Abiyou Girma is a qualified and a licensed lawyer. He obtained Bachelor of Laws (LLB), his first degree, from Saint Marry's University, Faculty of Law, in June 2007 and master's degree (MA), from Addis Ababa University Faculty of Law specializing in areas of Human Rights in 2012. He was at Ministry of Justice both as a public prosecutor and Legal adviser at International Co-operation on Legal Affairs Directorate. During his stay he has acquired an extensive experience in Civil law, commercial law and criminal Law, prosecutions, Human Rights and International Law.

ስለ ንብረት የዋጋ ግምት ጥቂት ነጥቦች

 

ለፍርድ ቤቶች በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ የንብረትን ትክክለኛ የዋጋ ግምት ማወቅ የግድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያቶች አሉ፡፡ ለመሆኑ የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ያስፈልጋል? የንብረት የዋጋ ግምት ተገምቶ እንዲቀርብ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት የመገመት ኃላፊነት በሕግ የተሰጠው ለማን ነው? በአሠራር ደረጃ የንብረት የዋጋ ግምት በማን እና እንዴት እየተገመተ ይገኛል? የንብረት ዋጋ ግምትን አስመልክቶ የሚታዩ ችግሮች ምንድን ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት ሲሰራ በመሠረታዊነት ሊካተቱ የሚገባቸው ነጥቦችስ ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ፅሁፍ በጥቂቱ እንዳስሳለን፡፡        

  1. የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ይጠቅማል?

የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፡፡ እነዚህም፡ -

  • ፍትሐዊና ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት እንዲቻል፤
  • የፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ሥልጣን ለመወሰን እንዲቻል፤
  • ለፍርድ ቤቶች ተገቢውን የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ለማከፈል፤
  • ጥፋተኛ ተብለው በወንጀል የሚፈረድባቸው ሠዎች ላይ ተመጣጣኝና የተገኘውን ልተገባ የጥቅም መጠን ወይም የደረሰውን የጉዳት መጠን መሠረት ያደረገ ቅጣት ለመወሰን ነው፡፡
  1. ተከራካሪ ወገኖች የንብረት ዋጋ ግምት መጠን እንዲጠቅሱ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው?
  • ክስ የሚቀርበው አንድን ንብረት ለማስለቀቅ ወይም ከአንድ ንብረት ላይ ድርሻ ለመጠየቅ በሆነ ጊዜ ክስ የቀረበበትን ንብረት ወይም የንብረቱን ወይም ከንብረቱ ላይ የሚገኘውን የድርሻ የዋጋ ግምት በክስ አቤቱታ ላይ ሊጠቀስ እንደሚገባ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ 222 /1/ /ቀ/ እና 226 /3/ /4/ ላይ ይጠይቃል፤
  • የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም በወጣው በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 11 /1/ እና 14 መሠረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከብር 500,000.00/አምስት መቶ ሺሕ/ በላይ የሆኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን እንዲሁም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከብር 500,000.00/አምስት መቶ ሺሕ/ በታች የሆኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን አከራክረው የመወሰን ሥልጣን ተሠጥቷቸዋል፡፡ ተከራካሪ ወገኖችም የሚያቀርቡትን የገንዘብ ወይም የንብረት ክርክር የዋጋ ግምት በክሳቸው ላይ መግለፃቸው የፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ሥልጣን የሚወስን በመሆኑ በአዋጁና በሥነ ሥርዓት ሕጉ መሠረት በዳኝነት የሚጠይቁትን የገንዘብ መጠን ወይም የንብረት የዋጋ ግምት የመጥቀስ ግዴታ ተጥሏል፤
  • ስለ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ገንዘብ አከፋፈል በወጣው የ1945 ዓ.ም. አስራ ሁለተኛ ዓመት ቁጥር 15 የሕግ ክፍል ማስታወቂያ ቁጥር 177 መሠረት ከሳሽ የሆነ ወገን ዳኝነት በሚጠይቅበት ገንዘብ መጠን ልክ ለፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ሊከፍል እንደሚገባና ተመኑም ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም አንድን ንብረት አስመልክቶ የፍትሐብሔር ክስ የሚያቀረብ ሠው ለፍርድ ቤቶች የዳኝነት የአገልገሎት ክፍያ አከፋፈል እንዲያመች የንብረቱን የዋጋ ግምት በክስ አቤቱታው ላይ የመግለፅ ግዴታ አለበት፡፡
  • የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባወጣው የተሻሻለው የቅጣት አወሳስን መመሪያ ቁጥር 2/2006 መሠረት በፍርድ ጥፋተኛ በተባሉ ሠዎች ላይ ቅጣትን ለመጣል በወንጀል ድርጊት የተገኘውን የንብረት ጥቅም ግምት ወይም የደረሰውን የንብረት ጉዳት ግምት ማወቅ አስፈላጊ ከመሆኑም ባለፈ የተጠቀሰው ሕግ የንብረት የዋጋ ግምት መጠን ላይ ክርክር ከተነሳበት የዋጋ ግምቱ ተለይቶ እንዲጠቀስና እንዲቀርብ ይጠይቃሉ፡፡    
  1. በሕጉ መሠረት የንብረት የዋጋ ግምት ላይ ክርክር ከቀረበ ግምቱን የሚገምተው ማን ነው? የግምት ሥራውስ እንዴትና በምን መመዘኛ ይሰራል?

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 250 መሠረት ከተከራካሪ ወገኖች መካከል አንደኛው የሚያቀርበውን የዋጋ ግምት ሌላኛው ተከራካሪ ወገን በዋጋ ግምቱ ባለመስማማት ሊቃወም እንደሚችልና የግምት ክርክር ከተነሳ ደግሞ ፍርድ ቤቶች የሀብቱን ወይም የንብረቱን የዋጋ ግምት በመገመት ለፍርድ ቤቱ እንዲያሳውቁ ምትክ ዳኞችን በመሾም ሊያስገምቱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡ 

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ላይ የንብረት ዋጋ ግምት እንዲገምቱ የሚሾሙ ምትክ ዳኞችም የንብረት ዋጋ ግምቱን ምንን መሠረት በማድረግና እንዴት እንደሚከናወኑ የሚያመለክተው ነገር ባይኖርም ምትክ ዳኞቹ የግምት ሥራ ሲሰሩ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 132 እስከ 135 በተመለከቱ ቅድመ ሁኔታዎችና የአሠራር ሥርዓት መሠረት የዋጋ ግምቱን ገምተው ሪፖርት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

Continue reading
  15726 Hits

ስለ ይርጋ ጥቂት ነጥቦች

 

 

ይርጋ ምንድን ነው? ይርጋ ዓላማው (ጠቀሜታው) ምንድን ነው? ይርጋ ጉዳቱስ ምንድን ነው? ይርጋ የሚያስጠብቀው የማንን መብት ነው? የይርጋ መሠረታዊ መርሆዎች ምንድን ናቸው? ይርጋን የሚመለከቱ የሕግ ድንጋጌዎች ምን ይመስላሉ? በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ጽሑፍ ይዳሰሳሉ፡፡  

የይርጋ ምንነት

ይርጋ የሚለው ቃል መነሻውረጋከሚለው የአማርኛ ቃል ጋር የተያያዘ ሲሆንረጋየሚለውን ቃል ደራሲ ተሠማ ኃብተ ሚካኤልከሠቴ ብርሀን ተሰማበተሰኘውና 2002 .. በድጋሚ ባሳተሙት የአማርኛ መዝገበ ቃላት ላይየሰው ሀሳቡ ከመውጣት ከመውረድ በሀሳብ ከመዞር ከመባከን ከመናወጥ ጠጥ (ፀጥ) አለበሚል ትርጓሜ ተሠጥቶታል፡፡ ከዚህ በመነሳትም ይርጋ የሚለውን ቃል በአንድ ጉዳይ ላይ ክስ የማቅረብ ወይም መብት የመጠየቅ ጉዳይን አስመልክቶ በጉዳዩ ላይ ክስ የሚያቀርብበት ሰው ስለጉዳዩ ያለውን ሀሳብ ከመውጣት ከመውረድ በሀሳብ ከመዞርና ከመባከን ከመናወጥ ከረጋ (ፀጥ) ካለ በኋላ ሊከሰስ ወይም ሊጠየቅ እንደማይገባ ያመለክታል በሚል ልንወስደው እንችላለን፡፡ በሌሎች ፅሁፎች ላይም ይርጋ ማለት አንድ መብቱ ወይም ጥቅሙ የተነካበት ሰው በሌላ ሰው ላይ ክስ፣ አቤቱታ ወይም የይገባኛል ጥያቄ እንዲያቀርብ በሕግ ተለይቶ የተቀመጠ የክስ (አቤቱታ) ማቅረቢያ ጊዜ ነው፡፡ በሕግ የተቀመጠው የክስ ማቅረቢያ ጊዜ ካለፈ በኋላም በዚያው ጉዳይ ላይ በጣም በውስንና ጥቂት ምክንያቶች ካልሆነ በስተቀር ክስ የማቅረብ መብት ቀሪ ይሆናል፡፡

Continue reading
  34461 Hits

ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት (የግዴታ ሥራ) እንደ ወንጀል ቅጣት

 

ጣልያንን ለዘጠኝ ዓመታት የመሩት የቀድሞው የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ ፕሬዚዳንትና ባለቤት እንዲሁም ቢሊየነሩ ሲልቪዮ ቤርሎስኮኒ በተከሰሱበት የታክስ ማጭበርበር ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው በሚላን ከተማ የሚገኘው ፍርድ ቤት ቤርሎስኮኒ የአራት ዓመታት እስራት ቢፈረድባቸውም የእስራት ቅጣቱ በተለያዩ ምክንያቶች ቀርቶ በተቃራኒው ቤርሎስኮኒ በአረጋውያን ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል ውስጥ ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ እ.ኤ.አ. በ2013 መወሰኑ ይታወቃል፡፡ በውሳኔው መሠረትም ቤርሎስኮኒ ሴሴኖ ከተማ ውስጥ በሚገኘውና ከ2000 በላይ በእድሜያቸው የገፉ፣ የአእምሮና የአካል ጉዳተኛ የሆኑ አረጋውያን በሚገኙበት ማዕከል ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በሳምንት ለአራት ሠዓታት በማዕከሉ እየተገኙ አረጋውያኑን እንዲመግቡ፣ እንዲንከባከቡ፣ እንዲያንሸራሽሩ እንደ አጠቃላይም በማንኛውም መልኩ ከአረጋውያኑ ጎን እንዲሆኑ ተወስኖባቸው ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱን ፈፅመው አጠናቀዋል፡፡        

ታዋቂው አሜሪካዊ የሙዚቃ አቀንቃኝ ቦይ ጆርጅም በመኖሪያ ቤቱ የኮኬይን ዕፅ ይዞ መገኘትና በሀሰት የመኖሪያ ቤቴ ተዘርፏል በሚል ካቀረበው የሀሰት ጥቆማና ሪፖርት ጋር በተያያዘ እ.ኤ.አ. በ2006 በማንሀተን የወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ የተወሰነበት ቅጣት ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጥ ይኸውም በኒውዮርክ ከተማ ለአምስት ቀናት ያህል የከተማዋን መንገዶች እንዲያፀዳ ሲሆን ከኒውዮርክ ከተማ የፅዳት አገልግሎት ክፍል ጋር በመሆን የከተማዋን አውራ ጎዳናዎች ለአምስት ቀናት ያህል በማፅዳት ቅጣቱን ፈፅሟል፡፡

ሆላንዳዊው የእግር ኳስ ተጫዋች የነበረውና ለአያክስ አምስተርዳም፣ ኤሲ ሚላንና ባርሴሎና እግር ኳስ ክለቦች ተጫውቶ ያሳለፈው ፓትሪክ ክላይቨርትም የ19 ዓመት ወጣት በነበረበትና ለአያክስ አምስተርዳም እግር ኳስ ክለብ በሚጫወትበት ወቅት በአምስተርዳም ከተማ ከፍጥነት ወሰን በላይ መኪና ሲያሽረክር ባደረሰው የመኪና አደጋ የቲያትር ዳይሬክተር የነበሩ የ56 ዓመት ጎልማሳ ሕይወታቸው እንዲያልፍ በማድረጉ በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብሎ ዕድሜው ገና 19 ዓመት የነበረና ተስፈኛ ስፖርተኛ መሆኑ ከግምት ገብቶ የተጣለበት የሶስት ወራት የእስራት ቅጣት በሁለት ዓመት የፈተና ጊዜ እንዲገደብ፣ ለ18 ወራት መኪና ከማሽከርከር እንዲታቀብ እና ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጥ ተወስኖበታል፡፡ በሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎቱም ፓትሪክ ክላይቨርት ለ240 ሰዓታት ታዳጊ ሕፃናትን በእግር ኳስ ስፖርት እንዲያሰለጥንና ለሕፃናቱ መልካም አስተዳደግ አስተዋፅኦ እንዲያደርግ ተወስኖበት ቅጣቱን መፈፀሙም ይታወቃል፡፡ ከእነዚህ ሠዎች በተጨማሪ ሌሎች ሠዎችም ለፈፀሙት የወንጀል ድርጊት ቅጣት እንሆን ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት እንዲሰጡ ሲወሰንባቸው ይታያል፡፡     

ለመሆኑ የወንጀል አጥፊዎች ላይ የሚጣሉ ቅጣቶች ምን ዓይነት ናቸው? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራ ምን ዓይነት ቅጣት ነው? ዓላማውስ ምንድን ነው? በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግስ ሽፋን ተስጥቶታል ወይ? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራ የሚወሰነው ምን ምን ሁኔታዎች ሲሟሉ ነው? ስንት ዓይነት የግዴታ ስራዎች አሉ? ፍርድ ቤቶችስ የግዴታ ስራን አስመልክቶ በሕግ ተለይቶ የተሰጣቸው ሥልጣን ምንድን ነው? ሕዝባዊ የግዴታ አገልግሎት መስጠት ወይም የግዴታ ስራን አስመልክቶ የሚስተዋሉ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ምንድን ናቸው? የሚሉና ተያያዥ ነጥቦችን በዚህ ፅሁፍ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡

Continue reading
  15080 Hits

የተፋጠነ ፍትሕ የማግኘት መብት እና ተግባራዊ አፈፃፀሙ

 

 

የተፋጠነ ፍትሕ ወይም ዳኝነት ያለመስጠትና የፍርድ ቤቶች በአሠራርና በውሳኔ አሠጣጥ ላይ መዘግየት ደግሞ ዋነኛው የዳኝነት ሠጪው አካል ሊመልሰው የሚገባ የተገልጋዩ ጥያቄ ነው፡፡

ፍትሕ /ዳኝነት/ በመስጠት ላይ ያለ መዘግየት አንድ ጉዳይ ለፍርድ ቤት ቀርቦ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥበት ጊዜ ድረስ ያለውን ያለበቂ እና አሳማኝ ምክንያቶች ያሉ መዘግየቶችን የሚያካትት ነው፡፡ ሁሉም ጉዳዮች እንደየባሕሪያቸውና ፀባያቸው የሚወስዱት የየራሳቸው ጊዜ ያላቸው ቢሆንም ተገልጋዮች ለፍርድ ቤት ያቀረቡት ጉዳይ እስኪወሰን ይፈጃል ወይም ይወስዳል ብለው የሚያስቡት ጊዜ ይኖራል፡፡ ችግሩ የሚያመጣውም በጉዳዮች ላይ ይፈጃል ወይም ይወስዳል ተብሎ ከሚገመተው ጊዜ በላይ እጅግ የተራዘመና ተከታታይ ቀጠሮዎች እየተሰጡ ጉዳዮች ሲጓተቱ ነው፡፡

እጅግ የተራዘመና የተዘገየ የፍትሕ ወይም የዳኝነት አሠጣጥ ሂደት ያለበት ሁኔታና አሠራርም ተከራካሪ ወገኖች ላይ ጥርጣሬ እና እምነት ማጣትን የሚያሳድር ከመሆኑም ባሻገር የፍትሕ ስርዓቱን ውጤታማነት እና ብቃት አጠያያቂ ሊያደርገው ይቻላል፡፡

Continue reading
  13271 Hits

Ethiopia’s Human Rights Treaty Reporting to the UN Treaty Bodies

INTRODUCTION

Preamble of the United Nations (UN) Charter requires member states and the people of the UN “to reaffirm faith in fundamental human rights, in the dignity and worth of the human person, in the equal rights of men and women and of nations large and small”. In order to achieve this goal of the charter and secure universal recognition and implementation of human rights to their citizens’ member states of the United Nations entered into seven major human rights treaties.

 

The seven core international human rights treaties create legal obligations for state parties to promote and protect human rights at the national level. When a country accepts one of these treaties through ratification, accession or succession, it assumes a legal obligation to implement the rights set out in that treaty. In addition to this, state parties to these treaties have also the obligation to report every activities conducted in the name of implementation to the United Nations treaty based bodies. 

Ethiopia as a member of the United Nation and member of these human rights treaties has the obligation to implement the treaties and report its implementation. However, a part from the implementation problem Ethiopia has been criticized for its failure or delay to report its implementation of the treaties. Keeping in mind this criticism related to Ethiopian human rights reporting record, questions and issues related with human rights reporting system with special emphasis to the Ethiopian context is assessed and analyzed under this paper. And, just because human rights reporting are highly related with the rights enshrined under the treaties concepts about some rights are discussed in a summarized fashion.  

Continue reading
  23577 Hits

Law as a means of Serving Justice

Anciently morality and religion were primary basis to govern the relationship between peoples. And there was no need to search for a law maker to enact laws that govern social relations. It was based on natural law that human relations were regulated. But, after a long and serious debate between legal scholars and philosophers it is determined that there must be a human made law to regulate human relations. 

 

Based on this conception, law made by human beings has played an important role in the definition and protection of certain relationships, systems and institutions and in the control of individual and collective human behavior. Through the use of normative, directive and prescriptive rules, supported by varying degrees of sanctions, law has been used to create a climate of social order, the usual justification of which has been that it benefits members of society. But, the issue whether human made laws are exact machinery to serve justice and fairness to all the society is always questionable.

 

Rights and duties are usually acknowledged through laws made by human beings. But, should a right be acknowledged and clearly indicated by law to be considered as a human right or is it enough to simply be a human being to enjoy human rights is debatable by itself.   

Continue reading
  54808 Hits
Tags:

The Police and Human Rights in Ethiopia

 INTRODUCTION

This article is about “The police and human rights in Ethiopia”. Every state has the obligation to respect, protect and fulfill human rights of human beings. And police as one part the executive organ of government has its own obligations towards human rights. These include the obligation to respect and protect human rights. And police officers have also a direct and day to day contact with the entire society that requires an enormous effort and patience of police officers to respect and protect human rights.

The objective of this article is to survey the different aspects of human rights, explore the role of police in relation to human rights in the federal system of Ethiopia and examine the possible remedies for violation of human rights in a summarized fashion.    

The scope of this article is limited to the police, its role in relation to the respect and protection of human rights, the possibilities in which police officers violate human rights and the possible remedies for violation of human rights. And deep analysis of all responsibilities of police is not the concern of this article. 

Questions such as: What are the responsibilities of police in respecting and protection human rights? How are victims treated by police officers? Is there any guideline or technique regarding treatment of victims in Ethiopia? What are the international, regional and national legal frameworks of remedies for violation of human rights? What are the possible remedies for violation of human rights? Are all the remedies effectively applicable in Ethiopia? How far are police officers responsible for their actions that violate human rights of citizens? and other related questions are answered, assessed and analyzed under this article. 

Continue reading
  36404 Hits

ሺሻን ለሽያጭ ከማቅረብና ከመጠቀም ጋር ተያይዘው የሚፈፀሙ ወንጀሎች

በልደታ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሺሻ በማስጨስ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ግለሰቦች እና የማስጨሻ ቤቶች መኖራቸውን የተረዳው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በሥሩ የሚገኙ የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች የሺሻ ማስጨሻ ዕቃዎችን እና ሺሻ ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ ሺሻን ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦች ላይም የወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው ሲሆን በምርመራ መዛግብቱ ላይ በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በኩል ተገቢውን የሕግ አስተያየትና ውሳኔ መስጠት ይጠበቃል፡፡ ሆኖም ጉዳዩ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ፍርድ ቤቶችና በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ሲታይ ያልነበረ በአንፃሩ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶችና በከተማ ነክ ፍትሕ ጽ/ቤቶች የአቤቱታ ምርመራና የክስ አቀራረብ ንዑስ የሥራ ሂደት ሲታዩ የነበረና ሺሻን አስመልክቶ በቂ መረጃና የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በተጣሩት የምርመራ መዛግብት ላይ ተገቢውን የሕግ አስተያየት እና ውሳኔ ለመስጠት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡

 

በመሆኑም የሺሻን ምንነት፣ ሺሻ የሚይደርሰውን ጉዳት፣ ሺሻን መጠቀም፣ ማስጠቀም እና ወደ አገር አስገብቶ ማከፋፈል ከሕግ አንፃር የሚያስከትለው ኃላፊነት ስለመኖሩ፣ ፖሊስና የወረዳ (ቀበሌ) አስተዳደር ሠራተኞች ሺሻ የሚያጨሱና የሚያስጨሱ ግለሰቦችን እንዲሁም የማስጨሻ ዕቃዎችን የሚይዙበትና ማስጨሻ ቤቶችን የሚዘጉበትን እንዲሁም ዐቃቤ ሕግ ሺሻ በሚያስጨሱ ግለሰቦች ላይ የተጣሩ የምርመራ መዛግብት ላይ የሕግ አስተያየት እና ውሳኔ የሚሰጥበት አግባብ ላይ እንደ አጠቃላይም ከሺሻ ጋር ተያይዘው ለሚነሱ ችግሮች የመፍትሄ ሃሳብ በማቅረብ ላይ ያተኮረ አነስተኛ ጥናት ማዘጋጀቱ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በዚሁ መሠረትም ይህ አነስተኛ ጽሑፍ ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

 

የሺሻ ምንነት

Continue reading
  10253 Hits
Tags: