የዜግነት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ የቅድመ ሁኔታዎቹ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ:- ለአቶ ግዛው ለገሰ የተሰጠ ምላሽ

ስለ ዜግነት አዎጁ በፃፍኩት ጽሑፍ ላይ አቶ ግዛዉ ለገሰ የተባሉ የሕግ ባለሙያ የፃፉት ምላሽ ደርሶኝ ተመለከትኩት፡፡ (የአቶ ግዛው ለገሰ ጽሑፍን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ፡፡ ) በመጀመሪያ ጸሐፊው የሕግ ባለሙያ እንደመሆናቸውም ብሎም ጽሑፉን ያወጡት እሳቸው ስላልተስማሙበት የሕግ ጽሑፍ ምላሽ ለመስጠት እንደ መሆኑ አቶ ጀዋር መሐመድን ለመደገፍ አልፃፍኩትም ለማለት አቶ ጀዋር የራሱ ጉዳይ ብለው ጽሑፉን መጀመራቸው፤ በጽሑፉ ውስጥ ለተነሱ እያንዳንዱ ክርክሮች ተገቢውን የሕግ ክርክር ከማንሳት ይልቅ በአመዛኙ በተራ የአዋቃለሁ ባይነት ጉራ ተሞልተው እኩይ ሴራ የሚሉ ያልተገቡ ቃላቶች መጠቀማቸው ብሎም በጽሑፉ ውስጥ  ለድምዳሜቸው ማስረጃ አድርገው ስላቀረቡት የሕግ ግምት (presumption of law) ምንነት ያሉት ነገር አለመኖሩ እና ሃሳባቸው ልክ ስለመሆኑ የሚደግፍ የሕግ አስተምሮ ሳይጠቅሱ በደፈናው የሕግ ግምት ያልገባው የሚል የወረደ ምላሽ መስጠታቸው ከሙያ ሥነ-ምግባር የወጣ ተራ ብሽሽቅ የመሰለ መውረድ ሆኖ አግንቼዋለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ የመጀመሪየው ጽሑፍ በግልፅ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት ላይ ብቻ አተኮሮ እንደተፃፈ በተገለፀበት ሁኔታ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ስለሌላቸው እንደ በሕግ ዜግነት ስለማግኘት የመሳሰሉ ለምላሹ ፋይዳ በሌላቸው ዝርዝሮች ላይ ማተኮራቸውም አስቀድመው ላልተስማሙበት ጽሑፍ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በቂ እድል ነፍጓቸዋል ጊዜያቸው አጥንቱን በመጋጥ ላይ መዋል ሲገባው መረቅ ለመጠጣት ውሏል፡፡

  9694 Hits

‘ጠባቂ የሌለው ጠበቃ’ ጥቂት ስለ ኢትዮጵያ የሕግ ባለሞያዎች ማህበር

መነሻ ነጥብ

የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማህበር በ1958 ዓ.ም.በእድርና እቁብ አይነት ቅርጽ የተመሰረተ ድርጅት ነው፡፡ በሰዓቱ ከአርባ የማይበልጡ አባላት የነበሩት ሲሆን አባሎቹም በከተማይቱ አዲስ አበባ የጥብቅና አገልግሎት የሚሰጡ ነበሩ፡፡ ይህ ማህበር የተደራጀና የአባላቱን እንዲሁም የተከበረ ሙያ የሆነውን የጥብቅና ሙያ ለማስጠበቅና ለመጠበቅ ሳይሆን በማህበርተኞች መካከል ለሚፈጥሩ ማህበራዊና ሰዋዊ ችግሮች ለመረዳዳት ተብሎ የተመሰረተ ተቋም ነበር፡፡ ይህ ስብስብ በተመሰረተ በአመቱ ማለትም በ1959 ዓ.ም. በቀድሞው አጠራር የሀገር ግዛት ሚኒስቴር ተመዝግቧል፡፡ ከአብዮቱም በኋላ የኢትዮጵያ የጠበቆች ማህበር የሚለውን ስያሜ የያዘ ሲሆን በማህበሩ ውስጥ ጠበቆች፣ የሕግ መምህራን፣ ዳኞች፣ የሕግ ጉዳይ ፀሐፊዎች እና ሌሎችም አባል ሆነው ይሰሩ ነበር፡፡ ስሙን ቀይሮ የመጣው ማህበር የግብርና የዓላማ ለውጦችንም በማድረግ ደረጃውን የጠበቀ የጥብቅና ሙያ እንዲኖር ግንባር ቀደም ዓላማው አድርጎ ተነሳ፡፡ በወቅቱም ልክ አሁን እንዳለው ተመሳሳይ አሰራር የጥብቅና ፍቃድ በማሳየትና የአባልነት ክፍያ በመክፈል አባል መሆን ይቻል ነበር፡፡

  14273 Hits

ARTICLE REVIEW - Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy

Seyoum Yohannes, the Normative Basis for Decision on the Merits in Commercial Arbitration: the Extent of Party Autonomy, Mizan Law Review, Vol. 10, No.2, December 2016, p. 341 - 365 (You may download this article from Here)

The arbitration agreement is an indispensable precondition for domestic and international commercial arbitration.  This is due to the fact that an arbitration contract is a process through which parties in dispute freely appoint their own private judge in lieu of a state judge to settle their dispute.  Nonetheless, whether the parties are at liberty to set all matters as they like, including the law(s) that will be applied to their case, is an issue. On the other hand, whether the arbitrators could settle as per the principle of laws or according to law and whether they have full autonomy to revise or rewrite the arbitration agreement to settle the parties’ dispute is also an issue. Seyoum’s article examines Ethiopian laws from hereinabove mentioned issues’ perspective. 

  5354 Hits

ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃ (Provisional Interim measure) እና የፍርድ ቤት ሥልጣን

ይህ ጽሑፍ በግልግል ወይም በእርቅ የሚታዩ ጉዳዮችን ተከትሎ የሚሰጡ ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃዎች ወይም ትዕዛዝ ያላቸዉን የሕግ ማዕቀፍ እና ተግባራዊ አፈጻጸም የሚዳስስ ነዉ፡፡

በሕጉ ዘርፍ በአብዛኛዉ  ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃ (Provisional Interim measure) ሀሳብ ከግልግል ዳኝነት ሂደቶች ጋር ተያይዞ የሚነሳ  እንደሆነ ብዙ ድርሳኖች  ያወሳሉ፡፡ የብላክስ ሎዉ መዝገብ ቃላትም  ጊዜያዊ የመጠባበቂያ ትዕዛዝን ከዓለም ዓቀፍ የግልግል አሰራር ጋር በማገናኘት ትርጉም የሚሰጠዉ ሲሆን የግልግል ፍርድ ቤት  የሙግቱን ዉጤት ሊጎዳ የሚችልን ያልተገባ ተግባር ለመከላከል ከፍርድ በፊት የሚሰጠዉ ትዕዛዝ እንደሆነና በብሔራዊ ሕጎች ከሚሰጠዉ ጊዜያዊ የእግድ ትዕዛዝ (temporary injunction) ጋር አቻ እንደሆነ ይገልፀዋል፡፡ 

  3993 Hits