በኢትዮጵያ የቅጣት አወሳሰን ህጉና ልምዱ
Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Search Federal Laws
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
    • Quick links
  • Study On-line
  • know your rights
  • Blog
  • Lawyers
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Contact us
    • Professional Advice?
    • How to submit a blog post
  • Court Fee Calculator
    • Arbitration Fee Calculator
    • Judgement Interest Calculator
    • Vat Calculator
  • login
Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Search Federal Laws
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
    • Quick links
  • Study On-line
  • know your rights
  • Blog
  • Lawyers
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Contact us
    • Professional Advice?
    • How to submit a blog post
  • Court Fee Calculator
    • Arbitration Fee Calculator
    • Judgement Interest Calculator
    • Vat Calculator
  • login
Details
Category: Sentencing and Execution
30.Jul
Hits: 12258

በኢትዮጵያ የቅጣት አወሳሰን ህጉና ልምዱ

ቅጣትን የሚመለከቱ የወንጀል ህጉ ድንጋጌዎች ይዘት

በወንጀል ህጉ ሁለተኛ ታላቅ ክፍል (ልዩ ክፍል) ለእያንዳንዱ የወንጀል ድርጊት መነሻና መድረሻ ቅጣት ተቀምጠዋል፡፡ አብዛኛዎቹ የቅጣት መነሻና መድረሻዎች የሚከተሉትን ይመስላሉ፡፡

  • ከ1 አመት እስከ 10 አመት
  • ከ3 አመት እስከ 10 አመት
  • ከ5 አመት እስከ 15 አመት

በህጉ ልዩ ክፍል ከተመለከቱት ቅጣቶች በተጨማሪ አጠቃላይ የቅጣት አወሳሰን ድንጋጌዎች አሉ፡፡

  • አንቀጽ 88 (የቅጣቶች አወሳሰን)
  • አንቀጽ 84 (ጠቅላላ የቅጣት ማክበጃዎች)
  • አንቀጽ 82 (ጠቅላላ የቅጣት ማቅለያዎች)
  • አንቀጽ 85 (ልዩ የቅጣት ማክበጃዎች)
  • አንቀጽ 83 (ልዩ የቅጣት ማቅለያዎች)
  • ከአንቀጽ 179-189 (ቅጣቱ ሲከብደና ሲቀል ስለሚጣለው ቅጣት መጠን)
  • ከአንቀጽ 190-200 (ቅጣትን ስለመገደብ) ናቸው፡፡

እነዚህን የተለያዩ ድንጋጌዎች መሰረት አድርጎ ቅጣት እንዴት ይወሰናል? በወንጀል ህግ አንቀጽ 189(1) የሚከተለው ተደንግጎ እናገኛለን፡፡

‹በአንድ ወንጀል ላይ ቅጣት የሚያከብዱና የሚያቃልሉ ጠቅላላ ምክንያቶች በተደራረቡ ጊዜ ፍርድ ቤቱ አስቀድሞ ማክበጃ ምክንያቶቹን ከግምት በማስገባት ያከብድና ቀጥሎ የሚያቃልሉትን ምክንያቶች መሰረት አድርጎ ቅጣቱን ያቃልላል›

ይላል፡፡

ከዚህ መረዳት እንደምንችለው መጀመሪያ ለማክበድ ከየት ይነሳል? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ ያደርገናል፡፡ ስለሆነም በግልጽ ባይቀመጥም ዳኛው፣

  • በቅድሚያ መነሻ ማስቀመጥ እንደሚኖርበት፣
  • ቀጥሎ ማክበጃ ምክንያቶች ከአሉ ቅጣቱን ማክበድ እንደሚኖርበት፣
  • ቀጥሎ ማቅለያ ምክንያቶች ከአሉ ቅጣቱን ማቅለል እንደሚኖርበት፣

ያስረዳል፡፡

ይሁንና፣

  • መነሻው ስንት ይሁን? በሕጉ መልስ የለም፡፡
  • ማክበጃዎች ሲኖሩ በምን ያህል ሊከብድ ይገባል ? በሕጉ መልስ የለም፡፡
  • ማቅለያዎች ሲኖሩ በምን ያህል ሊቀል ይገባል ? በሕጉ መልስ የለም፡፡

ስለሆነም በወንጀል ህጉ የተቀመጡትን የቅጣት ድንጋጌዎችና ስለቅጣት አወሳሰን የተቀመጡት ድንጋጌዎች በፍርድ ቤት የሚሰጡ ቅጣቶች፣

  • ወጥነት፣
  • ትክክለኛነት ያለው፣

ለማድረግ የሚያስችሉ አይደሉም፡፡

የቅጣት ውሳኔዎች ግምገማ

ቅጣት የተሰጠባቸው መዝገቦችን ስንመለከት፣

አቃቤ ህግ፣

  • ቅጣቱ ከብዶ ይወሰን፣
  • ተመጣጣኝ ቅጣት ይሰጠው፣

ከሚል ባለፈ ከብዶ ሲባል ከባዱ ምን ያህል እንደሆነ፣

  1. መነሻው ስንት ሆኖ ሊከብድ እንደሚገባ፣
  2. ተመጣጣኝ የሚሆነው ምንእንደሆነ ፣

የሚያመለክቱ አይደሉም፡፡

በተከሳሽ በኩል የሚቀርቡ የቅጣት አስተያየቶችም ጥቅል ሆነው ከሚቀርቡ በስተቀር ተመሳሳይ ችግር ያለባቸው ናቸው፡፡ዳኛው ቅጣትን ሲወስንም፣ ቅጣትን ለማክበድ፣

  • የወንጀል ሪከርድ አለው
  • የወንጀል አፈጻጸሙ አደገኛነት አለው፣
  • ድርጊቱ የተፈጸመው በአፍቅሮ ንዋይ በመሆኑ የሚሉ ምክንያቶችን በመጥቀስ፣

ቅጣቱን ለማቅለል

  • የወንጀል ሪከርድ የለውም ስለሆነም አደገኛ አይደለም፡፡
  • የቤተሰብ አስተዳዳሪ ነው፡፡ ወዘተ የሚሉ ምክንያቶችን በመጥቀስ፣

ቅጣት ይወስናል፡፡

ይሁንና ዳኞች እነዚህን ምክንያቶች ይጥቀሱ እንጂ፣

  • በየትኛውም መዝገብ ቅጣቱን ለመወሰን መነሻው ስንት መሆን እንዳለበት ተመልክቶ አይታይም፡፡
  • በማክበጃነት የቀረቡትንና በማቅለያነት የቀረቡትን ምክንያቶች የሚቀበለውና የሚቀበሉትንና የማይቀበሉትን ከለዩ በኋላ፣ ከምክንያቶቹ ጋር ግንኙነቱን ለማስረዳት በማይቻል መልኩ በጥቅሉ የቅጣቱ መጠን ይቀመጣል፡፡

ስለሆነም፣

  • መነሻ የቅጣት መጠኑ ስንት እንደሆነ፣
  • በማክበጃነት የተቀመጡት ምክንያቶች ቅጣቱን በማክበድ ያላቸው አስተዋጽኦ እንዲሁም
  • ማቅለያ ምክንያቶች እንዴት አገልግለው ቅጣቱ እንደቀለለ፣

ለማወቅ አይቻልም፡፡

ከዚህ አጠቃላይ ግንዛቤ በመነሳት በአገራችን ቅጣት አወሳሰን ምክንያታዊነት የጎደለው፣ በእርግጥም የተጣለው ቅጣት አግባብነት ያለው መሆኑን ለማስረዳት አይቻልም፡፡ በዚህም ምክንያት፣

በአንድ ዳኛ በተለያየ ጊዜ ወይም በተለያዩ ዳኞች ተቀራራቢና ተመሳሳይ ለሆኑ ወንጀሎች የሚሰጡ የተለያዩ ቅጣቶች መኖራቸው፣

ከዚህም የተነሳ በቅጣት አወሳሰን ተገማችነት የሌለው መሆኑ፣

ቅጣት አወሳሰን ግልጽነት የሌለውና በፍትህ አካላቱ ባለሙያዎች ላይ ተጠያቂ ለማድረግ የማያስችል ሆኖ እናገኘዋለን::

Read Next

  • Key Reforms in the 2021 Commercial Code
    31.Oct
  • "የግልግል ዳኝነት በኢትዮጵያ ሕግ" የሚል ርዕስ ያለው አዲስ የሕግ መጽሐፍ በገበያ ላይ
    17.Mar
  • Administrative Law (30)
  • African Human Rights Law (18)
  • African Union Law (6)
  • Alternative Dispute Resolution (33)
  • Agency (6)
  • Bankruptcy Law (4)
  • Civil Procedure (12)
  • Conflict Laws (3)
  • Constitutional Law (5)
  • Construction Law (3)
  • Contract Law (7)
  • Criminal Law (10)
  • Criminal Procedure (6)
  • Criminology (4)
  • Customary Law (4)
  • Employment and Labor Law (17)
  • Environmental Law (5)
  • Evidence Law (6)
  • Family Law (5)
  • Gender and the law (4)
  • Human Right Law (5)
  • Humanitarian Law (7)
  • Insurance, Banking and Negotiable Instrument Law (6)
  • Intellectual Property Law (4)
  • International Organizations (4)
  • Introduction to law and Law of Persons (4)
  • Investment Law (10)
  • Islamic Law (2)
  • Judgment writing (0)
  • Jurisprudence (1)
  • Land Law (10)
  • Law and Development (0)
  • Legal History (0)
  • Legal Profession (0)
  • Legal Research Methods (0)
  • Legal Writing (0)
  • Legislative Drafting (0)
  • Maritime Law (3)
  • Non-Contractual Liability (Tort Law) (10)
  • Pre-Trial Skills and Trial Advocacy (0)
  • Property Law (27)
  • Public Enterprises and Cooperatives (0)
  • Public International Law (0)
  • Refugee Law (0)
  • Sales and Security Devices (0)
  • Sentencing and Execution (4)
  • Succession Law (6)
  • Taxation Law (4)
  • Trade and Business Organizations (2)
  • Administrative Contract (16)
  • Federalism (3)
Copyright © 2026 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Legal Services LLP