The blogger (LLM in Business and Corporate) is a Lecturer at the University of Gondar, School of law. 

የኑሮ ውድነት እና የሸማቾች መብት ጥበቃ በኢትዮጵያ ሕግ

በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 51 እና 55 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የፌደራል መንግሥቱ የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት እንደ ኢትዮጵያዊያን አቆጣጠር 2006 ዓ.ም የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃን በአንድ የሚመራ የሕግ ማዕቀፍ ያዘጋጀ ሲሆን የዚህ ሕግ አላማ ተደርገው በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መግቢያ ላይ ከተቀመጡ ነገሮች አንዱ እና ዋነኛው ነገር ለሸማቹ ማህበረሰብ ጤናማ የሆነ የግብይት ሥርዓት መዘርጋት እና ከአወጣው ገንዘብ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የንግድ እቃ ወይም አገልገሎት እንዲያገኝ ማስቻል ነው። ይህን ጠቅላላ አላማም በአዋጁ ውስጣዊ ክፍሎች በተካተቱ በርካታ የሸማቾች መብቶች እና የንግዱ ማህበረሰብ ግዴታዎች ድንጋጌ ተደራሽ ለማድረግ ተሞክሯል።

  12585 Hits

የንግድ እቃን ማከማቸት፣ መደበቅ፣ ዋጋ ጨምሮ መሸጥ እና የኮረና ወረርሽኝ ከኢትዮጵያ ሕግ አንፃር

በአገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወረርሽኝ ሲከሰት የሰዎች ህይወትን ከመቅሰፉ በተጨማሪ የንግድ እንቅስቃሴዎችንም አደጋ ላይ ይጥላል። ንግድ የተሳለጠ እና ለሁሉ ተደራሽ የሚሆነው የተረጋጋ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብር ሲኖር ብቻ ነው። በንግድ ዓለም ውስጥ የነጋዴዎች ዋነኛ ግብ ተደርጎ የሚወሰደው በአጭር ጊዜ ወይም በረጅም ጊዜ ውስጥ ትርፋማ መሆን ነው። ነገር ግን ይህ ትርፋመነታቸውን የሚያሳኩት ሕግ እና ሥርዓትን በአከበረ መንገድ በሚደረግ እንቅስቃሴ ሊሆን ይገባል። ከሕግ እና ሥርዓት ውጭ ትርፍ ለማጋበስ የሚንቀሳቀስ ነጋዴ የተመሰረተበት አላማ ማትረፍ ስለሆነ በሚል ተልካሻ ምክንያት ዝም ተብሎ ሊታለፍ አይገባም። ይህንም መሰረት ለማስያዝ ሕግ እና ሥርዓት አስፈፃሚ አካላት ትልቅ ድርሻ አላቸው። ትርፍ ለማግኘት ከሚደረጉ ጥረቶች ጎን ለጎን ማህበራዊ ሀላፊነትን መወጣትንም መዘንጋት አይገባም። የነጋዴዎች ትርፍን ለማሳደግ የሚያርጉት እሩጫ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር ከተቋቋመ አካል ጋር በጥብቅ ከሚካረሩባቸው ወቅቶች አንዱ ወረርሺኝ የሚከሰትበት ወቅት ነው። ወረርሽኝ በሚከሰትበት ወቅት ሁሉም ከወረርሽኙ ለመዳን በሚያደርገው እሩጫ ወቅቱ የሚፈልጋቸው እቃዎች እና አገልግሎቶች እጥረት ሊከሰት ይችላል።

  10377 Hits