The blogger is an advocate and consultant at law and a columnist in the "Behig Amlak" column of the Reporter Amharic version. He graduated from Addis Ababa University Law Faculty in 2001 with his undergraduate and, in 2010, his masters in Human rights law. ጸሐፊውን በ getukow@gmail.com ማግኘት ትችላላችሁ::

ዘመን ሲለወጥ ያልተለወጡት ድንጋጌዎች

ሕግና ኅብረተሰብ ጠንካራ ቁርኝት አላቸው፡፡ ኅብረተሰብ በሌለበት ሕግን ማሰብ፣ ሕግ በሌለበት በሥርዓት የሚኖር ኅብረተሰብን ማሰብ አስቸጋሪ ነው፡፡ ይህ ግንኙነት አንዳንድ ጊዜ በመቀዳደም ሊፈጸም ይችላል፡፡ ሕግ ኅብረተሰብን ዘመናዊ ለማድረግና ለመለወጥ እንደ መሳሪያነት ሊያገለግል ይችላል፡፡ በእንዲህ ዓይነት ጊዜ የሕጉ ዓላማ ኅብረተሰቡ ያልደረሰበትን ለውጥ ማስገኘት ነው፡፡ በተቃራኒው ከኅብረተሰቡ የሚወጡ እሴቶችና ባህሎችን ወደ ሕግ ደረጃ በማሳደግም የኅብረተሰቡን ሕልውና ማስቀጠል ይቻላል፡፡ እነዚህ የተሳሰሩ ግንኙነቶች ኅብረተሰቡ ከሕግ መጠቀም የሚቻልበትን ሁኔታ የሚያሰፋ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ በሆነ መልኩ ሕጉ ከኅብረተሰቡ ዕድገት ወደ ጓላ ከቀረ ሕጉ ከወረቀት ያለፈ ተፈጻሚነት አይኖረውም፡፡ ይህን ችግር በአገራችን የተወሰኑ ሕግጋት እናስተውለዋለን፡፡

  13360 Hits
Tags:

የኤቲኤም ካርድ በጠፋ ጊዜ የባንክ ኃላፊነት

በዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ክፍያን ከሚያሳልጡ አሠራሮች መካከል አንዱ የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ነው፡፡ አንድ የባንክ ደንበኛ በባንኩ ውስጥ በከፈተው ሒሳብ ያጠራቀመውን ገንዘብ ለማውጣት የቁጠባ ሒሳብ ደብተሩን መያዝ፣ የባንክ ባለሙያን ማነጋገር፣ ገንዘብ ወጪ ለማድረግ የሚያስችል ፎርም መሙላት፣ ወረፋ መጠበቅ ወዘተ. አይጠበቅበትም፡፡ በደንበኛውና በባንኩ መካከል በሚፈጸም የኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ውል ከባንኩ ካርዱንና የሚስጥር ቁጥሩን በመቀበል ባንኩ በተለያዩ ቦታዎች ካስቀመጣቸው የኤቲኤም ማሽኖች አገልግሎት ማግኘት ይችላል፡፡ በአገራችን ይህ አሠራር በተግባር ላይ ከዋለ የተወሰኑ ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ በጣም ውሱን ከሆኑ ጀማሪ ባንኮች በስተቀር በሁሉም የግልና የመንግሥት ባንኮች ተፈጻሚ ሆኗል፡፡ የኤቲኤም ካርድን መጠቀም የራሱ የሆኑ ጥቅሞች እንዳሉት የታመነ ቢሆንም፣ የተወሰኑ በአጠቃቀም ወቅት የሚስተዋሉ ችግሮች እንዳሉ ብዙ ሰው የሚያውቀው ነው፡፡ የኤቲኤም ካርድ በአንዳንድ ማሽኖች ተቀባይነት አለማግኘቱ፣ አንዳንዶቹ ፈጽሞ የማይሠሩ (Active ያልሆኑ) መሆናቸው፣ በአንድ ቀን ማውጣት የሚቻለው የገንዘብ መጠን መወሰኑ፣ የኔትወርክ አለመኖርና ተደጋጋሚ የማሽን ብልሽት፣ በቂ የክፍያ ማሽኖች በየቦታው አለመኖራቸው፣ በኤቲኤም አሠራር የሚታዩ ግድፈቶች ወዲያው ሊታረሙ አለመቻላቸው ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው፡፡ በዚህ ጽሑፍ የምንመለከተው ግን ከባንኩ ውጭ በሆኑ ምክንያቶች በኤቲኤም ካርድ አገልግሎት ላይ ከተጋረጡ ችግሮች ዐቢይ የሆነውን የካርድ መጥፋት ጉዳይ ነው፡፡

  20110 Hits

የቴምብር ቀረጥ የሚከፈልባቸውና የማይከፈልባቸው ግብይቶች

መንግሥት ገቢ ከሚሰበሰብባቸው ምንጮች መካከል የቴምብር ቀረጥ አንዱ ነው፡፡ የቴምብር ቀረጥ ቀጥተኛ ያልሆነ ታክስ ሲሆን፣ የሚሰበሰበውም በተወሰኑ ሰነዶች ላይ እንዲለጠፍ ወይም እንዲከፈል በማድረግ ነው፡፡ በአገራችን የቴምብር ቀረጥ የተጣለው ስለ ቴምብር ቀረጥ አከፋፈል በወጣው አዋጅ ቁጥር 110/90 መሠረት ነው፡፡ የዚህ አዋጅ አፈጻጸም በተለያዩ ባለድርሻ አካላት መካከል ያለው አሠራር ተመሳሳይ አይደለም፡፡ በተግባር በሰነዶች የተለያዩ ግብይቶች (Transactions) የሚፈጸሙ ሰዎች፣ የአገር ውስጥ ገቢ ሠራተኞች፣ ባንኮች፣ ፍርድ ቤቶች ወዘተ የየራሳቸው የአዋጁ አረዳድ አላቸው፡፡ የልዩነቱ ምንጭ አዋጁን ካለማወቅ፣ ከአዋጁ ድንጋጌዎች ይልቅ በልማድ መሥራት፣ እንዲሁም የአዋጁን ክፍተት የሚሟሉ መመርያዎችን አለማወቅ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ የአዋጁ አፈጻጸም የሕግ አውጪውን መንፈስ እንዲከተል ማስቻል የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ነው፡፡

  21308 Hits
Tags:

ፍርድ ቤቶች የዘነጓቸው አንገብጋቢ የተገልጋይ መብቶች

ፍርድ ቤቶች ሐምሌ 30 ሥራቸውን ካጠናቀቁ አንድ ሳምንት ሆናቸው፡፡ በየዓመቱ በክረምቱ አጋማሽ ተዘግቶ በመስከረም መጨረሻ የሚከፈተው ፍርድ ቤት ክረምት ጭር ይላል፡፡ የተወሰኑ የወንጀል ችሎቶችና ተረኛ ችሎቶች ካልሆኑ በቀር ፍርድ ቤቱ ከመደበኛው ሥራ ይቀዘቅዛል፡፡ አዲስ ፋይል መክፈት፣ አስቸኳይ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ (ለምሳሌ እግድ) መስጠት፣ ከበድ ያሉ የወንጀል ጉዳዮች ከመመልከት ውጭ መደበኛ ቀጠሮ አይስተናገድም፡፡ በዚህ በክረምት ወቅት ችሎቶቹ አይሠሩም ማለት እንጂ አስተዳዳሪዎቹ፣ ስለ ፍርድ ቤቶቹ የተሻለ አሠራር፣ የዳኞች አቅም የማጎልበት ሥራ፣ ስለ ሥራቸውና አገልግሎት አሰጣጣቸው የሚቀርቡ ቅሬታዎችን የማስተካከል ሥራ ላይ ይጠመዳሉ ተብሎ ይታሰባል፡፡ ፍርድ ቤቱ ልማዳዊ የፍርድ ቤት አሠራሮችን በማስቀረት፣ የዳኞችን ሥነ ምግባር በመቆጣጠር እንዲሁም ለተገልጋዮች ምቹ የሚሆንበትን ሥራ የሚያስብበት ወቅት በመሆኑ፣ በዚህ ጽሑፍ በፍርድ ቤቶች የተዘነጉ ግን ተገልጋዮችን እየጎዱ ባለ ልማዶችና አሠራሮች ላይ የተወሰነ ምልከታ ለማድረግ እንሞክር፡፡

  15477 Hits
Tags:

ጥንቃቄ የሚፈልገው ዳኞችን የመሾም ሥርዓት

በማንኛውም አገር የመንግሥት አስተዳደር ከሕግ አውጪውና ከሕግ አስፈጻሚው እኩል የዳኝነት አካሉ አደረጃጀት፣ አወቃቀርና ጥንካሬ የሥርዓቱን ዴሞክራሲያዊነት ይወስናል፡፡ የዳኝነት አካሉ ገለልተኛና ነፃ ባልሆነ መጠን የሥርዓቱ ዴሞክራሲያዊነት ዋጋ ያጣል፡፡ የዳኝነት አካሉ መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ መርሆችን ለማስፈጸም፣ የዜጎች የሰብዓዊ መብቶች እንዲጠበቁና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን ገለልተኛ፣ ግልጽ አሠራርን የሚከተልና ጠንካራ እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ በ1987 ዓ.ም. የወጣው ሕገ መንግሥታችን በአንቀጽ 78 እና 79 እነዚህ መሠረታዊ የዳኝነት አካሉ መገለጫዎችን ደንግጓል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ መንግሥቱ ከወጣ ከ25 ዓመታት በኋላም የዳኝነት አካሉ የአሠራር ግልጽነትና ተጠያቂነት አመርቂ እንዳልሆነ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይስማማሉ፡፡

  11146 Hits

የልማድ አቤቱታ የፍርድ ጥራት ላይ ያለው ተፅዕኖ

መኳንንት ከሕግ ትምህርት ቤት ተመርቆ ሲወጣ ግር ያለው ነገር የትምህርቱና የአተገባበሩ ልዩነት ነው፡፡ በአብዛኛው በንድፈ ሐሳብ አስተምህሮና ትንተና ላይ የሚተኮረው ትምህርቱ በተግባር ከሚታየው የፍርድ ቤት ነባራዊ ሁኔታ ጋር አልታረቅ ብሎት ተቸግሯል፡፡ ይህን ችግሩን ያባባሰው ደግሞ ከቤተሰቡ አንዱ የወራሽነት የምስክር ወረቀት ከፍርድ ቤት እንዲሰጠው በማሰብ አቤቱታውን እንዲያዘጋጅለት ሲጠይቀው ነው፡፡ አቤቱታውን አዘጋጅቶ ለቤተሰቡ አባል ቢሰጠውም በአንዱ ክልል ከሚገኘው የወረዳ ፍርድ ቤት የገጠመው ነገር ሌላ ነው፡፡ ቤተ ዘመዱ በፍርድ ቤቱ አቤቱታው በትክክል አለመጻፉ ተነግሮት በፍርድ ቤቱ ደጃፍ ከሚገኙት ራፖር ጸሐፊ ተጽፎ እንዲመጣ ተመከረ፡፡ ሰውየውም የተባለውን ፈጽሞ አቤቱታው ተቀባይነት አግኝቶ የወራሽነት የምስክር ወረቀት አገኘ፡፡ የመኳንንትና የራፖር ጸሐፊው አቤቱታ ልዩነት ቀላል ነበር፡፡

  12922 Hits

የሰበር ፍርድ ያለማክበር ልማድና ውጤቱ

ጸሐፊው በሚከታተለው አንድ የንግድ ችሎት ጉዳይ ጠበቃው የችሎቱን ዳኛ ያማርራል፡፡ የዳኛውን የችሎት አካሄድ እየተቸ በዕለቱ በሰጠው ፍርድ ጠበቃው ለጉዳዩ ጠቃሚ የሆነውን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ የሕግ ትርጉም የችሎቱ ዳኛ በፍርዱ አለማካተቱ፣ ለጉዳዩ አግባብነት ያለው መሆኑንና ይዘቱንም በፍርዱ ለማንፀባረቅ ፈቃደኛ አለመሆኑ እጅጉን አንገብግቦታል፡፡ እንደ ጠበቃው አነጋገር ‹‹ከሳሾች ባቀረቡት ክስ ለጉዳዩ አግባብነት ያለውን የሰበር ችሎት ቅጹን፣ የመዝገብ ቁጥሩንና ቀኑን አመልክተን አቀረብን፣ በቃል ክርክርም ይህንኑ በአጽንአት እንዲመዘገብልን አመለከትን፤›› ይላል፡፡ ውጤቱን ሲገልጽ ደግሞ ዳኛው በፍርዱ ሀተታውም ሆነ ትንታኔ የሰበር ችሎቱን ፍርድ አልገለጸም፣ የሰጠውም ፍርድ ሰበር ችሎቱ ከሰጠው አስገዳጅ ትርጓሜ ጋር የሚጋጭ በመሆኑ በይግባኝ ከማሳረም ውጭ አማራጭ እንደሌለው ተናገረ፡፡ 

  10774 Hits

የ‹‹ያስቀርባል … አያስቀርብም›› እንቆቅልሽ

ዶ/ር ትዝታ በፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ጉዳዩዋን ለመከታተል በችሎት ታድማለች፡፡ በሥር ፍርድ ቤት በቤቷ ላይ ያለአግባብ ፍርድ ተሰጥቷል ብላ ስላመነች የተማረ ጠበቃ የይግባኝ አቤቱታ ጽፎላት ጉዳይዋን በራሷ ትከታተላለች፡፡ እንደ እርሷ አስተሳሰብ ጉዳይዋን ከእርሷ ይልቅ የሚረዳው የለም በሚል ከዳኛ ፊት ቀርባ ለማስረዳት ጓጉታለች፡፡ በዛሬው ቀጠሮ ይህ ሐሳቧ እንደሚሳካላት በውጭ የሚያማክራት ጠበቃ ነግሯታል፡፡

  16090 Hits

ሰበር በአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ሥልጣን ላይ ያሰመረው ቀጭን መስመር

የአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣናቸውን የተመለከቱ የተለያዩ ክርክሮች ተነስተዋል፡፡ ዋናው ክርክር በተቋቋመበት ወቅት የተነሳው የሕገ መንግሥታዊነት ጭብጥ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 78 እስከ 80 የዳኝነት አካሉን ሲያዋቅር በተለያዩ ደረጃዎች ያሉት የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚቋቋሙ በመግለጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚወሰዱ ጊዜያዊና ልዩ ፍርድ ቤቶች እንደማይቋቋሙ ደንግጓል፡፡

  14399 Hits

የማይደፈረውን ፍርድ ቤት መድፈር

በአንጌሳ ኢቲቻ የተጻፈውን ‹‹ችሎት መድፈር፡- ሕጉና የአሠራር ግድፈቶች›› የሚለውን ሳነብ እ.አ.አ በታኅሣስ 2013 በተመሳሳይ ርዕስ የጻፍኩትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ፡፡ በዚህ ጽሑፌ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ማለት ነው? የኢትዮጵያ ሕግ ስለ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ይላል? የሕጉ ዓለማስ ምንድነው፣ የወንጀሉ አወሳሰን ልዩ ባህርይስ እንዴት ይታያል፣ በአፈጻጸም የሚታዩ ችግሮች ምንድናቸው የመሚለውን እዳስሳለሁ፡፡

  11957 Hits