በኢትዮጵያ የክስረት ሕግ ነጋዴ ከሰረ የሚባለው መቼ ነው? ከክሥረት ጋር የተያያዙ ወንጀሎችን ከወንጀል ሕጉ አንፃር

የንግድ ሥራ ኢትዮጵያውያን ከ 11 ኛው ምዕት አመት በፊት ባህር አቋርጠው ድንበር ሳይገድቧቸው ቤትና ሀገር ያፈራውን ከሌላው ለሙሙላትና ለመቀያየር አሁን የምንጠቀምበት አይነት ገንዘብ ከሌለበት ጊዜ ጀምሮ ንግድን ስራዬ ብለው ሲሰሩት ነበር። ረጅም ጉዞ በሚደረግብት የጥንቱ ንግድ ግን ሁሉ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ያላሰቡት ሽፍታ ከመንገድ ሁሉን ከነጋዴው መዝረፍ፣ የተቀየሩት ንብረቶች ፈላጊ በማጣት ነጋዴውን አትራፊ ከመሆን ይልቅ አክስሮት፣ ለአባዳሪዎች እንግልትና ሲሳይ ይዳርገው ነበር። የከሰረ ነጋዴ በማህበረሰቡ ዘንድ የሚቆጠረው በስራው የገጠመው ዕድለቢስነት በመሆን ሳይሆን መቅሰፍት የወረደበት ተደርጎ ነው። የከሰረን ነጋዴ በጎሪጥ መመልከት፣ ብድር እንኳ ቢጠይቅ ማንም የማያበድረው በመሆኑ የተነሳ አንዴ ወድቆ የማይነሳ ምሳር የበዛበት የሚሆንበት አጋጣሚ አለ።

  1274 Hits