"በሕግ አግባብ"ያለአግባብ ስለመታሰር

 

ካሳ አልባ የፍትሕ ሥርዓቱ ተጎጂዎች

እንዲያው አያድርገውና በወንጀል ተጠርጥረው ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆብዎ አስቸጋሪውን የወንጀል ምርመራ ተቋቁመው ካለፉ በኋላ በዓቃቤ ሕግ ተከሰው የዋስትና መብትዎን ተከልክለው ክራሞትዎ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሆነ እንበል፤ በሕግ ጥላ ሥር፡፡

የፍርድ ቤት ቀጠሮዎት በደረሰ ጊዜ እጅዎ በካቴና ተጠፍንጎ ወይም ከሌላ እስረኛ ጋር ተቆራኝቶ ጠመንጃ በወደሩ ፖሊሶች በአይነ ቁራኛ እየተጠበቁ ለወራት ወይም ለዓመታት ነጻነትዎ ተነፍጎ የፍርድ ሂደቱን ሲከታተሉና ሲሟገቱ ከባጁ በኋላ በመጨረሻ ጉዳይዎትን ይመለከት የነበረው ዳኛ የችሎቱን ጠረጴዛ በመዶሻው ግው! በማድረግ ‹‹ከተከሰሱበት ወንጀል በነፃ ተሰናብተዋል ቅንጣት ያህል ጥፋት የለብዎትም›› ብሎ ቢያሰናብትዎ ምን ይሰማዎታል???

እርግጥ ነው፣ ተሟግተው በማሸነፍዎና ንጹህነትዎን በማስመስከርዎ አልያም የእሥር ህይዎትዎ በማክተሙና ፀሐይቱን ያለ አንዳች ከልካይና ተቆጣጣሪ እንዳሻዎ ሊሞቋት በመብቃትዎ ደስታ እና እፎይታ እንደሚሰማዎ አያጠራጠርም፡፡

Continue reading
  14584 Hits

በገጠር መሬት የመጠቀም መብትን በዋስትና ማስያዝና አርሶ አደሩ

 

 

አባትነትን DNA በትክክል ማወቅ ይቻላል?

ስለ ኪሜራ ምን ያውቃሉ?

 ሰላም እንዴት ናችሁ በማለት እስኪ ሙያችን በተመለከተ አንድ ቁምነገር ላንሳ፡፡

Continue reading
  18346 Hits

የረዳት አብራሪው ኃይለመድህን አበራ የወንጀል ክስ ጉዳይ በየትኛው አገር ፍ/ቤት መታየት አለበት?

ፌቡራሪ 17/2014 እ.ኤ.አ. ዕለተ ሰኞ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ በበረራ ቁጥር ET 702 የተመዘገበ ቦይንግ 767 የመንገደኞች ማመላለሻ አውሮፕላን ከአዲስ አበባ በሱዳን በኩል አድርጎ ወደ ጣሊያን ሲበር በረዳት አብራሪው ሃይለመድህን አበራ ተገድዶ ስዊዘርላንድ ጄኔቭ ማረፉን ተከትሎ የስዊዘርላንድ መንግስት ረዳት አብራሪውን ለኢትዮጵያ አሳልፎ እንደማይሰጥና በስዊዘርላንድ መንግስት የህግ ከለላ እንደሚደረግለት እንዲሁም ረዳት አብራሪው ያቀረበው የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄም ከፍርድ ሂደቱ በኋላ ምላሽ እንደሚያገኝ ጉዳዩም በስዊስ ሃገር ፍ/ቤት የሚዳኝ መሆኑን መግለጹን ከተለያዩ ሚዲያዎች መገንዘብ ችለናል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የፌደራል አቃቤ ህግ የወንጀል ህግ 507(1)ን በመተላለፍ አውሮፕላንን ያላግባብ መያዝ ወይም ማገት ወንጀል እና የወንጀል ህግ አንቀጽ 508(1)ን በመተላለፍ አውሮፕላንን አስጊ ሁኔታ ላይ መጣል ወንጀል ፈጽመሟል በማለት በረዳት አብራሪው ኃይለመድህን አበራ ላይ ሁለት የወንጀል ክሶችን መስርቷል፡፡

ተከሳሹም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ ቢደረግለትም ሊገኝ ባለመቻሉ (ለፎርማሊቲ እንጂ በጋዜጣ ጥሪ እንደማይመጣ ይታወቃል) ጉዳዩ በሌለበት መታየቱ ቀጥሎ የአቃቤ ህግ ምስክሮች ከተሰሙ በኋላ ፍ/ቤቱ በቀን 07/07/07 ዓ/ም በዋለው ችሎት በወንጀል ህግ አንቀጽ 507(1) ስር አውሮፕላንን ያላግባብ መያዝ ወንጀል ስር ጥፋተኛ ነው ብሎ ሲወስን በሁለተኛው ክስ ግን ነፃ ነው ብሎታል፡፡

እዚህ ላይ ሊነሳ የሚገባው ዋና ጥያቄ የስዊዘርላንድ መንግስት ረዳት አብራሪውን አሳልፌ አልሰጥም የፍርድ ሄደቱ በስዊዘርላንደስ ሃገር ይታያል ባለበት ሁኔታ የፌደራል ዓቃቤ ህግ በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በረዳት አብራሪው ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡና ፍ/ቤቱም ጉዳዩን ተቀብሎ ማስተናገዱ ከወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህጋችን እና ከወንጀል ህጋችን አኳያ ሲታይ አግባብ ነው ወይ? የሚለውን ጥያቄ ማንሳት እወዳለሁ፡፡

በኢትዮጵያ መርከብም ሆነ በኢትዮጵያ አውሮፕላን ላይ ከኢትዮጵያ ግዛት ውጪ የሚፈጸም ወንጀልን በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ እንደ ተፈጸመ ይቆጠራል ተብሎ በወ/መ/ስ/ስ/ህጋችን አንቀጽ 104 ላይ ተደንግጓል፡፡ በኢትዮጵያ ግዛት የተፈጸመን ወንጀልን ለመዳኘት የኢትዮጵያ ፍ/ቤቶች የዳኝነት ስልጣን እንዳላቸው ቅቡል ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ ተፈጸመ የተባለው ወንጀል ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሆነው በበረራ ቁጥር 706 ቦይንግ 767 ላይ በመፈጸሙ በወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ህግ ቁጥር 104 መሠረት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ እንደተፈጸመ ስለሚቆጠር የኢትዮጵያ ፍ/ቤቶች ረዳት አብራሪው የፈጸመውን ድርጊት በተመለከተ የሚቀርቡለትን የወንጀል ክሶች ተቀብለው ማስተናገድ ይችላሉ በማለት በቀላሉ ድምዳሜ ላይ ልንደርስ እንችላለን፡፡

Continue reading
  16012 Hits
Tags: