገልጽ የእነዚህ ፍ/ቤቶችም በመጀመሪያ ደረጃ ስልጣንም ሆነ በይግባኝ ደረጃ ጉዳዮችን ተቀብለው አይተው እና አከራክረው ወሳኔ ሊሰጡ የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በዝርዝር ደንግጓል፡፡

ይህ አዎጅ ይህንንም ሲገልጽ እነዚህ የፌደራል ፍ/ቤቶች ጉዳየን ለማየት እንዳለቸው ስልጣን የተፋጠነ ፍትህን ለመስጠት እንዲያስችል እያንዳንዱ ፍ/ቤት ቢያንሰ ሶስት ችሎቶች እነዚህም የፍትሐብሄር፣ የወንጀል እና የስራ-ክርክር ችሎቶች ሊኖሩት እንደሚገባ (በፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 25/88 አ.ቁ 20(1) ፣23(1)) ሲደነግግ እንደሚቀርቡለት የጉዳዮች ብዛትና ዓይነት በስሩ እንደ ነገሩ ሁኔታ ሊይዛቸው የሚችሉ ችሎቶችን ፍ/ቤቱ በራሱ አስተዳደራዊ ውሳኔ የማብዛት መብት አለው (በተሻሻለው ፌ/ፍ/ቤቶች አዎጅ 454/97 አ.ቁ 23(1))፡፡

Continue reading
  13632 Hits

ተደራሽ ግን ርካሽ ዳኝነት - የኦሮሚያ ወረዳ ፍርድ ቤቶች ምልከታ



በዳኛው ገጠመኝ እንጀምር። የአንዱ የኦሮሚያ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ ለተዘዋዋሪ ችሎት በሕዝብ ትራንስፖርት እየሄደ ነበር። መኪናው ውስጡ ሞልቶ ረዳቱ ከላይ ለመጫን ይቃጣዋል። መኪናው ላይ የተፃፉ ጥቅሶች እንቅጩን ይናገራሉ።

"ታሪፍ እንጂ ትራፊክ የለም፣ ጠጋ ጠጋ በሉ" 
"የሰው ልጅ ክቡር ነው፣ ትርፍ ሰው የለም ግቡ"
"ሞላ የሰው ስም ነው፣ገባ ገባ በሉ"

ወዘተ። 

እና ዳኙዬ ተጣብቆ ቆሞ ከቦታው ደረሰና ችሎት ስራውን ይጀምራል። መኪና ውስጥ ወንበር ላይ ተቀምጦ የነበረ ባለ ጉዳይ ውጭ ቆሞ ከጓደኛው ጋር "ቆሞ የመጣው ሶዳ (አማቻችን) እዚህ ደርሶ ወንበር አገኘ" እያለ ይሳለቃል። ችሎት ተደፈረ? ፖሊስ የለም። የቀበሌ ታጣቂ እንኳን የለም።

 
ሰውየው ተራ ደርሶት ተጠራና ይገባል። ዳኛው ከንግግሩ ላይ ንዴት ይነበባል። ሰውየው ግን ቀላል ፎጋሪ አይደለም "ቅድም እኮ ዳኛ መሆንህን ባውቅ እነሳልህ ነበር" ብሎ ፈገግ አለ። ከፈገግታው ጥፊ ይሻላል። ችሎት ተደፈረ? የለም የለም! ይህ የዳኛው እውነተኛ ገጠመኝ ነው።

Continue reading
  7669 Hits

በኮሮና ወረርሽኝ ፍርድ ቤቶችን እንዴት ማስቀጠል ይቻላል?

 

እርግጥ ነው አሁን ያለንበት የኮሮና ቫይርስ ወረርሽኝ ወቅት እጅግ ፈታኝ፣ ፈጣን አስተዳደራዊ ውሳኔ ለመስጠት የሚከብድበት የቱ ትክክልየቱ ስህተት እንደሆነ ለማመዛዘን የሚቸግር ጊዜ ነው፡፡ በተለይም በወረርሽኙ ምክንያት የሰዎች ህይወት አደጋ ላይ መውደቁ ሲታይ አሳሳቢና አስጨናቂ ነው፡፡

በዛው መጠን ደግሞ በማዕበሉ ወቅትም ቢሆን ህዝብና የመንግሥት አስተዳደር ይቀጥላል፡፡ ፍርድ ቤቶች ደግሞ እጅግ በጣም አስፈላጊና ወሳኝየህዝብ አገልግሎት ሰጪ አካላት መሆናቸው ሳይታለም የተፈታ ሐቅነው፡፡ ፍ/ቤቶች ከሶስቱ የመንግሥት አካላት (the three organs of Government/state) አንደኛው ቅርንጫፍ/አካል ናቸው፡፡ ሌሎቹ የመንግሥት አካላት(አስፈፃሚውና ሕግ አውጪው) ሥራቸውን እያስኬዱ ነው፡፡ ፍርድ ቤቶችም በወረርሽኙ ምክንያት የሰውን ህይወት ለአደጋ በማያጋልጥና በጥንቃቄ ሥራቸውን የሚያስኬዱበት መንገድ ሊፈተሸ ይገባል፡፡

በጣም የሚያስደነግጠው ደግሞ የዓለም ጤና ድርጅት ‹‹የኮሮና ቫይረስ ለማጥፋት በርካታ ዓመታት ሊወስድ ይችላል፡፡ የሚጠፋበት ጊዜ ቅርብ አይደለም እንደውም እንደ ኤች.አይ.ቪ ላይጠፋ ይችላል›› የሚል መግለጫን አውጥቷል፡፡

ስለዚህ ፍርድ ቤቶችም ሆኑ ሌሎች ወሳኝ አገልግሎት ሰጪ አካላት በቀጣይ ከቫይረሱ ጋር በጥንቃቄ ህይወት የሚቀጥልበትን መንገድ ሊያስቡበት ግድ ይላቸዋል ማለት ነው፡፡ እጅን አጣጥፎ ‹‹ጥሩ ቀን ቶሎ ና›› እያሉ ብቻ መጠበቅ አያስኬድም አያዋጣም፡፡

Continue reading
  3736 Hits

የፍርድ ቤቶች በከፊል መዘጋት በማረምያ ቤት ከሚገኙ እስረኞች መብት አንጻር

 

 

የኮሮና (COVID-19) በሽታ አለም አቀፍ ችግር ሆኗል፡፡ በአለም ላይ ያሉ ሳይንቲስቶች በደረሱበት የምርምር ደረጃም በትክክል የሚተላለፍባቸው መንገዶች በሙሉ ተለይተው አይታወቁም፡፡ ነገር ግን በሽታው በሰዎች መካከል በሚኖር ቀጥተኝ (መጨባበጥ፤ መተቃቀፍ..) እና ቀጥተኛ ያልሆነ (አንድ ሰው የነካውን ግኡዝ ነገር ሌላ ሰው በመንካት …) አካላዊ ንክኪ እና የትንፋሽ ግንኙነት በቀላሉ የሚተላለፍ መሆኑ በትክክል ይታወቃል፡፡ ይህ ከሰዎች ባሕሪ ጋር በቀጥታ የተገናኘ የመተላለፍያ መንገዱ በሽታውን እጅግ አደገኛ እና አስፈሪ አድርጎታል፡፡ በሽታው ምንም አይነት ፈዋሽ መድሀኒት የሌለው መሆኑ እና ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፍበት እና የሚሰራጭበት ፍጥነት በድምር ሲታይ ብሔራዊ ስጋት ተደርጎ እንዲወሰድ አድርጎታል፡፡ በበሽታው የተፈጠረው ብሔራዊ ስጋት ተራ ስጋት ሳይሆን ከፍተኛ እና ከባድ ስጋት ነው፡፡   

በሽታው ምንም አይነት ፈዋሽ መድሀኒት የሌለው ከመሆኑ አንፃር ያለው ብቸኛ መዳኛ መንገድ በበሽታው ላለመያዝ አስቀድሞ የሚደረግ የመከላከል ተግባራትን መፈፀም ብቻ ነው፡፡ የሕክምና ባለሙያዎች ከበሽታው አስቀድሞ መከላከያ መንገዶች አድርገው በዋናነት የሚጠቅሷቸው ዘዴዎች አካላዊ ርቀትን መጠበቅ እና ንፅህናን መጠበቅ ናቸው፡፡

አካላዊ ርቀትን መጠበቅ የሚለው የመከላከያ ዘዴ ሰዎች በቤታቸው ተቀምጠው ራሳቸውን ከሌላው ሕብረተሰብ ከልለው እንዲቀመጡ ከማድረግ ጀምሮ በስራ፤ በትራንስፖርት እና በሌሎች አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥም ቢያንስ የሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ርቀትን በማስጠበቅ እንዲንቀሳቀሱ እና አገልግሎት እንዲገኙ ማድረግን የግድ ይላል፡፡ ይህን በከተማ ብሎም በሀገር ደረጃ ተግባራዊ ማድረግ እና ተግባራዊነቱን መከታተል እና መቆጣጠር ቀላል ተግባር አይደለም፡፡ በዚሕ መሀከል የሚፈፀም ትንሽ ስህተት ተቆጥሮ የማያልቅ የብዙ ሰዎችን ሕይወት የሚቀጥፍ ወይም አደጋ ላይ የሚጥል ውጤት ሊያስከትል ይችላል፡፡

Continue reading
  4159 Hits

በፍርድ ከሄደች በቅሎየ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦየ (ለውጥ የሚሹ የፍርድ ቤት ጉዳዮች)


ፍርድ ቤት የበደል ስር የሚቆረጥበት ፤ ተበዳይ የሚካስበት፤ አጥፊ የሚቀጣበትና መንግስት ከህግ በታች መሆኑ የሚረጋገጥበት መድረክ ነው፡፡ ፍርድ ቤት ፍትህ ከረቂቅነት ከፍ ብላ የምትታይ ፣ የምትሰማ እና የምትዳሰስ ህልው መሆኗ የሚታወቅበት አደባባይ ነው፡፡ ፍርድ ቤት የሰለጠነ ህዝብ የኔ የሚለውን ህግ የሚያስከብርበት መሳሪያ ነው፡፡ ህይወቱ ፣ ንብረቱና የኔ የሚላቸው እሴቶቹ ሁሉ ጥበቃ ያላቸው ስለመሆኑ የሚተማመንበት ዋሱ ነው ፍርድ ቤት፡፡


የምትታሰረው ፣ የምትፈታው፣ ከአታላዮች ገንዘብህን የምታስመልስው፣ ስሜ አስጠላኝ ልቀይር ፣ ትዳር ከበደኝ ልፋታ ካልክ መሄጃህ ፍርድ ቤት ነው፡፡ ሞት የሚፈርደብህ፣ ቀሪ ዘመንህን በአንድ የተከለለ የቆርቆሮ ግቢ ውስጥ በጥበቃ ስር ሆነህ እንድታሳልፍ የምትገደደውም በፍርድ ቤት ነው፡፡ ተበድያለሁ ልካስ ፣ በድሏል ይቀጣ ፣ የመናገር ነፃነቴ ይከበር ፣ የመዘዋወር መብቴ ተገደበ ብለህ የምትጮህውም ፍርድ ቤት ነው፡፡ ክብሬ ተንክቷል ልከበር ፣ ስሜ ጠፍቷል ይታደስ ፣ ገንዘቤ ተወስዷል ይመለስ ማለት የምትችለውም በዚያው ነው፡፡ አርእስቱን የተቀኘው ባለቅኔም በፍርድ ከሄደች ብዙ ዋጋ ከምታወጣው በቅሎው ይልቅ ያለፍርድ የሄደችው በሳንቲም የምትተመነው ጭብጦው የቆጨችው ያለፍርድ በዘፈቀደ የሚደረግ ድርጊት የፍትህ መዛባት የፍርድ መጓደል አድርጎ ስለሚመለከተው ነው፡፡


ታዲያ ይህን ሁሉ ማድረግ የሚችሉት ፍርድ ቤቶቻችን እነዚህን ጉዳዮች በጊዜው ፣ በእኩል እና ያለአድሎ ለመፈጸም በሚያስችላቸው ቁመና ላይ ይገኛሉ? በርግጥስ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚታመን ሲቀጣም ሲፈታም ልክ ነው የሚባል ፍርድ ቤት ገንብተናል? ፍትህ ለሁሉም በግዜው ተደራሽ ሆኗል?


ፀሃፊው ለጥያቄዎቹ የሚሰጠው ምላሽ ከፁሁፉ አርእስት ጋር አንድ እና ያው ነው፡፡ ይህ ፅሁፉ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ክብርት ፕሬዝዳንቷ ከመሾማቸው ቀደም ብሎ ለንባብ ለማብቃት ታስቦ በመሃል ክብርት ፕሬዝዳንቷ በመመረጣቸው የፅሁፉ ፋይዳ ከትችት ወደ ቸግር ተቋሚነት ከፍ ብሏል፡፡ የትላንቱ የፍርድ ቤት ዘመን አጥፍቶም ሆነ አልምቶ አልፏል፡፡ ለለውጥ የተሾሙት እና የሚሾሙት አዲስ ሀይሎች የትላንቱን ችግር መፍትሄ ማፈላለጊያ በማድረግ አዲስ ዘመን እንደሚያነጉ ይታመናል፡፡
ይህ ፅሁፍ መንግስት ለፍርድ ቤቶች ትኩረት ከመንፈጉ የተነሳ፣ በተበላሸ አስተዳደር ምክንያት ፣ ለሙግት ምክንያት የሚሆኑ ጉዳዮች ፍርድ ቤቶችን በማጨናነቃቸው ሳቢያ ፣ ለነሱም ትኩረት እና ምስጋና ሳይቸራቸው በሚቻላቸው መጠን በችግሮቹ መሀል ያላቸውን የሰጡ ለሀቅ እና ለፍትህ የቆሙ ዳኞችን አይመለከትም፡፡ ይልቁንስ በዚህ ችግር መሃል የቻሉትን አድርገዋል እና ምስጋናየ ይድረሰቻው፡፡ ይልቁንም ፅሁፉ ለችግሮቹ ዋና ምክንያት የሆኑትን የትኩረት ማጣት፣ የአስተዳደር ብልሽት እና ስሁት የሆኑ የፖሊሲ ጉዳዬች ላይ ያተኩራል፡፡


ዳኛ መሆን የሚገባው ማን ነው፡፡

Continue reading
  9676 Hits
Tags:

Fly-by-Night: A Brief Overview of the Federal Courts Draft Proclamation

 

 

1. Introduction

This piece provides a bird’s eye view of the draft proclamation on the Federal Courts with particular focus on issue of Cassation.

Needless to mention, the Ethiopian legal system is used to be typical follow continental legal system as it mainly contains four substantive codes i.e., Civil Code, Criminal Code, Commercial Code and Maritime Code and two procedural codes i.e., Civil Procedure Code and Criminal Procedure Code.  This implies that decisions of courts will not have a binding and precedential value to settle future related cases.

Continue reading
  4145 Hits

The Control of constitutionality of laws - (A comparative analysis between Ethiopia and Nigeria)

1.      Introduction

This essay examines the normative contemporary constitutional law question ‘how constitutionality of laws is controlled?’ under Ethiopian and Nigerian Federal Systems. In constitutional terms, both this question and federal systems require a written constitution that serve as a fundamental or basic law and placed hierarchically at the highest peak.

Federalism with written constitutions is one of the hallmarks of the Ethiopian and Nigerian political system. In both countries there are constitutionally entrenched distribution of powers between States and federal government to enact law, to execute and adjudicate as means of modern attempt to accommodate democratic complexity and pluralism. In exercising these constitutionally entrenched powers, the possibility of enacting inconsistent and ultra virus laws and hence, disputes regarding the constitutionality of laws is inevitable. The federal and state laws should be consistent not only with the terms and conditions of the federal constitution i.e. considered as a Basic Law but also should exist in harmony with each other. The settling of disputes concerning the constitutionality of laws is essential in federal systems and takes distinct form. Irrespective of its distinct form, the constitutionality of laws is one of the central problems of Constitutional Law that must be addressed in any federal states.

The objective of this essay is therefore; to compare how Ethiopia and Nigeria arrange the control of constitutionality of laws in their federal structure the aim of which is to guarantee and ensure the observance of hierarchy of legal norms and rule of law. In doing so, the essay is divided in to four sections. Section I explore the methods of controlling Unconstitutional Provisions and provide list of possible solutions for comparison. Section II demonstrates the general background and legal basis for application of control over unconstitutional provisions in Ethiopia and Nigeria. Section III compares the two countries method followed by conclusion under Section IV.  

 

Continue reading
  16978 Hits