- Details
- Category: Non-Contractual Liability (Tort Law)
ውል ከማድረግ በፊት የተደረገ ድርድር ቁጥር 2055
አንድ ተዋዋይ ውል ገብቶ በውሉ መሠረት ግደታውን ሳይወጣ ከቀረ በውሉ መሠረትና በውል ድንጋጌዎች መሠረት አላፊ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን ውል ከመግባቱ በፊት አንደ ሰው ሌላኛውን ወገን ውል እንዲገባ ሊያግባባውና ውሉንና ከውሉ የሚያገኘውን በማሰብ ለወጪ ሊዳርገው ይችላል፡፡ ይህን ወጪ ከወጣ በኃላ ግን አግባቢው ውል ውስጥ ላይገባ ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ አግባቢው በቁጥር 2055 መሠረት ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
በውል የገባውን የግዴታ ቃል ስላለማክበር ቁጥር /2056/
የዚህ ርዕስ ቁጥር ትክክል አይመለስንም ምክንያቱም አንድ ሰው በውል የገባውን የግዴታ ቃል ያለማክበሩ ጉዳይ የሚዳኘው ከውል ውጨ ሕግ አላፊነት ሳይሆን የሚዳኘው ቁጥር 2047/2/ ስር እንደተመለከተው በውል አለመፈፀም ድንጋጌዎች መሠረት ነው፡፡
ሁለተኛ ደግሞ ቀጥለን እንደምንመለከተው ሁለት ሌሎች ተዋዋዩች የመሠረቱትን ውል ነው እንዳይተገበር መሰናክል የሚሆነው ፡፡ ስለዚህ ርዕሱ መሆን ያለበት በተዋዋይ ወገኖች መሃል ጣልቃ መግባት ነው፡፡
በቁጥር 2056 /1/ መሠረት ሁለት ቀድሞ ውል የተዋዋሉ ይኖራሉ፡፡ ሌላ ሶስተኛ ወገን ደግሞ ይህ ሁለቱ ተዋዋይ ወገኖች የገቡት ውል እንዳይተገበር ከአንደኛው ተዋዋይ ጋር ሌላ ውል ያደርጋል ፡፡ ሁለት ነጥቦች ግልፅ መሆን አለባቸው፡፡ መጀመሪያ ሶስተኛው ወገን በሁለቱ ሰዎች መሃል ውል መኖሩን ማወቅ አለበት፡፡ የዚህ እውቀት ከሌለው በዚህ ቁጥር መሠረት ተጠያቂ አይሆንም ሁለተኛ ነገር ሶስተኛው ወገን በዚህ ድርጊቱ ቀድሞ በሁለት ወገኖች መሃል የተደረገ ውል እንዳይተገበር ማድረግ አለበት፡፡ እነዚህ ሁለቱ ሁኔታዎች ካሉ ነው ጥፋተኛ የሚባለው፡፡ ውል እንዳይተገበር ሆኗል በዚህም ጉዳት ደርሶብኛል የሚል ወገን ይህን እንዳይሆን አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ይህን አስፈላጊውን ጥንቃቄ በቸልተኝነት ሳያደርግ ከቀረ በቁጥር 2056 /2/ መሠረት የኃለኛው ተዋዋይ ጥፋተኛ አይሆንም፡፡
የማይገባ ውድድር ቁጥር /2057/
የማይገባ ውድድርን ለማወቅ ጤናማ ውድድርን /fair competition/ ብናውቅ አይከፋም፡፡ ጤናማ ውድድር ሁለት ወይም ከሁለት የሚበልጥ በተመሳሳይ ሥራ የተሰማሩ ወገኖች /ነጋዴዎች/ ለደንበኖቻቸው የተሻለ አገልግሎት ወይም ሸቀጥ /Services or goods / ለመስጠት ወይም ለመሸጥ የሚደረግ ውድድር ማለት ነው፡፡ ይህም በሚከተለው መንገድ ይገለፃል፡፡
- የሸቀጦችን ዋጋ በመቀነስ
- ደረጃውን የጠበቀ ሸቀጥ በማምረት
- ደንበኛን ሊያረካ የሚችል ግልጋሎት
በመስጠት እና በሌሎችም፡፡ ሆኖም ግን ስለሌላኛው ተወዳዳሪ ነጋዴ ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ ማሳተም፣እንዲሁም ሀሰተኛ ወሬ መንዛት፣ የሌላኛውን ተወዳዳሪ የንግድ ምልክት ወይም አርማ /Trade name or trade mark/ ወይም ተመሳሳይ መያዥ /container/ መጠቀም የማይገባ ወይም ጤናማ ያለሆነ ውድድር ስለሆነ ይህን አደርጊ በቁጥር 2057 መሠርት ጥፋተኛ ይሆናል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዚ ፍ/ቤት ለተጉጂው ካሣ እንዲከፈል ከማዘዙም በተጨማሪ በቁጥር 2122 መሠረት ድርጊቱ እንዲቆም ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡
የሌላውን አስመስሎ ማስራት ቁጥር /2058/
በእግሊዝኛው /simulation/ የሚባለው ነው፡፡ በአጭሩ ማስመሰል በዚህም ሌላውን ለጉዳት መዳረግ ነው፡፡ በከተማው አባባል ቁጭ ይበሉ የሚባለው ነው፡፡ ይህን በምሳሌ እናስረዳ፡፡
አዲስ አበባ ከተማ ቦሌ መሄጃ መንገድ ላይ የኢትዩጵያ አየር መንገድ አይሮኘላንን በሚመስል መልክ የተሰራ ካፍቴሪያ ይገኛል፡፡ ስሙም ለንደን ካፌ ይባላል፡፡ አንድ ቀን አንድ የከተማ ጮሌ ወደ ሐጂ ለመጓዝ የሚፈልጉ የገጠር ሰዎችን አገኘ እንበል ጉዳያቸውን ከጠየቃቸው በኃላ ወደ ሐጂ መጓዝ እንደሚፈልጉ ገለፁለት እንበል፡፡ ይህ የከተማ ጮሌ ሰዎቹን ወደ ተባለው የአይሮኘላን ምስል ወስዶ ካፍቴሪያው ውሰጥ ካስገባቸው በኃላ ብሩን አምጡ እኔ ከፍዬ እስክመጣ ድረስ አይሮኘላኑ ሞተሩን ያግላል አሁንም እንደሚታዩት እየጋለ ነው በማለት የሻይና ቡና መስሪያ ማሸኑ ሲሰራ ያሳያቸዋል እንበል፡፡ የገጠሩ ሰዎችም አመነውት ብራቸውን ይሰጡታል፣ ጮሌውም “መጣሁ” ጠብቁኝ በማለት እዛው ጥሏቸው ሄደ እንበል፡፡ ቢጠብቁት አይመለስም፣ አስተናጋጅ ትመጣና ምን ልታዘዝ ትላለች፡፡ ወደ ሐጂ ለመብረር እዚህ “አይሮኘላን” ውስጥ አንደገቡ ቲኬታቸውንም እየተጠባበቁ መሆናቸውን ይነግሯታል፡፡ አስተናጋ²ም እውነተኛውን ትነግራቸዋለች፡፡ ማስመሰል በዚህም ሌላውን መጉዳት ይህ ነው፡፡
ያልተስተካከለ ወሬ ቁጥር /2059
በዚህ ቁጥር መሠረት አንድ ሰው ያልተስተካከለ ወሬ /መረጃ/ በማሰተላለፍ ተጠያቂ አይሆንም፡፡ ተጠያቂ ለመሆን ሁለት ነገሮችን ማሟላት አለበት፡፡ የመጀመሪያ ሆን ተብሎ ወይም በቸልተኝነት የተላለፈውን መረጃ / information / የተቀበለው ሰው ወይም ሌላ ሰው በመረጃው መሠርት እንደሚተገብርና /act/ ሁለተኛ ደግሞ በመረጃው መሠረት /act/ ያደረገው ሰው ላይ ጉዳት እንደሚደርስበት ማወቅ አለበት፡፡ ለምሳሌ ሰዎች በአንድ አዳራሽ ውስጥ ፊልም ወይም ትያትር እየተመለከቱ እያለ አንድ ተመልካች እሳት ሳይነሳ ወይም ሳይኖር እሳት! እሳት! እያለ ቢጮህና ይህንንም በማድረጉ ሰዎች ትርምስመሳቸው እንደሚወጣና አንዱ በአንዱ ላይ ጉዳት እንደሚያደርስ እያወቀ ይህን ያደረገ እንደሆነ በቁጥር 2059/1/ መሠረት ጥፋተኛ ይህናል፡፡
ይህ ንዑስ ቁጥር ለተራ ሰው ነው፡፡ ባለሞያ ከሆነ ግን ከሞያው ጋር በተያያዘ መስጠት የሚገባው መረጃ ትክክለኛ መሆን አለበት፡፡ በሰጠው መረጃ ሰዎች /act/ ማድረግና ጉዳት ሊደርስባቸው አይጠበቅም፡፡ ሞያው ጋር በተያያዘ አንድ ባለሞያ ትክክለኛ መረጃ አለመስጠት ብቻውን ጥፋተኛ ያደርገዋል 2059/2/
ሆኖም ግን አንድ ሰው መልሶ ገንዘብ መክፈል ስለሚችል ገንዘብ እንደሰጠው ለማድረግ ሥራ ለማስገኘት ስለችሎታው መናገር የንግድ ዕቃ እንዲሰጠው ስለዚህ ሰው ችሎታ ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ መስጠት በፅሑፍ ተደርጐ ተፈርሞ ካልተሰጠ በሰተቀር በቁጥር 2060 መሠረት ተጠያቂ አይደለም፡፡ ይህን አንድ ምሳሌ በመውሰድ ለማስረዳት እንሞክር የአንድ ሰው ዘመድ የሆነችን አንዲት ልጅ በቤት ሠራተኝነት ለማስቀጠር የተለያዩ ምግቦችን የመስራት ችሎታ አላት በማለት ሥራ ቢያስገኝላት ይህ ሰው ይህን ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ የሰጠው ለልጅቷ ሥራ ለማስገኘት ብቻ ከሆነ ጥፋተኛ አይባልም፡፡ ግን እነዚህን ትክክለኛ መርጃዎች የሰጠ ሰው ቃሉን በፅሑፍ አድርጐ ፊርማውን ካኖረ በቁጥር 2060/2/ መሠረት ተጠያቂ ይሆናል፡፡
ምስክሮች ቁጥር /2061/
ምስክሮች አንድ ነገር መፈፀሙን ወይም አለመፈፀሙን /occurrence or non occurrence/ ወይም አንድ አድራጉት መኖሩን ወይም አለመኖሩን /the existence or the non existence/ ሊመሰክሩ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ የጋብቻ ስርዓት መፈፀሙን ወይም አለመፈፀሙን ወይም ጋብቻ መኖሩን ወይም አለመኖሩን ሊመሰክሩ ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ይህ የሰጡት የምስክርነት ቃል እርግጠኛ /accuracy/ ስለመሆኑ አለፊዎች ናቸው፡፡
ሰዎች ይህን በምስክሮች የተሰጠውን ቃል በመንተራስ አንድ ነገር ሊፈፅሙ ይችላሉ፡፡ለምሳሌ አንዲት ሴት ባለትዳር ከሆነ ሰው ጋር ምስክሮች ትዳር የለውም በማለታቸው ትዳር ልትመሰርት ትችላለች፡፡ በዚህ አድራጉታቸው ለሴትየዋ ኃላፊ ይሆናሉ በሌላ በኩል ደግሞ እነዚሁ ሰዎች ይህን የምስክርንት ቃል የሰጡት በቅን ልቦና ከሆነና በሌላ ሰው ተሳስተው መሆኑን ካረጋገጡ በዛ ባሳሳቻቸው ሰው ላይ ክስ መመስረት ይችላሉ ፡፡ 2061/3/፡፡
ምክር ወይም የአደራ ቃል /advice or recommendation/ ቁጥር /2062/
አንድ ሰው ለሌላ ሰው አንድ ነገር እንዲያከናውን ወይም እንዳያከናውን ምክር ሊሰጠው ይችላል፡፡ ለምሳሌ ጠንቋይ ዘንድ ቢሂድ ከበሽታው እንደሚድን ሊመክረው ይችላል፡፡ መካሪው በዚህ ብቻ ከተወሰነ በቁጥር 2062 መሠረት ጥፋተኛ አይደለም ሆኖም ግን ከዚህ ምክር አልፎ ጠንቋዩ ዘንድ ይዞት ብሄድና በዚህ ምክንያት ምክር ተቀባዩ ጉዳት ቢደርስበት መካሪውና መሪው ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
ስለ መያዝ /Distraint/ ቁጥር 2063
አንድ ባለዕዳ ዕዳውን በጊዜ ላይከፍል ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ አበዳሪው ባለዕዳው ዕዳውን እንዲከፍል ለማስገደድ የባለዕደውን ንብረት ሊይዝ ይችላል፡፡ ለምሳሌ የአንድ ሰው ከብት ወደ ሌላ ሰው ማሳ ገብቶ አዝዕርቱን ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ባለእርሻው ባለከብቱ ከብቶቹ ያደረሱትን ጉዳት እንዲከፍለው ለማድረግ ከብቶችን ሊይዝ ይችላል ይህ ጥፋት አይደለም፡፡
ይህ መያዝ ጥፋት የሚሆነው ባለዕዳው ሊቀበል ከሚገባው ገንዘብ ጋር የተያዘው ንብረት ከዕዳው ሲበልጥ ነው በተጨማሪም መያዙ አስፈላጊ ሳይሆን ሲቀር ለምሳሌ ከብቶቹ ላጠÕት ባለከብቱ እንደሚከፍል ዋስ ቢጠራ መያዙ ያለአስፈላጊ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ያዡ ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
የፍርድ ትዕዛዝ ስለመፈፀም ቁጥር /2064/
ሆኖም ንብረት በፍርድ አስፈፃሚ ሊያዝ ይችላል፡፡ የተያዘው ንብረት ከዕዳው ሊበልጥ ይችላል፡፡ ሆኖም የፍርድ አስፈፃሚው ጥፋተኛ አይሆንም ነገር ግን የሚከተሉት መሟላታቸውን እርግጠኛ መሆን አለብን፡፡
የፍርድ አስፈፃሚው ንብረቱን የያዘው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለማስፈፀም መሆን አለበት፡፡ በሌላ አካል የሚሰጥ ትዕዛዝ ለማስፈፀም መሆን የለበትም ማለት ነው፡፡
ትዕዛዙ ትክክለኛ አሰራሩን የያዘ ፎርም መሆን አለበት፡፡ ትዕዛዙ ትክክለኛ ነው ለማለት ትዕዛዙ የዳኛ ፊርማና የፍርድ ቤቱ ማህተም ሊኖረው ይገባል ትዕዛዙ በፅሑፍ መሆን አለበት፡፡
ስለሆነም ትዕዛዙ የዳኛውን ፊርማ ያልያዘ ከሆነ ወይም የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ያልያዘ ሆኖ እያለ ንብረቱን ከያዘ ፍርድ አስፈፃሚው ጥፋተኛ ይህናል 2064/2/ በተጨማሪ ፍርድ አስፈፃሚው ከተሰጠው ትዕዛዝ ውጭ ከሆነ ለምሳሌ በትዕዛዙ ላይ የተባለውን ንብረት ሳይሆን ሌላ ንብረት ከያዘ ወይም ተጨማሪ ንብረት ከያዘ ወይም ትዕዛዙን ሕግን ባለማክበር የፊፀመ እንደሆነ ለምሳሌ በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ መሠረት ሊያዙ የማይችሎትን ንብረቶች ከያዘ ጥፋተኛ ይሆናል፡፡ 2064/2/
ስለ ይርጋ ቁጥር /2065/
አንድ ሰው በአንድ ጉዳይ ላይ ክስ ለመመስረት የሚችለው የይርጋ ጊዜው ሳያልፍበት ነው፡፡ ለምሳሌ በውል የይርጋ ጊዜው 10 ዓመት ነው፡፡ ስለሆነም ባለገንዘቡ በባለዕዳው ላይ በ10 ዓመት ጊዜ ውስጥ ክስ መመስረት አለበት፡፡ ይህን ከላደረገ ክሱ በይርጋ ይታገድበታል፡፡ በሌላ በኩል ባለዕዳው ዕዳውን ባለመክፈሉ በቁጥር 2030 መሠረት ጥፋተኛ ነው፡፡ ይህ ቁጥር ተጠቀሱ ክስ ቢመሠረትበት ባለዕዳው ቁጥር 2065ን በመጥቀስ በይርጋ ደንብ መክሰሰ ቀርቶልኛል ብሎ ቢከራከር ጥፋተኛ አይሆንም፡፡
- Hits: 7179
- Details
- Category: Non-Contractual Liability (Tort Law)
የኢፊድሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 40 ስር የግል ንብረት ምን ማለት እንደሆነ ዘርዝሮ ማንኛውም የኢትዩጵያ ዜጋ የግል ንብረት ባለቤት መሆኑ /መሆኗ እንደተከበረ የሕግ ጥበቃም እንዳለው ደንግጓል፡፡ ይህ መብት የመሸጥ፣ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ ባለቤትነት የማዘወር ወይም የካሣ ክፍያ የመጠየቅ መብትን ይጨምራል እንዲሁም መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ ቢሆንም በይዞታ የመያዝና የመጠቀም መብት መኖሩን በዚሁ አንቀፅ ስር ተደንግጓል፡፡
ስለሆነም በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 2053 መሠረት አንድ ሰው በሕግ ሳይፈቀድለትና የቤቱ ባለቤት ወይም ባለይዞታ እንዲሁም የመሬቱ ባለይዞታ ሳይፈቅድለትና ያለመፍቀዱንም በግልፅ እየተናገረ እላይ በተጠቀሰው የቤት ሀብት ወይም የመሬት ይዞታ ከገባ የገባው ሰው ጥፋተኛ ነው፡፡
አንድ ሁለት ነጥቦችን እናንሳ የመጀመሪያው በሕግ ሳይፈቀድለት እንግሊዝኛው /without due legal authority/ የሚለው ነው፡፡
ለምሳሌ አንድ ፖሊስ ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ ይዞ ቢመጣና ለመበርበር ቤቱ ውስጥ ቢገባ አግባቡ በሕግ ሳይፈቅድለት አይባልም ፡፡ እንዲሁም አንድ ሰው የወንጀል ድርጊት ፈፀሞ ወደ አንድ ቤት ወይም መሬት ቢገባና ሌላ ሰው ወይም ፖሊስ ተከትሎት እዛ ቤት ወይም መሬት ቢገባ አግባቡ በሕግ ሳይፈቅድለት ነው አይባልም፡፡ በዚህ ሁኔታ ወደ ቤት ወይም መሬት የገባ ሰው የባለቤቱ ወይም የበላይዞታው ፍቃድ ባይኖር እንኳን ጥፋተኛ አይባልም፡፡
ሁለተኛው ነጥብ የማይፈቀድ መሆኑን በግልፅ እየተናገረ የሚለው ነው፡፡ ይህ ተቃውሞ በቃል ወይም በፅሑፍ ሊሆን ይችላል፡፡ በማጠረስ ሊሆን ይችላል? በሌላ በኩል ደግሞ ወደ መሬት ወይም ቤት መግባቱ የግድ በገቢው በራሱ መፈፀም አለበት? በቤት እንሰሳ አማካኝነት ቢሆንስ?ግዑዝ በሆነ ነገርስ ሊሆን ይችላል ? ለምሳሌ እኔ ቤት የበቀለ ዛፍ ቅርንጫፍ ወደ ጉረቤቴ ቢያልፍስ? ቆሻሻ ወደ ሌላ ሰው ቤት ቢጣልስ? ዛሬ ቴክኖሎጂው በሪሞት ኮንትሮል በሚንቀሳቀስ አንስተኛ አሸንጉሊት መኪና ወደ ሌላ ሰው ቤት ወይም መሬት ቢገባስ? ሰልጣኖች እስቲ በእነዚህ ጥያቄዎች ላይ ተወያዩባቸው፡፡
ንብረት ስለመደፈር ቁጥር /2054/
እላይ የተመለከትነው የማይንቀሰቀስ ንብረት ነው በዚህ ክፍል ደግሞ የምንቀሳቀስ ንብረትን አስመልክቶ ሕጉ ምን እንደሚል እንመለከታለን፡፡ እንደህ ዓይነት ንብረትንም አስመልክቶ ቁጥር 2054 በሕግ ሰይፈቀድለት የሚለውን ሐረግ ይጠቀማል፡፡ ስለሆነም ከላይ ለማስቀመጥ አንደሞከርነው አንድ ፖሊስ አንድን የሚንቀሳቀስ ንብረት በእግዚቢትነት ለመያዝ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይዞ ቢመጣና ንብረቱን ቢወስድ ሕገ ሳይፈቅድለት ወሰደ አያስኘውም፡፡ የግል ንብረቱ ወይም የባለይዞታው ፍቃድ እንኳን ሳይኖር ቢወሰድ ጥፋተኛ አያስብለውም፡፡
ሌላው ነጥብ አለመፍቀዱንም በመግለፅ ሲናገር የሚለውን በሌላ የፍትሐብሔር ቁጥር ለማስረዳት ቁጥር 1148/2/ መሠረት አንድ ሰው እጅ ያደረገው ነገር በንጥቂያ ከተወሰደበት የተወሰደበትን ነገር መመለስ እንደሚችል ይደነግጋል፡፡ ስለዚህ እንዳይነጥቅ የሚያደርገው ትግል ነገሩ እንዳይወሰድበት አለመፍቀዱን መግለጫ ነው ስለሆነም አንድ ሰው የሌላን ሰው ተንቀሳቃሽ ንብረት ሕግም ሳይፈቅድለት ወይም ባለቤቱ ወይም ባለይዞታው ሳይፈቅደለት የወሰደ እንደሆነ በቁጥር 2050 መሠረት ጥፋተኛ ነው፡፡
- Hits: 7331
- Details
- Category: Non-Contractual Liability (Tort Law)
ይህ ድርጊት በፍትሐብሔርም በወንጀል ሕግም ጥፋት ነው የወንጀል ሕግ ቁጥር 613ን ተመልከቱ እነዚህ ቁጥሮች በኘሬስና ሀሳብን በነፃ የመግለፅ ሕገ መንግስታዊ መብት ላይ የተደረጉ ገደቦች ናቸው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የኢፊዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 39 /3/ ስር የኘሬስና የሌሎች መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም የሥነ ጥበብ ፈጠራ ነፃነት መረጋገጡን ደንግጉ አንቀፅ 29/6/ ስር የሰውን ክብርና መለካም ስም ለመጠበቅ ሲባል ሕጋዊ ገደቦች በእነዚህ መብቶች ላይ ሊደነገጉ ይችላሉ ይላል፡፡ ስለሆነም በዚህ ገደብ አማካኝነት ጥበቃ የተደረገላቸው መልካም ስምና ክብር ናቸው፡፡
ይህን ያህል ለመግቢያ ካልን አንዳንድ ነጥቦችን አንስተን እንወያይ የስም ማጥፋት ድርጊት የሚፈፀምበት ሰው በሕይወት ያለ መሆን አለበት ይህም የሰም ማጥፋት የሚደረገው ስሙ የጠፋው ሰው እንዲጠላ ወይም እንዲዋረድ ወይም እንዲሳቅበትና ብሎም ስሙ በጠፋው ሰው ላይ ሌላው እምነት እንዳይኖረው ለማድረግ ወይም መልካም ዝናው ወይም የወደፊት ዕድሉ እንዲበላሽ ለማድረግ ነው፡፡ ይህን ያደረገ ጥፋተኛ ነው፡፡
አንዳንድ ምሳሌዎችን እንውሰድ፡፡ አንድ ሰው በወንጀል ሕግ የሚያስቀጣ ወንጀል ሳይፈፀም ሰርቷል ወይም አንድን የሕክምና ዶክተር ችሎታ እያለው ችሎታ የለውም ማለት አንድን ነጋዴ ሳይከስር ዕዳውን ለመክፈል አይችልም ማለት ተላላፊ በሽታ ሳይኖርበት እንዳለበት አድርጐ ማውራት ለስም ማጥፋት እንደምሳሌ ልንወስዳቸው እንችላለን፡፡ እንዲሁም ነገሩ እውነት ሆኖም ሰውዬውን ለመጉዳት ብለን ካደረግነው ድርጊታችን ጥፋት ይሆናል፡፡ /የወ.ሕግ 613/
አንድ ቃል ወይም አረፍተ ነገር ስም ማጥፋት ነው እንዲባል ቃሉ ወይም ዐረፍተ ነገሩ ለሶስተኛ ሰው ሊነገር ይገባል፡፡ ለሶስተኛ ሰው ሳይሆን ለራሱ ለተበዳዩ ቀጥታ የተነገረ እንደሆነ ስም ማጥፋት ሳይሆን ስድብ /insult/ ነው የሚሆነው፡፡
ስም የማጥፋት ድርጊት በቃል ሊሆን ይችላል፡፡ በፅሁፍና እንዲሁም በሌላ ዘዴ /ለምሳሌ ሌላ የኪነ ጥበብ ውጤት / ሊሆን ይችላል፡፡ ስም ማጥፋት አለ ለማለት የግድ የመጉዳት ሃሳብ መኖር የለበትም፡፡ 2045 /1/ እንዲሁም ቁጥር 2ዐ45/2/ ስር እንደተደነገገው በብድን ስም /group defamation/ የለም፡፡ ስለሆነም አንድ ሰው ስም አጠፋ ለማለት በንግግሩ ወይም በፅሁፍ የማንንም ሰው በተለይ ካልገለፀ በቀር ስም እንዳጠፋ አይቆጠርም፡፡ ሆኖም ግን ይህ አድራጉቱ ሌላ ሰው እንዲጉዳ አስቀድሞ ለመረዳት መቻሎ ከተረጋገጠ አላፊ ሊሆን እንደሚችል ቁጥር 2ዐ41/3/ ይደነግጋል፡፡
ቀጥለን መከላከያዎችን እንመለከታለን፡፡ የመጀመሪያው መከላከያ ቁጥር 2ዐ46 ስር የተደነገገው የሕዝብን ጥቅም በሚነኩ ጉዳዩች ላይ አሳብን መግለፅ ነው፡፡ ይህ የተገለፀው ሃሳብ ሌላውን ሰው በሕዝብ ዘንድ የሚያስወቅስ እንኳን ቢሆን እንደስም ማጥፋት አይቆጠርም ሆኖም ስም አጠፋ የተባለው ሰው ጠፋ የተባለው ሰው ላይ የሰጠው አስተያየት ሃሰት መሆኑን በእርግጠኝነት ካወቀ ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
ሁለተኛው መከላከያ ደግሞ የተነገረው ነገር እውነት መሆኑ ነው፡፡ ይህንንም በማስረጃ ማረጋገጥ አለበት ሆኖም ግን የተባለው ነገር እውነት ቢሆንም ስሙ ጠፋ የተባለውን ሰው ሆን ብሎ ለመጉዳት ቃሉን ወይም ዓረፍተ ነገሩን የተናገረው ተከሣሽ ጥፋተኛ ይሆናል፡፡ /በቁጥር 2ዐ47/
ሶስተኛ መከላከያ ደግሞ የማይደፈር መብት በእንግሊዝኛው /immunity/ የሚባለው ነው፡፡ ይህ መብት ለተወሰኑ ሰዎች የተሰጠ ነው ለፖርላማ አባላትና በፍርድ ቤት ፊት ለሚከራከሩ ወገኖች፡፡ አንድ የፖርላማ አባል በፖርላማ ውስጥ በሚደረግ ውይይት ሀሳቡን ሲገልፅ ግለሰብን አንስቶ ሊናገር ይችላል፡፡ ይህ ግን የፖርላማ አባሉን በስም ማጥፋት ተጠያቂ ሊያደርግው አይችልም፡፡
በፍርድ ሂደት ክርክርም የሰዎች ስም ሊነሳ ይችላል ለፍትህ አሰጣጥ የግድ ከሆነ ግለሰብ ሊነሳ ይችላል፡፡ ይህን ያነሳ ተከራካሪ በስም ማጥፋት ጥፋተኛ አይባልም፡፡
በተጨማሪም ቁጥር 2ዐ45/2/ ስር እንደተደነገገው በምክር ቤት ወይም በፍርድ ቤት የተደረገን ንግግርና ክርክር እንዳለ /እንደወረደ እንደሚባለው/ የገለጠ ሰውም በአላፊነት ሊጠየቅ የሚችለው ስሙ በውይይቱ ወይም በክርክሩ የተነሳውን ሰውዬ ለመጐዳት ብቻ አስቦ ከሆነ ብቻ ይሆናል፡፡
በመጨረሻም የስም ማጥፋት ተግባር በጋዜጣ ላይ ሊደረግ ይችላል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ስም አጠፋ የተባለው ሰው ፋጥተኛ የሚሆነው፣
- አንድን ሰው ለመጉዳት ብሎ አስቦ ከሆነ
- ይህንንም የፈፀመው በከፍተኛ ቸልተኝነት ከሆነ
- ወዲያውኑ መልሶ ይቅርታ ካልጠየቀ ነው፡፡
በሌላ አባባል ስም ማጥፋቱን የፈፀመ አንድን ሰው ለመጉዳት ሆን ብሎ አስቦ ሳይሆንና በቸልተኝነት ካልሆነ ይህንንም ካደረገ በኃላ ወዲያውኑ መልሶ ይቅርታ ከጠየቀ ጥፋተኛ አይሆንም፡፡ 2ዐ49/1/
ቁጥር 2ዐ49 /2/ እና /3/ የይቅርታው አጠያየቅ ጊዜ እና በምን ላይ መሆን አለበት የሚለውን ይመልሳሉ፡፡ በንዑስ ቁጥር ሁለት መሠረት ስም ማጥፋት ድርጊቱ የተደረገው ከአንድ ሳምንት በበለጠ ጊዜ በሚወጣ ጋዜጣ ላይ ከሆነ ይቅርታው የግድ የሚቀጥለው ጋዜጣ እስኪወጣ መጠበቅ የለበትም ይህ ከሆነ ተበዳዩ ይጉዳል፡፡ የጠፋውንም ስምና ጉዳቱንም ማስተካከል የማይቻልበት ደረጃ ላይ ሊደረስ ይችላል፡፡ ስለዚህ ይቅርታው ተበዳዩ በሚመርጠው ጋዜጣ ላይ መውጣት አለበት፡፡ ይህ ጋዜጣ የበዳዩም ሊሆን ይችላል፡፡ የሌላ ሰወ ጋዜጣም ሊሆን ይችላል፡፡ ተበዳዩ ጋዜጣ ካልመረጠ በንዑስ ቁጥር ሶስት መሠረት የስም ማጥፋቱ ነገርና የይቅርታው መጠየቁ የሚታተመው ስምን ማጥፋቱ በወጣበት ተከታይ ዕትም ላይ ይሆናል፡፡
- Hits: 10543
- Details
- Category: Non-Contractual Liability (Tort Law)
የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 17 ስር በሕገ ከተደነገገው ሥርዓት ውጭ ማንኛውም ሰው ወንድም ሆነ ሴት ነፃነቱን/ቷን አያጣም /አታጣም ተብሎ ተደንግጓል፡፡ በተጨማሪም ንዑስ አንቀፅ ሁለት ስር ማንኛውም ሰው በሕግ ከተደነገገው ሥርዓት ውጭ ሊያዝ እንደማይችል ተደንግጓል፡፡ ስለሆነም ይህ የነፃነት መብት ሕገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡
ይህም በመሆኑ ነው የፍትሐብሔር ቁጥር 2ዐ4ዐ/1/ አንድ ሰው ሕግ ሳይፈቀድለት ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የሌላውን ሰው ነፃነት /ሕገ መንግስታዊ ነፃነት/የነካና አንደተፈቀደለት መጠን ካንዱ ቦታ ወደ ሌላው እንዳይዘዋወር /የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 32/ ሰውየውን የከለከለ እንደሆነ ጥፋተኛ ነው በማለት የደነገገው፡፡
እዚህ ላይ አንዳንድ ነጥቦችን እንመልከት የመጀመሪያው ሕግ ሳይፈቀድለት የሚለው ነጥበ ነው፡፡ በሌላ አባባል አንድ ሰው ሌላውን ሰው ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወር መከልከል ሕግ የፈቀደለት ከሆነ ጥፋተኛ አይሆንም ማለት ነው፡፡ ለምሳሌ የፍሐብሔር ሕግ ቁጥር 265 እና በተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ /1992/ አንቀፅ 256 መሠረት አሳዳሪው አካለ መጠን ያልደረሰውን ልጅ መኖሪያ ቦታ የመወሰን ስልጣን ብቻ ሳይሆን አካለመጠን ያላደረሰ ልጅ ያለአሳዳሪው ፈቃድ ያን ቦታ ሊተው አይችልም፡፡ ስለሆነም አካለ መጠን ያለደረሰው ልጅ ያን ቦታ ትቶ የሄደ እንደሆነ አሳዳሪው መኖሪያ ቦታው ላይ እንዲመለስ ሊያስገድደው ይችላል፡፡ ስለዚህ አካለመጠን ያለደረሰውን ልጅ የመዘዋወር ነፃነት የመገደብ ስልጣን ለሞግዚቱ አለው ማለት ነው፡፡
እንደተፈቀደለት የሚለው ደግሞ መብራራት ያለበት ሁለተኛው ነጥብ ነው፡፡ በእንግሊዝኛ / As he is entitled to/ የሚለው ነው፡፡ የእንግሊዝኛው የተሻለ ይገልፀዋል፡፡ ይህ ሐረግ ቀጥታ ሕግ መንግስቱን ነው የሚያመለክተው የሕግ መንግስቱ አንቀፅ 32 /1/ ይህን መብት ሲደነግግ
“ማንኛውም ኢትዩጵያዊ ወይም በሕጋዊ መንገድ ሀገሪቱ ውስጥ የሚገኝ የውጭ ዜጋ በመረጠው የሀገሪቱ አካባቢ የመዘዋወር እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሀገር የመውጣት ነፃነት አለው” ብሏል፡፡
ስለሆነም አንድ ሰው ሕግ ሳይፈቅድለት ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወር የከለከለው ከሆነ ሕገ መንግስታዊ መብቱን መንካት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡
ሶስተኛው ነጥብ ደግሞ መከልከሉ የግድ ለረዥም ጊዜ መሆን የለበትም፡፡ በአማርኛው ለተወሰነ ጊዜ ይለዋል፡፡ እንግሊዝኛው ግን / Even for a short time/ በማለት ይገልፀዋል፡፡ ስለዚህ ይህ መከልከል የግድ ረዥም ጊዜ መሆን የለበትም ለአጭር ጌዜም ቢሆን ከልካዩን ጥፋተኛ ያደርጋል፡፡ እንዲሁም በተበዳይ /victim/ ሰውነት ላይ የግድ ጉዳት ማድረስ ይለበትም፡፡
መከላከያ ቁጥር / 2ዐ42 እና 2ዐ43/
የመጀመሪያ መከላከያ ቁጥር 2ዐ42 ስር የተደነገገው ነው፡፡ በዚህ ቁጥር መሠረት በሌላ ሰው ነፃነት ጣልቃ የገባው ሰው /ተከሣሽ/ ሁለት ነገሮችን ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡
የመጀመሪያው ነፃነቱ የተነካበት ሰው አንድ የወንጀል ድርጊት ሰርተዋል የሚለው ነው፡፡ ድርጊቱ የወንጀል ድርጊት መሆን አለበት፡፡ በፍትሐብሔር ሕግ ተጠያቂ ሊያደርግ የሚችል መሆን የለበትም፡፡ ሁለተኛው ነጥብ ደግሞ የወንጀል ድርጊቱን ሰርቶአል ብሎ ለማሰብ የሚያስችለው በቂ ምክንያት መኖሩን ማስረዳት አለበት፡፡ ይህን በምሳሌ እናስረዳ፡፡
አንድ ሰው በደም የተበከለ ቢላዋ ከደም በተጨማለቀ እጁ ይዞ ቢገኝ ይህን ሰው ወንጀል ሰርተዋል ብሎ ለማሰብ በቂ ምክንያት ሊሆን አይችልም ሆኖም ይህንኑ ሰው ሌሎች ሰዎች “ያዘው ያዘው” እያሉ እየጮሁ ቢያበሩት እነዚህ ሁሉ ተደምረው ይህ ሰው የወንጀል ድርጊት ፈፅሟል ብሎ ለማሰብ በቂ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ስለሆነም ይህን ሰው በቁጥጥር ስር ያለው ሰው ጥፋተኛ አይደለም ማለት ነው፡፡
ሌላ አንድ ምሳሌ እንጨምር አንዲት የቤት እመቤት ባለቤቷን በሌላ ሴት ትጠረጥረዋለች፡፡ እንበል አንድ ቀን ለቅሶ መሄዴ ነው ብሎ ሲወጣ በስውር ትከተለዋለች አባዋራውም አንዲት ጋለሞታ ቤት ይገባና በሩ ይዘጋል ሚስትም የተከረቸመውን በር እንዲከፍት ብታንኳኳ አይከፈትላትም በዚህ ጊዜ በሩን ከኃላ በቁልፍ ትቆልፍና ፖሊስ ትጠራለች ይህ ድርጊቷ ጥፋተኛ አያሰኛትም ምክንያቱም የመዘዋወር ነፃነቱ የተነካበት /ባሏ/ ወንጀል ሰርትዋል ብሏ ለማሰብ በቂ ምክንያት /ከሌላ ሴት ጋር በሩን መቆለፍ/ ስላላት ነው፡፡
ይህን ወንጀል ሰርቷል ተብሎ የተጠረጠረውን ሰው አሳሪው ወዴያውኑ ለባለሥልጣኑ /ፖሊስ/ ማስረከብ ይኖርበታል፡፡ በምሳሌው ላይ የተጠቀሰችው ሲትዩ በሩን በቁልፍ ከቆለፈች በኃላ ወዲያውኑ ፖሊስ ጠርታለች፡፡ ደግሞ የተጨማለቀውንም ሰውዩ ወዲያውኑ ለፖሊስ ማስርከብ ያስፈልጋል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን የዛን ሰውዩ የመዘዋወር ነፃነት የገደበው ሰው በቁጥር 2ዐ42 /2/ መሠረት ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
ሁለተኛው መከላከያ ቁጥር 2ዐ41 ስር የተደነገገው ነው በርግጥ ይህን ቁጥር ለማስረዳት እላይ የገለፅነው የአካለ መጠን ያለደረሰው ልጅ ሞግዚት ድርጊትን መጠቀም እንችላለን፡፡ ሆኖም አንድ ሌላ ምሳሌ እንውሰድ ፡፡
አንድ ሰው በሕግ አግባብ ቁጥጥር ስር የዋለ እንደሆነ የመዘዋወር ነፃነቱ ይገደባል፡፡ ይህንንም የሚያስፈፅም ሰው ለምሳሌ ፖሊስ ጥፋት ሰራ አይባልም ሕግ በሚፈቅድለት አኳኋን መሆን እንዳለበት ቁጥር 2ዐ41 ይደነግጋል፡፡ በሌላ አባባል በስልጣኑ ስር ያለን ሰው ማንገላታት የለበትም ነው ይህ እንደሆነም የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 21 ስር
“በጥበቃ ስር ያሎና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በሚጠብቁ ሁኔታዎች የመያዝ መብት አላቸው”
በማለት ደንግጓል፡፡ ስለሆነም የመዘዋዋር ነፃነታቸው የተገደበ ሰዎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በሚነካ ሁኔታ መያዝ የለባቸውም ይህን የጣሰ ሰው የተያዡን ሕገ መንግስታዊ መብት ስለሚነካ ጥፋተኛ ይሆናል፡፡
ሌላው መነሳት ያለበት ነጥብ ደግሞ ነፃነቱ የተነካበት ሰው ነፃነቱን በነካው ሰው ስልጣን ስር ያለ መሆን አለበት ይህ ስልጣን ከሕግ ወይም ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሊመነጭ ይችላል፡፡ ሞግዚቱ አካለ መጠን ባለደረሰ ልጅ ላይ ያለው ስልጣን የሚመነጨው ከሕግ /የፍትሐብሔር ሕገ ቁጥር 265 እና የተሻሻለው የቤተሰብ ሕግ ቁጥር 256/ ሲሆን የፖሊስ ደግሞ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወይም ከሕግ የመነጨ ሊሆን ይችላል፡፡
በመጨረሻም ዋስ የሆነ ሰው ዋስ የሆነለት ሰው ሊጠፋ ነው የሚያስብል መሰናዶ ማድረጉን የሚያሳምን በቂ ምክንያት ካለው የዚህን ሰው ነፃነት ቢነካበት ጥፋተኛ እንደማይሆን ቁጥር 2ዐ43 ይደነግጋል፡፡ ይህን ቁጥር በጥንቃቄ መመልከት የሚያሻ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ቀድሞ ግዞት ከሚባል ፅንሰ ሃሳብና ተግባር ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህን የሚልበት ምክንያት አንድ ሰው ለሌላ ሰው ዋስ የሚሆነው ዋስ የተገባለት ሰው ባንድ በተወሰነ ቦታ እንዲኖር ነው፡፡ ይህን ዋስትና የሚሰጠው ደግሞ ለመንግስት ባለስልጣናት ነው፡፡ ስለዚህ ዋሰ የተገባለት ሰው ዕዳ ኖሮበት ወይም የወንጀል ድርጊት በመፈፀም ተጠርጥሮ ሳይሆን ዋስ የሚኮንለት ባንድ በተወሰነ ቦታ እንዲኖር ነው፡፡ በቀድሞ ጊዜ ሰዎች ለንጉስ ነገስቱ የፖለቲካ ተቀናቃኝ ከሆኑ ወደ ገጠር ይወሰዱና አንድ አካባቢ ብቻ እንዲኖሩ ለዚህም ጠዋትና ማታ ፖሊስ ጣቢያ ሪፖርት እንዲያደርጉ ይደረጋሉ፡፡ ያን ስፍራ እንደማይለቁ ደግሞ ዋስ ይጠራሉ ያ ዋስ ነው እንግዲህ ግዞተኛው ቦታውን ለቆ ለማምለጥ መሰናዳቱን የሚያሳምን በቂ ምክንያት /ለምሳሌ ዕቃዎችን ያሰናዳ መንገድ ለመሩት ከሚችሎ ሰዎች ጋር ተነጋግሮ ቀብድ ከከፈለ ወዘተ/ ካለው ይህ ሰው እንዳይንቀሳቀስ ሊያግደው ይችላል፡፡ ይህን ማድረጉ ግን ጥፋተኛ አያደርገውም፡፡
ግዞት ግን በአሁኑ ጊዜ ቀርቷል፡፡ ሰዎች ለፖለቲካ አመለካከት የመያዝ ብቻ ሳይሆን ያን አመለካከት በሰላማዊ መንገድ የማራመድ በነፃ የፖሊቲካ ውድድር ተወዳድሮ የመንግስት ስልጣን የመያዝ መብታቸው በኢፊድሪ ሕገ መንግስት ተረጋግጧል፡፡ ይህን በማድጋቸው በግዞት በአንድ ቦታ እንዲቆዩ የሚደረጉበት ምክንያት የለም፡፡ /በአንድ ቦታ ለመቆየት ጥሩ ምሳሌ የሚትሆነን የበርማዋ ተወላጅ የናቢል ሰላም ተሸላሚዋ ሚስ ሳንሶዥ ናት ዛሬ ይህች ፖለቲከኛ በወታደራው ጁንታ ከቤቷ እንዳትወጣ /House arrest ይሉታል ፈረጆች/ ተወስኖባታል፡፡ ምናልባት ለዚህ አንድ ሰው ዋሰ እንዲሆኗት ጠርታ እንደሆነና ዋስ ልትጠሩ መሰናዶ ብታደርግ ዋስ የሆኗት ሰው ከዛ ቤት እንዳትወጣ ሊያደርጋት ይችላል፡፡
- Hits: 7293