Can You Sue Coca Cola for Using Your Name?

Back Ground of the Law

In these days, it is in our usual venture to see many Ethiopian names on the bottles of Coca Cola thanks to the fanciful marketing strategy of Coca Cola Company. Coca Cola used this strategy to promote its product or I can say to instigate its customers, hence each name affixed on each bottle is believed to have a power to call an individual, whose name is affixed thereon, to the market. As it is described in some Medias, the company has used around 200 names, which are familiar to Ethiopia, to adopt this marketing campaign.

Despite of my full appreciation of this marketing strategy, I tend to see the act of the company in the eyes of the law just to lay down some legal remarks. The theme of my discussion will focus on the dictation of the law towards "The Right to Own Name and The Right to Use Name". The specific law that deals with the issue we have at hand is our Civil Code which is fully titled as Civil Code of The Empire of Ethiopia Proclamation No. 165 of 1960. It is the first section of the Code that deals with the attribution of personality with specific provisions vested to regulate issues embarking from the birth and/or conception until the death of a natural person. Under this section, the law has laid a specific chapter that deals with names of a natural person pertaining to the acquisition and usage of a name.

When we tend to the first point of our discussion, i.e. "the right to own name", we will find out sub-Article 1 of Article 32 of the Civil Code which puts the principle towards the right of a natural person to "own name" by stating as follows;

"Every individual has a family name, one or more first name and a patronymic."  

Continue reading
  9379 Hits

"ድፍረት" ፊልም - የቅጅ መብት ጥበቃ ለታሪካዊ እውነታ ወይስ ለአእምሮ ፈጠራ?

በአእምሯዊ ንብረት ማዕቀፍ ተካተው በህግ ጥበቃ ከሚደረግላቸው ኢ-ቁሳዊ የንብረት ባለቤትነት መብቶች መካከል የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንሰ ሃሳብ ውልደት የኃልዮሽ ተጉዞ በታሪክ ተጠቃሽ ወደ ሆነውና  ከታላቋ ብሪታንያ ተነስቶ ወደ ሌሎች የምዕራብ አውሮፓ ሀገራት እና ሰሜን አሜሪካ ወደ ተስፋፋው የኢንዲስትሪ አብዮት ይወስደናል፡፡ የዚህ ዘመን ካፈራቸው እውቅ ሳይንቲስቶች መካከል አንዱ በሆነው ጆን ጉተንበርግ የተፈጠረው የህትመት ማሽን ለቅጅ መብት ጥያቄ መጠንሰስ ምክንያት በመሆን የኋላ የኋላም በወቅቱ የብሪታንያ ንግስት በነበሩት ንግስት አን ስም ለተሰየመው የአን ስታቲዩት (Anne Statute) ተብሎ ለሚታወቀው የህግ ማዕቀፍ እ.ኤ.አ በ1710 ዓ.ም መደንገግ ምክንያት ሆኗል፡፡ የህትመት ማሽኑ መፈጠር በወቅቱ በነበሩ ደራስያን የሚጻፉ መጽሃፍት በፍጥነት እየተባዙ ወደ አንባቢዎች እጅ እንዲደርሱ በማድረግ ከአሳታሚዎች ፍቃድ ውጪ የሚታተሙ መጽሃፍት እየበዙ እንዲመጡ አስገድዷል፡፡ ይህም በአሳታሚዎች ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እያደረሰ በመምጣቱ በወቅቱ በተሰሚነት እና በገንዘብ አቅም ገናና የነበሩት አሳታሚዎች መንግስት ለመብታቸው መከበር ህጋዊ ሽፋን ይሰጣቸው ዘንድ መወትወታቸውን ተከትሎ ነበር የአን ስታቲዩት (Anne Statute) በሀገረ እንግሊዝ ሊታወጅ የቻለው፡፡

በዚህ መልኩ ወጥ የሆነ የህግ ማዕቀፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ወጥቶለት በሀገረ እንግሊዝ የተጀመረው የቅጅ መብት ጥበቃ በጎረቤት የአውሮፓ ሀገራት እየተስፋፋ የመጣውን የመጻሃፍት ህትመት እና ስርጭት ተከትሎ ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ የህግ ከለላዎችን መሻቱ አልቀረም፡፡ በዚህም ሳቢያ ዓለም ዓቀፍ የቅጅ መብት ስምምነቶች አስፈላጊነት አሳማኝ እየሆነ በመምጣቱ ሀገራት በዜጎቻቸው የሚሰሩ የፈጠራ ስራዎች በሌሎች ሀገራት ውስጥ የህግ ከለላ እንዲያገኙ የሚያስችሉ ስምምነቶችን በመፈራረም በድንበር ተወስኖ የነበረው የህግ ከለላ ዓለም ዓቀፋዊ ይዘት እንዲይዝ አድርገዋል፡፡ በዘርፉ ከተደረጉ ስምምነቶች መካከልም የበርን ስነጽሁፍ እና ኪነ ጥበብ ስራዎች ጥበቃ ዓለም ዓቀፍ ስምምነት እና ዩኒቨርሳል የቅጅ መብት ኮንቬንሽን በቀደምትነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከፍ ሲል በጥቅሉ በተገለጸው መልኩ እየተስፋፋ የመጣው የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንስ ሃሳብ እየጎለበተ እና እየዳበረ መጥቶ በኪነ-ጥበብ እና በስነ-ጥበብ ዘርፍ ከስራ አመንጪዎች ጋር ተጓዳኝ ተሳትፎ ላላቸው እንደ ከዋኝ፣ የድምጽ ሪከርዲንግ ፕሮዲውሰሮች እና የብሮድካስት ተቋማት የተዛማጅ መብቶች ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ የዛሬውን የተሟላ የህግ ጥበቃ ስርዓት መልክ ለመያዝ በቅቷል፡፡

ሀገራችንም በ1957ቱ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ እና በ1960 ዓ.ም በደነገገችው የፍትሐብሔር ህግ የቅጅ መብት ጥበቃን የሚመለከቱ ድንጋጌዎች በማካተት የፈጠራ ስራ አመንጪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የህግ ከለላ እንዲኖራቸው ማድረግ ችላለች፡፡ ሆኖም የእነዚህ ህጎች ወሰንም ሆነ አተገባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ በአይነት እና በይዘት እየጨመረ የመጣውን የፈጠራ ስራዎች ግብይት ሊመጥኑ የሚችሉ ባለመሆናቸው በ1996 ዓ.ም የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ ቁ. 410/96 ን በመደንገግ ተግባራዊ እያደረገች ትገኛለች፡፡

የዚህ ጽሁፍ ዋነኛ ዳሰሳ የቅጅ መብት ጥበቃ ለታሪካዊ እውነታ ወይስ ለአእምሮ ፈጠራ? የሚለውን ርዕሰ ጉዳይ በአሁን ወቅት በስራ ላይ በሚገኘው የሀገራችን የህግ ማዕቀፍም ሆነ በዓለም ዓቀፍ ስምምነቶች ተቀባይነት ባገኙ ዓለም ዐቀፋዊ መርሆች እይታ መቃኘት ነውና የቅጅን መብት ጥበቃ አጀማመር ታሪካዊ ዳራ በዚህ መልኩ ከጠቆምኩ ወደዚሁ አንኳር ነጥብ ላምራ፡፡ መግቢያዬ ላይ እንደጠቆምኩት የቅጅ መብት ጥበቃ ጽንሰ ሃሳብ የጀመረው ለአእምሮ ፈጠራ ውጤት ለሆኑ የስነ ጽሁፍ ስራዎች ጥበቃ በመስጠት ነው፡፡ ለእነዚህ የፈጠራ ስራዎች ጥበቃ ለማድረግ የተደነገጉ የህግ ማዕቀፎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻሉ መጥተው ሌሎች በኪነ ጥበብ፣ በስነ ጥበብ እና በሳይንሳዊ መስክ የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች የጥበቃው አካል እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡ በሀገራችን የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ አንቀጽ 2(30) ስር እንደተደነገገው በአዋጁ ጥበቃ የሚያገኙ ስራዎች እንደ መጽሃፍ፣ ቡክሌት፣ መጣጥፍ፣ ንግግር፣ ሌክቸር፣ ለአንድ ለተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል የሚደረግ መልዕክት አዘል ንግግር፣ የሃይማኖት ስብከት እና በይዘት ደረጃ ሌላ በቃል የቀረበ ስራ፣ ድራማ፣ ድራማዊ የሙዚቃ ስራ፣ በእንቅስቃሴ ብቻ የሚቀርብ ድራማ /ፓንቶምይምስ/፣ የመድረክ ውዝዋዜ፣ የሙዚቃ ስራ፣ ኦድዮቪዥዋል ስራ፣ የፎቶግራፍ ስራ፣ የስዕል ስራ፣ ካርታ፣ ፕላን፣ ስዕላዊ መግለጫ፣ የንድፍ ስራ እንዲሁም የጥልፍና የፊደል ቅርጽ ስራዎች፣ ኪነ - ህንጻ፣ የሀውልት፣ የቅርጻ ቅርጽ እና የኮምፒውተር ፕሮግራሞችን እና የመሳሰሉትን ያካትታል፡፡ ከዚህ የህግ ድንጋጌ በግልጽ መረዳት የምንችለው የቅጅ መብት ባለቤት ለመሆን በመጀመሪያ ደረጃ ከላይ ከተዘረዘሩ ወይም መሰል ስራዎች መካከል የአንዱ ባለቤት መሆን የግድ ይሆናል፡፡ በቅጅ መብት ጥበቃ ዘርፍ የመጀመሪያ ሰፊ ተቀባይነት ባገኘው የበርን የስነ ጽሁፍ እና የኪነጥበብ ስራዎች ጥበቃ ዓለም ዓቀፍ ስምምነት አንቀጽ 2 ላይም በግልጽ እንደተመላከተው የስምምነቱ አባል ሀገራት የቅጅ መብት ጥበቃ እንዲሰጡ የሚገደዱት ከላይ በተዘረዘሩት የስራ ዘርፎች አስቀድሞ የተሰራ ስራ ሲኖር ብቻ ነው፡፡

Continue reading
  9130 Hits
Tags: