ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል?

ይህ አጭር ጽሁፍ በቅርብ ጊዜ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር መዝገብ ቁጥር 76248 ላይ፤ በኦሮሚያ ጠቅላይና በአዳማ ልዮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተሰርቷል ማለት አይቻልም በሚል፤ በሶስት ዳኞች ጥቅምት 6 2005 የተዘጋን ጉዳይ መሰረት አደርጎ የቀረበ ነዉ፡፡ የምንዳስሰዉ ጥያቄ በጽሁፉ ርእስ ላይ የተመለከተዉን ነዉ፤ ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል? ለጽሁፉ አላማ የተከራካሪ ወገኖችን ስም መጥቀስ አስፈላጊ ስላልሆነ አበዳሪ፤ ከሳሽ፤ ተበዳሪ፤ እና የተበዳሪ ልጅ የሚሉትን እንጠቀማለን፡፡ በአጭሩ ፍርድ ቤቶቹ የወሰኑት ባለእዳዉ ሳይሆን ሌላ ሰዉ (የጽሁፍ ዉክልና ሳይሰጠዉ በፊት) በባለእዳዉ ስም ያደረገዉ የእዳ አከፋፈል እንዳልተደረገ ስለሚቆጠር ይርጋን አያቋርጥም በማለት ወስነዋል፡፡

  13242 Hits

ስለ እንደራሴ (ውክልና) ሕግ አንዳንድ ነጥቦች

ውክልናን የተመለከተው ሕግ በአገራችን በብዛት ስራ ላይ ከሚውሉ የሕግ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የፍትህብሄር ሕግ ቁጥር 2199 ውክልናን እንደተረጐመው “ውክልና ማለት ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ህጋዊ ሥራዎች በወካዩ ሥም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ማለት ነው” ይላል፡፡ ከትርጉሙ ለመረዳት እንደምንችለው ውክልና የሚደረገው በወካይና በተወካይ መካከል ሲሆን በውክልናው የሚከናወኑት ስራዎች ህጋዊ መሆን አንዳለባቸው ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ህጋዊ ባልሆኑ ነገሮች ላይ የሚደረግ ውክልና ተቀባይነት የለውም  ማለት ነው፡፡ በሰፊው ስንመለከት ሁለት አይነት ውክልናዎችን እናገኛለን፡፡ እነሱም በፍተሃብሄር ሕግ ቁጥር 2189 ላይ የተቀመጠው ፍፁም የሆነ እንደራሴነት /disclosed or complete  agency/ እና በዚሁ ሕግ ቁጥር 2197 ላይ የተቀመጠው እንደራሴው በራሱ ስም ተግባሮችን የሚፈፅምባቸው የውክልና አይነት/undisclosed agency/ ናቸው:: ለዚህ ፅሁፍ አላማ ግን  የመጀመሪያው አይነት ውክልና ማለትም ፍፁም የሆነውን የእንደራሴነት አይነት እንመለከታለን፡፡ ይህም በፍትሃብሄር ህጉ ቁጥር 2199-2233 ድረስ ያሉትን የህጉን አንቀጾች የተመለከተ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ ፅሁፍ ውስጥየውክልና አስፈላጊነት፣ የውክልና ምንጮች ፣ የውክልና አመሰራረት፣ የውክልና አይነቶች፣ የውክልና ግብ ፣ የተወካይና የወካይ ግዴታዎች፣ ውክልና የሚቋረጥበት ሁኔታ፣ ከውክልና መመሰረት ጀምሮ በውክልና አማካኝነት የሚከናወኑ ተግባሮችና ውጤቶቻቸው ድረስ ወካይ፣ ተወካይና የውክልና ማስረጃውን የሚሰጡ አካሎች ሊያደርጓቸው የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የሚዳሰሱ ይሆናል፡፡

  31914 Hits
Tags:

የእንደራሴነት ሕግ (Agency Law) ዋና ዋና ነጥቦች

ሰዎች ኑሮአቸውን ስኬታማ ለማድረግ በሚፈጽሙት የእለት ተእለት ተግባራቸው ከሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎች ጋር ዘርፈ ብዙ መስተጋብሮችን የሚፈጽሙ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይሁንና እነኚህን መስተጋብሮች  በተለያዩ ምክኒያቶች በራሳቸው ለመፈጸም የማይችሉ በሆነ ጊዜ ሥራዎችን ሌላ ሰው እንዲያከናውንላቸው ፍላጎት ሊያድርባቸው እንደሚችል የሚያሻማ አይደለም፡፡ በዚሁ መሠረት ይህንኑ ሥራቸውን ማን፣ መቼ፣ በምን ሁኔታ እና በድካም ዋጋ ክፍያ ወይም ያለ ክፍያ  ሊሠራላቸው እንደሚገባ የመወሰን ነጻነት ሊኖራቸው የተገባ ነው፡፡  

  13494 Hits
Tags:

Ferqe - Agency and Arbitration under Ethiopian Law

A principal-agent relationship is like a tripartite contract where the agent enters into any legal transaction on behalf of the principal. Art 2199 of the Civil Code defines agency as “a contract whereby a person, the agent, agrees with another person, the principal, to represent him and perform on his behalf one or several legally binding acts.” Such an authority can be conferred by court or by agreement of the parties.

  15519 Hits