Copyright Protection in Ethiopia Shining Law, Zero Effect

The idea of enacting a copyright law was first developed to encourage creativity and further grew on that sole purpose and protecting companies’ and individuals’ right to ownership.  Such protections of copyright is expressed by giving the author or the owner of copyrightable works the exclusive right of reproduction, sale, rent, transfer, and other communication of the work to the public.

According to David Bainbridge, a well-known writer on Intellectual Property, copyright means an intangible, incorporeal property right granted by the law to the owner of the specified types of literary and artistic works such as films and sound recordings. Furthermore, copyright protection subsists in original works of authorship fixed in any tangible medium of expression. In no case does copyright protection for an original work of authorship extend to any idea, procedure, process, and system, method of operation, concept, principle, or discovery.

One important feature of copyright law is that it does not protect ideas, rather protects the expression of an idea.

However, protecting the interest of the owner of the copyrightable work is not the only purpose of the copyright law. Copyright law has to also take in to account the interest of the society at large.

The protection given by the law to the owner of the copyright, in recognition of the time and effort taken to create the work, ensures a fair balance between the needs of the copyright user and the rights of the copyright owner. People need to be able to copy materials produced by others, but if there were no limits in place, the owners of the copyright material would not be remunerated for their work, and there would be no incentive to create further work.

Continue reading
  15224 Hits
Tags:

"ድፍረት" ፊልም - የቅጅ መብት ጥበቃ ለታሪካዊ እውነታ ወይስ ለአእምሮ ፈጠራ?

በአእምሯዊ ንብረት ማዕቀፍ ተካተው በህግ ጥበቃ ከሚደረግላቸው ኢ-ቁሳዊ የንብረት ባለቤትነት መብቶች መካከል የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንሰ ሃሳብ ውልደት የኃልዮሽ ተጉዞ በታሪክ ተጠቃሽ ወደ ሆነውና  ከታላቋ ብሪታንያ ተነስቶ ወደ ሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ ወደ ተስፋፋው የኢንዲስትሪ አብዮት ይወስደናል፡፡ የዚህ ዘመን ካፈራቸው እውቅ ሳይንቲስቶች መካከል አንዱ በሆነው ጆን ጉተንበርግ የተፈጠረው የህትመት ማሽን ለቅጅ መብት ጥያቄ መጠንሰስ ምክንያት በመሆን የኋላ የኋላም በወቅቱ የብሪታንያ ንግስት በነበሩት ንግስት አን ስም ለተሰየመው የአን ስታቲዩት (Anne Statute) ተብሎ ለሚታወቀው የህግ ማዕቀፍ እ.ኤ.አ በ1710 ዓ.ም መደንገግ ምክንያት ሆኗል፡፡ የህትመት ማሽኑ መፈጠር በወቅቱ በነበሩ ደራስያን የሚጻፉ መጽሃፍት በፍጥነት እየተባዙ ወደ አንባቢዎች እጅ እንዲደርሱ በማድረግ ከአሳታሚዎች ፍቃድ ውጪ የሚታተሙ መጽሃፍት እየበዙ እንዲመጡ አስገድዷል፡፡ ይህም በአሳታሚዎች ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያደረሰ በመምጣቱ በወቅቱ በተሰሚነት እና በገንዘብ አቅም ገናና የነበሩት አሳታሚዎች መንግስት ለመብታቸው መከበር ህጋዊ ሽፋን ይሰጣቸው ዘንድ መወትወታቸውን ተከትሎ ነበር የአን ስታቲዩት (Anne Statute) በሀገረ እንግሊዝ ሊታወጅ የቻለው፡፡

በዚህ መልኩ ወጥ የሆነ የህግ ማዕቀፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ወጥቶለት በሀገረ እንግሊዝ የተጀመረው የቅጅ መብት ጥበቃ በጎረቤት የአውሮፓ ሀገራት እየተስፋፋ የመጣውን የመጻሃፍት ህትመት እና ስርጭት ተከትሎ ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ የህግ ከለላዎችን መሻቱ አልቀረም፡፡ በዚህም ሳቢያ ዓለም ዓቀፍ የቅጅ መብት ስምምነቶች አስፈላጊነት አሳማኝ እየሆነ በመምጣቱ ሀገራት በዜጎቻቸው የሚሰሩ የፈጠራ ስራዎች በሌሎች ሀገራት ውስጥ የህግ ከለላ እንዲያገኙ የሚያስችሉ ስምምነቶችን በመፈራረም በድንበር ተወስኖ የነበረው የህግ ከለላ ዓለም ዓቀፋዊ ይዘት እንዲይዝ አድርገዋል፡፡ በዘርፉ ከተደረጉ ስምምነቶች መካከልም የበርን ስነጽሁፍ እና ኪነ ጥበብ ስራዎች ጥበቃ ዓለም ዓቀፍ ስምምነት እና ዩኒቨርሳል የቅጅ መብት ኮንቬንሽን በቀደምትነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከፍ ሲል በጥቅሉ በተገለጸው መልኩ እየተስፋፋ የመጣው የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንስ ሃሳብ እየጎለበተ እና እየዳበረ መጥቶ በኪነ-ጥበብ እና በስነ-ጥበብ ዘርፍ ከስራ አመንጪዎች ጋር ተጓዳኝ ተሳትፎ ላላቸው እንደ ከዋኝ፣ የድምጽ ሪከርዲንግ ፕሮዲውሰሮች እና የብሮድካስት ተቋማት የተዛማጅ መብቶች ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ የዛሬውን የተሟላ የህግ ጥበቃ ስርዓት መልክ ለመያዝ በቅቷል፡፡

ሀገራችንም በ1957ቱ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ እና በ1960 ዓ.ም በደነገገችው የፍትሐብሔር ህግ የቅጅ መብት ጥበቃን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በማካተት የፈጠራ ስራ አመንጪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የህግ ከለላ እንዲኖራቸው ማድረግ ችላለች፡፡ ሆኖም የእነዚህ ህጎች ወሰንም ሆነ አተገባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ በአይነት እና በይዘት እየጨመረ የመጣውን የፈጠራ ስራዎች ግብይት ሊመጥኑ የሚችሉ ባለመሆናቸው በ1996 ዓ.ም የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ ቁ. 410/96 ን በመደንገግ ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች፡፡

የዚህ ጽሁፍ ዋነኛ ዳሰሳ የቅጅ መብት ጥበቃ ለታሪካዊ እውነታ ወይስ ለአእምሮ ፈጠራ? የሚለውን ርዕሰ ጉዳይ በአሁን ወቅት በስራ ላይ በሚገኘው የሀገራችን የህግ ማዕቀፍም ሆነ በዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች ተቀባይነት ባገኙ ዓለም ዐቀፋዊ መርሆች እይታ መቃኘት ነውና የቅጅን መብት ጥበቃ አጀማመር ታሪካዊ ዳራ በዚህ መልኩ ከጠቆምኩ ወደዚሁ አንኳር ነጥብ ላምራ፡፡ መግቢያዬ ላይ እንደጠቆምኩት የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንሰ ሃሳብ የጀመረው ለአእምሮ ፈጠራ ውጤት ለሆኑ የስነ ጽሁፍ ስራዎች ጥበቃ በመስጠት ነው፡፡ ለእነዚህ የፈጠራ ስራዎች ጥበቃ ለማድረግ የተደነገጉ የህግ ማዕቀፎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ መጥተው ሌሎች በኪነ ጥበብ፣ በስነ ጥበብ እና በሳይንሳዊ መስክ የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች የጥበቃው አካል እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡ በሀገራችን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ አንቀጽ 2(30) ስር እንደተደነገገው በአዋጁ ጥበቃ የሚያገኙ ስራዎች እንደ መጽሃፍ፣ ቡክሌት፣ መጣጥፍ፣ ንግግር፣ ሌክቸር፣ ለአንድ ለተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል የሚደረግ መልዕክት አዘል ንግግር፣ የሃይማኖት ስብከት እና በይዘት ደረጃ ሌላ በቃል የቀረበ ስራ፣ ድራማ፣ ድራማዊ የሙዚቃ ስራ፣ በእንቅስቃሴ ብቻ የሚቀርብ ድራማ /ፓንቶምይምስ/፣ የመድረክ ውዝዋዜ፣ የሙዚቃ ስራ፣ ኦድዮቪዥዋል ስራ፣ የፎቶግራፍ ስራ፣ የስዕል ስራ፣ ካርታ፣ ፕላን፣ ስዕላዊ መግለጫ፣ የንድፍ ስራ እንዲሁም የጥልፍና የፊደል ቅርጽ ስራዎች፣ ኪነ - ህንጻ፣ የሀውልት፣ የቅርጻ ቅርጽ እና የኮምፒውተር ፕሮግራሞችን እና የመሳሰሉትን ያካትታል፡፡ ከዚህ የህግ ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የምንችለው የቅጅ መብት ባለቤት ለመሆን በመጀመሪያ ደረጃ ከላይ ከተዘረዘሩ ወይም መሰል ስራዎች መካከል የአንዱ ባለቤት መሆን የግድ ይሆናል፡፡ በቅጅ መብት ጥበቃ ዘርፍ የመጀመሪያ ሰፊ ተቀባይነት ባገኘው የበርን የስነ ጽሁፍ እና የኪነጥበብ ስራዎች ጥበቃ ዓለም ዓቀፍ ስምምነት አንቀጽ 2 ላይም በግልጽ እንደተመላከተው የስምምነቱ አባል ሀገራት የቅጅ መብት ጥበቃ እንዲሰጡ የሚገደዱት ከላይ በተዘረዘሩት የስራ ዘርፎች አስቀድሞ የተሰራ ስራ ሲኖር ብቻ ነው፡፡

Continue reading
  11334 Hits
Tags: