The blogger is a master's student in Social Work at the University of Addis Ababa He graduated in Law (LLB) from Mekelle University in 2007 and worked as a Public Prosecutor from 2008 to 2009 he is working as a Legal Expert in FDRE Justice Organs Professionals Training Center. 

ስለ እንደራሴ (ውክልና) ሕግ አንዳንድ ነጥቦች

ውክልናን የተመለከተው ሕግ በአገራችን በብዛት ስራ ላይ ከሚውሉ የሕግ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የፍትህብሄር ሕግ ቁጥር 2199 ውክልናን እንደተረጐመው “ውክልና ማለት ተወካይ የተባለ አንድ ሰው ወካይ ለተባለው ሰው እንደራሴ ሆኖ አንድ ወይም ብዙ ህጋዊ ሥራዎች በወካዩ ሥም ለማከናወን ግዴታ የሚገባበት ውል ማለት ነው” ይላል፡፡ ከትርጉሙ ለመረዳት እንደምንችለው ውክልና የሚደረገው በወካይና በተወካይ መካከል ሲሆን በውክልናው የሚከናወኑት ስራዎች ህጋዊ መሆን አንዳለባቸው ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ህጋዊ ባልሆኑ ነገሮች ላይ የሚደረግ ውክልና ተቀባይነት የለውም  ማለት ነው፡፡ በሰፊው ስንመለከት ሁለት አይነት ውክልናዎችን እናገኛለን፡፡ እነሱም በፍተሃብሄር ሕግ ቁጥር 2189 ላይ የተቀመጠው ፍፁም የሆነ እንደራሴነት /disclosed or complete  agency/ እና በዚሁ ሕግ ቁጥር 2197 ላይ የተቀመጠው እንደራሴው በራሱ ስም ተግባሮችን የሚፈፅምባቸው የውክልና አይነት/undisclosed agency/ ናቸው:: ለዚህ ፅሁፍ አላማ ግን  የመጀመሪያው አይነት ውክልና ማለትም ፍፁም የሆነውን የእንደራሴነት አይነት እንመለከታለን፡፡ ይህም በፍትሃብሄር ህጉ ቁጥር 2199-2233 ድረስ ያሉትን የህጉን አንቀጾች የተመለከተ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ ፅሁፍ ውስጥየውክልና አስፈላጊነት፣ የውክልና ምንጮች ፣ የውክልና አመሰራረት፣ የውክልና አይነቶች፣ የውክልና ግብ ፣ የተወካይና የወካይ ግዴታዎች፣ ውክልና የሚቋረጥበት ሁኔታ፣ ከውክልና መመሰረት ጀምሮ በውክልና አማካኝነት የሚከናወኑ ተግባሮችና ውጤቶቻቸው ድረስ ወካይ፣ ተወካይና የውክልና ማስረጃውን የሚሰጡ አካሎች ሊያደርጓቸው የሚገባቸው ጥንቃቄዎች የሚዳሰሱ ይሆናል፡፡

  31880 Hits
Tags: