I am interested in using comparative, economic, and legal approaches and insights to understand, explain and assess institutional, policy, legal, and regulatory frameworks governing various activities. In the past, I was a research fellow in the United Nations, working on climate governance and regulatory affairs, and a lecturer of law at Mekelle University and University of Surrey. I studied comparative law and economics at Addis Ababa University (LLB, 2001); Ghent University (LLM, 2004); Erasmus University of Rotterdam, Ghent University and University of Manchester (EMLE, 2009); and University of Surrey (Ph.D., 2011).

በጽሑፍ የሰፈረን የውል ቃል የምስክርና ሌላ ዓይነት ማስረጃን በማቅረብ ማሻሻል ይቻላል?

የጉዳዩ መነሻ

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በመዝገብ ቁጥር 78398 በአቶ ሽፈራዉ ደጀኔ እና ወ/ሮ ጸሀይ ተስፋዬ በአንድ በኩልና በአቶ ሲሳይ አበቡ በሌላ በኩል በተደረገ ሙግት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ጥቅምት 19 2005 የሰጠዉ ዉሳኔ ነዉ፡፡ ጉዳዩ የተጀመረዉ በወረዳ ፍርድ ቤት በአቶ ሲሳይ አበቡ ከሳሽነትና በአቶ ሽፈራዉ ደጀኔ እና ወ/ሮ ጸሀይ ተስፋዬ ተከሳሽ ነዉ፡፡ ከሳሹ እንደሚለዉ በእሱና በተከሳሹ መካከል ሐምሌ 17 2003 የተቋቋመ የቤት ሽያጭ ዉል አለ፡፡

Continue reading
  16263 Hits

Legal Effects of Unregistered Property Interests on Third Parties: What is the Position of Ethiopian Law?

If you have an interest on a property and this interest is registered, it will have legal effects on third parties. The idea is the third party knew or should have known of a prior interest registered before the acquisition of his own interest. Government enhances certainty and security of land transactions by providing a registry system. The purpose of this registry system is to register anyone who has prescribed interests (such as mortgage) on a land so that third parties would have a chance to inspect the registry and decide whether to make another transaction. There is of course a practical question of as to whether the current registry system provides such service to inquirers. Leaving this aside, another question is what if the interest is not registered because the law does not require such interest to be registered in the first place or because of other reasons. Consider the following:

 

X owns a building part of which is rented to Y on the basis of a written but unregistered contract for a period of 15 years. Y has undertaken to pay the rent quarterly in advance. X developed a business idea and borrowed money from Easymoney Share Company by providing his building as collateral. The contract of mortgage is registered. Now that X defaulted in paying back the sum he borrowed, Easymoney plans to foreclose the building. The question is now as to whether Easymoney or any purchaser of the building will have the right to evict Y?

 

The above set of facts presents two competing interests. On the one hand, there is the property interest of the bank which did not know of the existence of this long-term contract of rent. On the other hand, you have the contractual interest of Y which has planned all his business on the understanding that he would have the right to the use of the building for the agreed period of time. It is true that this contract was not registered but it is also true that the law does not require such contracts to be registered. In a recent case, the Cassation Division of the Federal Supreme Court decided that Article 1723(1) does not include contracts of leases (Rental Houses Administration Agency v Sosina Asfaw [2005] File Number 15992). Article 1723(1) provides that "a contract creating or assigning rights in ownership or bare ownership on an immovable or an usufruct, servitude or mortgage of an immovable shall be in writing and registered with a court or notary". It should be noted that Article 1723 is concerned with the validity of the contract between the parties and not with its effect on third parties. Therefore, it can be argued that contracts of lease for whatever period of time could be made in any form and will still be valid. The question relates to the effect of contracts of lease on third parties. In this regard, Article 2899(1) provides that "leases for a period exceeding five years shall not affect third parties until they are entered in the registers of immovable property at the place where the immovable is situate". It follows therefore that even if oral or written but unregistered contracts of lease are binding on the parties, their effect on third parties depend on the period of time they are made and whether they are registered. If the lease is made for a period of time exceeding five years, it should be registered for it to have affect third parties. In the above example, the contract of lease is for a period of 15 years but not registered. In such cases, Article 2899(2) provides that the contract of lease affects third parties only for five years from the day when the the third party has registered his/her right on the immovable. It follows therefore that the contract of lease between X and Y affects Easymoney for a period of five years. If on the other hand, the period of time for which the contracts of lease is made is not certain and the contract of lease is not registered, Article 2933(1) and Article 2899(3) provide that this contract is deemed to have been made for indeterminate period of time. Assume in the above case the period of time for which the contract of lease is made is uncertain; in such cases, Easymoney can presume this contract to have been made for indeterminate period of time. The question is what will be the effect of that presumption? According to Article 2966, contracts of leases for an indeterminate periods of time can be terminated by giving default notice. To conclude, it can be said that contracts of lease is binding on the parties in whatever form and for however it is made. But is the effect on third parties depends on two factors:

Continue reading
  12489 Hits

አንዳንድ ጉዳዮች ስለ ሕገ-መንግሥት እና ፍርድ (ትርጉም)

 

 

 

መንደርደሪያ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የስራ ዘመን ከማለቁ በፊት ምርጫን ማከናወን እንደማይችል፤ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ካሳወቀ ጊዜ ጀምሮ፤ የጉዳዩ ሕገ መንግሥታዊ ገፅታዎች በተለያዩ መድረኮች ውይይት እየተደረገባቸው ነው። አራት አማራጭ መፍትሄዎች የቀረቡለት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ በጉዳዩ ላይ የሕገ መንግሥት ትርጉም፤ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጠይቋል። የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ፤ ጥያቄውን ተቀብሎ፤ የሕገ መንግሥት ምሁሮች አስተያየታቸውን በፅሁፍ እንዲያቀርቡ ጋብዟል። በቃልም እንዲያስረዱና ጥያቄዎችን እንዲያቀርቡ ጋብዟል።

የቀረበውን ግብዣ መሰረት በማድረግ አሰተያየት ለማቅረብ ውስኜ ነበር። በተለያዩ ምክንያቶች ሳላደርገው ቀርቻለሁ። አንደኛ፤ ግብዣው ለሕገ መንግሥት ምሁራኖች የቀረበ ጥሪ ነበር። ሁለተኛ፤ ጉባኤው የቀረበለትን አሰተያየት የመመልከት ግዴታ እንደሌለበት አስታውቋል። ሶስተኛ፤ በጊዜ እጥረት፤ በዛው ሳምንት የመጀመሪያ ልጄ ስለተወለደና በዚሁ ትኩረቴ ተይዞ የቆየ ስለነበረ። እንዲያም ሆኖ ግን በተለያዩ አጋጣሚዎች አንዳንድ አስተያየቶችን በማህበራዊ ሜዲያ ሳቀርብ ነበር። እነዚህን አስተያየቶቼን እንደሚከትለው አደራጅቼ አቅርቤያለሁ።

Continue reading
  7538 Hits

ወጣቱ ፎቶ አንሺ፣ ጃንሆይ እና ማርክስ

 

መምህሩ ወጣቱን ተማሪ ጠየቀው፤ “በየዓመቱ ይህን ፎቶ ታሳየኛለህ፣ ሁሌም አስተያየቴ አንድ ነው፣ አይረባም። ይህን ያህል ፎቶውን ለምን ወደድከው?”

ወጣቱ መለሰ፤ “ምክንያቱማ፤ ይህን የተፈጥሮ ገጽታ ለመፎተት በጣም ትልቅ ተራራ በእንፉቅቅ መውጣት ስለነበረብኝ ነው”።

 የመታደል ውጤት/ተጽእኖ

የተለያዩ ጥናቶችና ግንጥል-ታሪኮች (Anecdotes) እንደሚያሳዩት ሰዎች በእጃቸው ላለ ነገር የሚሰጡት ዋጋ/ቦታ/ግምት፣ ነገሩ ባይኖራቸው ኖሮ ከሚሰጡት ዋጋ ይበልጣል። ሰዎች የሚፈልጉትን ያውቃሉ፣ ፍላጎታቸው ደግሞ ሙሉ፣ ወጥ፣ እና ተሻጋሪ ነው ይሉናል የክላሲካል የምጣኔ ኃብት ምሁሮች፡፡ በእነሱ አባባል ለአንድ ነገር የምንሰጠው ዋጋ ተመሳሳይ ነው፣ ነገሩ በእጃችን ሲኖርና ሳይኖር፡፡ በዚህ ረገድ፣ በእጅ የያዙት ወርቅ ከመዳብ ይቆጠራል፣ በጉዋሮ ያለ ጸበል ልጥ መንከሪያ ይሆናል፣ ደብተራ ባገሩ አይከበርም፤ አወኩሽ ናኩሽ ከሚሉት ያገራችን አባባሎች ጋር ይጣረሳል፡፡ በእነዚህ አባባሎች መሠረት፣ በእጃችን ላለ ነገር የምንሰጠው ዋጋ ነገሩ ባይኖረን ከምንሰጠው ዋጋ ያንሳል። (የአገራችን አባባሎች መሰረታቸው ምንድን ነው? ነገሩ በእጃችን ከገባ በሁዋላ ለምንድን ነው የምንሰጠው ዋጋ የሚቀንሰው? ነገሩ እንደ ልባሽ/ያገለገለ ስለሚቆጠርና መልሰን ልንሸጠው ብንሞክር ስለሚቀንስ ነው? ነገሩ በገበያ የማይሸጥ ቢሆንስ? ስለነዚህ አባባሎች ለማውጋት አይደለም። እንዲህ አይነቱን አባባሎች ለማጣጣልም አይደለም። ምሳሌያዊ አባባሎች መቼና በምን ሁኔታዎች የውሳኔ ምክንያት ይሆናሉ፥ መቼ እንደ መሪና መካሪ መቁጠር አለብን ወይስ ወግ የማሳመሪያ ውብ አባባሎች (የቋንቋ ቀለማት) ብቻ ናቸው? ጊዜ ያለፈባቸው፥ ብስባሽ ቅሪቶች ናቸው? ይህን ለሌላ ጊዜ እናቆየው።) ለእነዚህ ምጣኔሃብት ምሁሮች ግን፣ ዋጋው ተመሳሳይ ነው፣ ወይም መበላለጥ የለበትም።

Continue reading
  11530 Hits

ወይኖን ግረፈው ኳሊ እንዲሰማህ፤ የወንጀል ኢኮኖሚክስ ክፍል ሁለት

 

1.  የመያዝና የመቀጣት እድል፤ ማጅራት መቺዎችን እና ቤት ሰርሳሪዎችን ከተማን በማጽዳት እንዋጋቸው ወይኖን ግረፈው ኳሊ እንዲሰማህ እና ሌሎችም አሳቦች

1.1 አጠቃላይ

ማስታወሻ ለአንባቢ፤ ይህ በወንጀል ኤኮኖሚክስ ዙሪያ የጻፍኩት ሁለተኛው ጽሑፌ ነው፡፡ የመጀመሪያውን ክፍል እዚህ ማግኘት ይቻላሉ:: አሳቦቼን ለማስረዳት ስል አንዳንዴ ተጓዳኝ ጉዳዮችን እያነሳው ባወራም፤ የዋናው ሃሳብ ፍሰት አይዛባም የሚል ዕምነት አለኝ፡፡

በመጀመሪያው የጽሑፉ ክፍል የተቀመጠው ቀመር ሌላኛው አካል የመያዝና የመቀጣት እድልን መጨመር ነው፡፡ ለማስታወስ ያህል ቀመሩ ይህ ነው፤

Continue reading
  12338 Hits

የወንጀልና ቅጣት ግሽበት፤ ቅጣት እንደ እንቁ እና ሌሎች ጉዳዮች ከወንጀል ኤኮኖሚክስ አንጻር ክፍል አንድ

 

ጠቅላላ

የዚህ ጽሑፍ ርዕስ ምንም እንኳ የወንጀል ኤኮኖሚክስ ቢልም፤ እንዲሁም ይህ ጽሑፍ የተጠቀመባቸው የጥናትና ምሁራዊ ጽሑፎች የኖቤል ሎሬት ጌሪ ቤከር የጀመረውና በሌሎች ምሁራን የዳበረው የጥናት ክፍል የወንጀል ኤኮኖሚክስ በመባል ቢጠራም፤ በጽሑፉ የሚነሱት ዋና ዋና ነጥቦች በአጠቃላይ በቅጣት ለማስፈጸም የሚሞከርን ሕግን ይመለከታል፡፡ በመሆኑም ወንጀል ባይሆንም በአስተዳደራዊም ሆነ በሌላ ዓይነት ቅጣት የሚፈጸም ሕግን በዚህ የጥናት ዘርፍ በዳበሩ አስተሳሰቦች አንጸር መገምገም እንችላለን፡፡

ግለሰቦች ሕግን ለማክበርና ላለማክበር ሲወስኑ ብዙ ነገሮችን ግምት ውስጥ ያስገባሉ፡፡ (ይህ አስተሳሰብ ግለሰቦች ሕግን ሲጥሱ አስበውበት ነው ከሚል ይነሳል፡፡ በእርግጥ በደመነፍስ ወይም ያለእውቀት የሚፈጸም የሕግ ጥሰቶች አሉ፡፡) እንደ ኤኮኖሚክስ ባለሙያዎች አባባል፤ ሕጉን በመጣስ የሚገኘው ጥቅም ሕጉን በመጣስ ከሚያስከትለው ቅጣት ካነሰ ግለሰቦች ሕጉን ያከብራሉ፡፡ የሚያስከትለው ቅጣት የተባለው በሕጉ ላይ የተቀመጠው ቅጣት አይደለም፡፡ ይልቅስ ዜጎች የሚያወዳድሩት በሕጉ ላይ የተቀመጠው ቅጣት ሲባዛ በመያዝና በመቀጣት እድል ነው፡፡ ትክክለኛው ቀመር ይህ ነው፤

ሕግ በመጣስ የሚገኘው ጥቅም    (በሕጉ የተቀመጠው ቅጣት X የመያዝና የመቀጣት እድል X ዲስካውንት ፋክተር) + ሕጉን ለመጣስ የሚወጣው ወጪ + (ኢመደበኛ ቅጣት X የመያዝና የመቀጣት እድል X ዲስካውንት ፋክተር)

Continue reading
  14174 Hits

እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል?  

 

ጥያቄው?

በዚህ ጽሁፍ መመለስ የምፈልገው ጥያቄ ቀላል ይመስላል፤ እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል የሚለውን ነው፡፡ ቀጥታ ጥያቄውን ወደ መመለሱ ከመሄዴ በፊት፤ ጥያቄው የሚመለከታቸው ሁኔታዎች ምን አይነቶቹን እንደሆነ ግልጽ ላድርግ፡፡

ያለ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ሲባል?

እንደሚታወቀው ንብረትን (የማይንቀሳቀስም ይሁን ልዩ ወይም ተራ የማይንቀሳቀስ) ለሌላ ሰው ውልን መሰረት አድርጎ ለማስተላለፍ የባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሰጥቷል ነገር ግን ፈቃዱ ሙሉ እና ነጻ አልነበረም የሚባለው የባለቤቱ ፈቃድ በስህተት ወይም በማታለል ወይም በሃይል ተግባር ምክኒያት የተሰጠና በሕጉም መሰረት ውሉ ፈራሽ ውል ሲባል ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን የገለጸው ራሱ ወይም በወኪሉ በኩል ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ሁኔታ የባለቤቱ ፈቃድ ጉድለት አለበት፤ ነገር ግን ንብረቱ ተላልፎ ሊሆን ይችላል ወይም የመብት ገደብ ተቋቁሞ ሊሆን ይችላልና እንዴት ባለቤቱ ንብረቱን ማስመለስ ገደቡን ማስነሳት ይችላል የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

ባለቤቱ በምንም አይነት መልኩ ፈቃዱን ሳይገልጽ ከሆነስ?

በሁለተኛ ደረጃ የንብረት ማስመለሱና የመብት ገደቡን የማስመለስ ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው ከመጀመሪያውኑ ባለቤቱ በምንም መልኩ ፈቃዱን ያልገለጸ ከሆነ ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሳይገልጽ እንዴት ንብረት ይተላለፋል ወይም መብት ይገደባል ለሚል ጥያቄ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሁኔታዎች መልስ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

1. አንድ ሰው ህጋዊ ባለቤት ሳይሆን ባለቤት እንደሆነ በማስመሰል ከሌላ ሰው ጋር በመዋዋል ንብረቱን ሊያስተላልፍ ወይም የመብት ገደብ ሊያቋቁም ይችላል፡፡ ንብረቱ ተራ የሚንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ይህን ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ ንበረቱ የማይንቀሳቀስ ወይም ልዩ ተንቀሳቃሽ ቢሆንም ይህን ለማደድረግ ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን ሰነዶችን ፎርጅድ ማድረግ ሊጠይቅ ወይም የሌላ አካል ትብብርን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እነዚህ ሰነዶች ይህ ሰው ባለቤት መሆኑን የሚያሳዩ ወይም ንብረቱን አስመልክቶ በባለቤቱ ስም ውል የመዋዋል ስልጣን አንዳለው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  19716 Hits

አላግባብ/በስህተት የተከፈለን የጡረታ አበል ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የሚያስቀረዉ የይርጋ ዘመን ምን ያህል ነዉ?

መግቢያ

የፌዴራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት በሰበር ችሎት ዉሳኔዎች ቅጽ 14 መግቢያ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፤ “ለተመሣሣይ ጉዳዮች በጣም የተራራቁ ዉሣኔዎችን በመስጠት ይታይ የነበረዉን ችግር በመቅረፍና የዉሣኔዎችን ተገማችነት በማረጋገጥ ረገድ የሰበር ዉሣኔዎች አስገዳጅ መሆን ከፍተኛ ዉጤት አስገኝቷል ማለት ይቻላል፡፡ አልፎ አልፎ በዉሣኔዎች ጥራትና ስርጭት ሊታዩ የሚችሉ ችግሮች ሥርዓቱ እየተጠናከረ ሲሄድ የሚፈቱ ሲሆን አነዚህን ችግሮች ለማቃለል እኛም ጥረት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ጥረታችን ሊሳካ የሚችለዉ በዉሣኔዎቹ ላይ በሕግ ምሁራንና ባለሙያዎች ገንቢ የሆኑ ትችቶችና አስተያየቶች ሲቀርቡ ነዉ”፡፡ እኔም ይህን ግብዣ በመቀበል የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት ሕዳር 21 ቀን 2005 ዓ.ም. በሰጠዉ ዉሳኔ ላይ ትችቴን ከዚህ በመቀጠል አቀርባለሁ፡፡ ዉሳኔዉ የተሰጠዉ በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ እና ታዬ አበራ መካከል ባለዉ ክርክር በሰበር መዝገብ ቁጥር 72341 ነዉ፡፡ በዚህ መዝገብ ከተነሱት ዋነኛ ጉዳዮች ዉስጥ፤ አላግባብ የተከፈለ ጡረታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይ፤ ከታገደስ የይርጋ ዘመኑ ምን ያህል ነዉ የሚሉት ይገኙበታል፡፡

የጉዳዩ መነሻ

አቶ ታዬ አበራ ከግንቦት 01 ቀን 1984 ዓ.ም. ጀምሮ በየወሩ የጡረታ አበል ይወስዱ ነበር፡፡ ከሰኔ 01 ቀን 1989 ዓ.ም. ጀምሮ ደግሞ በመንግስት መስሪያ ቤት ተቀጥረዉ ደመዎዝ ተከፍሏቸዋል፡፡ አቶ ታዬ የጡረታ አበላቸዉን መዉሰዳቸዉንም እንደቀጠሉበት ነዉ፡፡ የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 209/1955 አንቀጽ 30(2) እና በመንግስት ሰራተኞች ጡረታ አዋጅ ቁጥር 345/1995 አንቀጽ 46(1) መሰረት፡ የአገልግሎት የጡረታ አበል በመቀበል ላይ ያለ ባለመብት እንደገና በመንግስት መሥሪያ ቤት ተቀጥሮ ደመዎዝ ማግኘት ከጀመረ አበሉ ይቋረጣል፡፡ በመሆኑም በማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ የተጠየቀዉ ዳኝነት እነዚህን ያጠቃልላል፡፡ 1) ከሰኔ 01 ቀን 1989 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 1995 ዓ.ም. ድረስ በየወሩ ብር 105.00 የወሰዱት ለሰባ አምስት ወራት ያህል ተባዝቶ የሚመጣዉን ዉጤት ብር 7575.00፤ 2) ከሐምሌ 01 ቀን 1996 ዓ.ም. እስከ ሀምሌ 01 ቀን 1998 ድረስ በየወሩ ብር 115.50 የወሰዱት ታስቦ የሚመጣዉን ድምር ብር 4045.50፤ 3) ወጪና ኪሳራ እንዲሁም ከሕጋዊ ወለዱ ጋር እንዲከፍሉ፡፡ የማኅበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ለመጀመሪያ ጊዜ ክስ የተመሰረተዉ በጥቅምት 18 ቀን 2003 ዓ.ም. ነዉ፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዉሳኔ

Continue reading
  9201 Hits

ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል?

መግቢያ

ይህ አጭር ጽሁፍ በቅርብ ጊዜ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰበር መዝገብ ቁጥር 76248 ላይ፤ በኦሮሚያ ጠቅላይና በአዳማ ልዮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተሰርቷል ማለት አይቻልም በሚል፤ በሶስት ዳኞች ጥቅምት 6 2005 የተዘጋን ጉዳይ መሰረት አደርጎ የቀረበ ነዉ፡፡ የምንዳስሰዉ ጥያቄ በጽሁፉ ርእስ ላይ የተመለከተዉን ነዉ፤ ያለዉክልና የሌላን ሰዉ እዳ መክፈል ይርጋን ያቋርጣል? ለጽሁፉ አላማ የተከራካሪ ወገኖችን ስም መጥቀስ አስፈላጊ ስላልሆነ አበዳሪ፤ ከሳሽ፤ ተበዳሪ፤ እና የተበዳሪ ልጅ የሚሉትን እንጠቀማለን፡፡ በአጭሩ ፍርድ ቤቶቹ የወሰኑት ባለእዳዉ ሳይሆን ሌላ ሰዉ (የጽሁፍ ዉክልና ሳይሰጠዉ በፊት) በባለእዳዉ ስም ያደረገዉ የእዳ አከፋፈል እንዳልተደረገ ስለሚቆጠር ይርጋን አያቋርጥም በማለት ወስነዋል፡፡

የጉዳዩ መነሻ

ተበዳሪዋ ከኢትዮጲያ ንግድ ባንክ አዳማ ቅርንጫፍ ለንግድ ማስፋፊያ በሚልና ንብረት በማስያዝ በየወሩ ተከፍሎ በአንድ አመት ዉስጥ የሚያልቅ ብድር ወስደዋል፡፡ ነገር ግን አንድም ወር የተስማሙትን ወርሀዊ ክፍያ ሳይፈጽሙ በብድር ዉሉ ላይ የተጠቀሰዉ የእዳ መክፈያ ጊዜ ያልፋል፡፡ የብድር ዉሉ የተፈረመዉ በ25/11/1987 ሲሆን በ24/11/1988 ተከፍሎ ማለቅ ነበረበት፡፡ የተበዳሪዋ ልጅ የመጀመሪያዉን የ28000 ብር ክፍያ በተበዳሪዋ ስም የፈጸሙት በ24/11/1989 ነበር፡፡ ከዛ በመቀጠል በ15/8/1994 በዚሁ ልጅ በተዳሪዋ ስም የ2000 ብር ክፍያ ተፈጽሟል፡፡ ክሱ በቀረበበት ወቅት ከመጀመያዉ ክፍያ ጀምሮ ሲሰላ ከአስር አመት በላይ አልፎታል፡፡ ነገር ግን ከሁለተኛዉ ክፍያ ጀምሮ ከተሰላ አስር አመት አልሞላም፡፡

ተበዳሪዋ ለቀረበባቸዉ ክስ የይርጋ መቃወሚያ አንስተዋል፤ ክሱ በአስር አመት የይርጋ ጊዜ ዉስጥ ስላልቀረበ ይታገዳል በሚል፡፡ ሁለተኛዉን ክፍያ በተመለከተ፤ አልከፈልኩም በክፍያ ሰነዱም ላይ ያለዉ ፊርማ የኔ ፊርማ አይደለም ብለዋል፡፡ ይህንን እኔ ያልከፈልኩትን የሁለተኛ ክፍያ ሰነድ ያቀረበዉ ከሳሽ በይርጋ ቀሪ የሆነዉን የብድር ገንዘብ በፍርድ ቤት ክስ መስርቶ ለማስመለስ እንዲያመቸዉ ነዉ የሚል ነዉ፡፡  

Continue reading
  9882 Hits

On the power of the federal government to develop and enforce criminal laws: Part 2

In the previous post, I argued that legal form cannot and should not be used to allocate governmental powers and responsibilities between the federal government on the one hand and constituent units of the federation, i.e., regional states, on the other. On such basis I argued that criminal law as a form of law cannot be said to belong to the federal or regional level of government. Hence, I have cautioned against the literal and independent reading of article 55(5) of the constitution which says that the House of Peoples’ Representatives shall enact a criminal code and regional states shall enact criminal law on matters not covered by the federal criminal legislation.

I submitted that this constitutional provision should be read in light of Article 51 which deals with the powers and responsibilities of the federal government. Accordingly the federal government can pass any kind of law, including criminal law, on matters which fall under the jurisdiction of the federal government. Such matters are provided in Article 51. It is, therefore, the duty of the federal government to demonstrate that the criminal laws it has passed or plans to pass are relating to matters falling under one or more of the twenty-one items in Article 51 and other parts of the constitution. Regional states, on the other hand, can pass criminal legislation on matters which are outside the federal jurisdiction.

I finished the last post by posing a question. Regarding forestry offences, for example, can regional states provide for a higher penalty than what is provided in the federal law for the same offence? I will add another question here and address the two together: can regional states expand or contract the scope of federal offences relating to forestry?

As I have said, if we read Article 55 of the constitution literally and independent of Article 51, we ask a simple question: is the offence provided in the federal criminal legislation? If the answer is yes, then it follows that a given regional state can neither provide for a higher penalty nor expand and contract the definition of the relevant forestry offence. But I have suggested against this rather simplistic reading of the relevant constitutional provisions.

In my view, in order to answer the above question, we must first determine the respective roles of the federal government regarding management of forest resources? Does the federal government have exclusive power over the management of our forest resources? If the answer to this question were yes, then it follows that the federal government would have the exclusive power to develop and enforce forest laws, including criminal laws relating to forestry. But the constitutional reality is different.

Continue reading
  16011 Hits