መጥላት ላለብን የጥላቻ ንግግር የተጨማሪ ሕግ አስፈላጊነት

ኢትዮጵያውን የሚሳተፉባቸውን የማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሚጠቀምና ሌሎች ተጠቃሚዎች የሚጽፏቸውን ወይንም የሚጭኗቸውን ጽሑፎች፣ ምሥሎችና ድምፆች ለሚከታተል ሰው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንድ ግልጽ የሆነ አዝማሚያ እያደገ መምጣቱን ያስተውላል፡፡ ይኼውም ጥላቻን ያዘሉ ንግግሮች መበራከታቸውን ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር እጅግ ብዙ የሆኑ በጎ እሴቶችን የመናጃ መንደርደሪያ ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር ጥላቻ ላይ የተመሠረቱ ወንጀሎችን መጥሪያ ነው፡፡ የጥላቻ ንግግር አድልኦና መገለልን ያመጣል፡፡ የጥላቻ ንግግር የአንድን ብሔር አባላት፣ የሃይማኖት ተከታዮች፣ ስደተኞችንና ሌሎች ቡድኖችን እንበለ ምክንያት በጭፍኑ እንዲጠሉ መንገድ ያለሰልሳል፡፡ የከፋው ደግሞ የዘር ማጥፋትን ወይንም ቡድን ጠረጋን ሊያስከትል ይችላል፡፡ በበርካታ አገሮችም ተከስቶ ነበር፡፡

  16582 Hits