ሰበር በአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ሥልጣን ላይ ያሰመረው ቀጭን መስመር

የአዲስ አበባ ፍርድ ቤት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣናቸውን የተመለከቱ የተለያዩ ክርክሮች ተነስተዋል፡፡ ዋናው ክርክር በተቋቋመበት ወቅት የተነሳው የሕገ መንግሥታዊነት ጭብጥ ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 78 እስከ 80 የዳኝነት አካሉን ሲያዋቅር በተለያዩ ደረጃዎች ያሉት የፌዴራልና የክልል ፍርድ ቤቶች እንደሚቋቋሙ በመግለጽ የፍርድ ቤት ሥልጣን ከመደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚወሰዱ ጊዜያዊና ልዩ ፍርድ ቤቶች እንደማይቋቋሙ ደንግጓል፡፡

  14462 Hits

የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ስልጣን ከአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ አንፃር

በአሁን ሰዓት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ማለትም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም የከተማ አስተዳደሮች ህጋዊ ጥንስሳቸው የአዲስ አበባ ከተማ ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያለው ሲሆን የድሬዳዋ ከተማ ደግሞ የቻርተር መሰረት ያለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት በኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 49 (1) መሰረት የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ነው በማለት ለከተማው እውቅና ሰጥቷል፡፡ የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 49 (2) የአዲስ አበባ ከተማ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለውም ደንግጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 የድሬዳዋ ከተማን በማቋቋም እራሱን በራሱ እንደሚያስተዳድር ደንግጓል፡፡

  14082 Hits