Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Search Federal Laws
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
    • Quick links
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Contact us
    • Professional Advice?
    • How to submit a blog post
  • login
Abyssinia Law Abyssinia Law
  • Home
  • Laws
    • Search Federal Laws
    • Regional Laws
    • Constitutions
    • Audio Legal Resources
  • Decisions
    • Cassation Decisions by Volume
    • Cassation Decisions Database
    • FFI Court Commercial Bench Decisions
  • Blog
  • Resources
    • Researches Papers
    • Policies and Strategies
    • Codes, Commentaries and Explanatory notes
    • Legal Forms
    • Bench Books
    • Human Right Documents
    • Modules and Materials
    • About Our Laws
    • Quick links
  • Study On-line
  • know your rights
  • Lawyers
  • About Us
    • Who Are We
    • Our Partners
    • Advertise with Us
    • Privacy Policy
    • Contact us
    • Professional Advice?
    • How to submit a blog post
  • login
Details
Category: Property Law
13.Feb
Hits: 8457

ልዩ የጋራ ባለሃብትነት (Special joint ownership)

ሁለተኛው የጋራ ባለሃብትነት ግንኙነት ልዩ የጋራ ባለሃብትነት ሲሆን የዚህ መብት መሰረት (subject matter) የጋራ ግንብ፤ አጥር፡ አፓርትማ ወ.ዘ.ተ. ሊሆን ይችላል፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ.1209(1)) ሰዎች በዚህ ዙርያ የሚኖራቸውን መብት በማስመልከት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 40(7) ማንኛወም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም ለሚያደርገው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው፡፡ . . ."  በማለት ሁለት በአዋሳኝ የሚገናኙ ሰዎች በጋራ መሬታቸው ለሚገነቡት ግንብ፡ አጥር ወይም አፓርትማ የጋራ ባለቤትነት መብት እንዳላቸው በማረጋገጥ ይህን መብታቸውን የመሸጥ የመለወጥ የማውረስና የመሬቱ ተጠቃሚነት ሲቋረጥ ንብረቱን የማንሳት ባለቤትነቱን የማዛወር ወይም የካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው ህገ-መንስታዊ እውቅና የተሰጠው የንብረት መብት ነው፡፡ ልዩ የጋራ ባለሃብትነት ከንብረት ህግ አኳያ ሲታይ መብቱም ሆነ ግዴታው የሚመነጨው የጋራ ግንብ፣ አጥር፣ ኮሪደር (በረንዳ) ወ.ዘ.ተ. በሚጠቀሙ አጐራባች ባለሃብቶች መካከል ከሚደረግ ውል ወይም የህግ ግምት ነው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1259 ፤ 1281 እና 1282) ከዚህ ውልና የህግ ግምት የንብረት ህግ ሊመነጩ የሚችሉ የልዩ የጋራ ባለሃብቶች መብቶችና ግዴታዎች ያሉ ሲሆን መብቶችን በቅድሚ ስንመለከት ፡-

 

የልዩ የጋራ ባለሃብቶች መብትና ግዴታ

 

የጋራ ግንብ (common wall) ፣ አጥር፣ መውጪያና መግብያ (ኮሪደር) የሚኖራቸው ሰዎች ከተጋሪው ጋር አብሮ ለመስራትና ለመገልገል የመደራደርና አብሮ ሰርቶ አብሮ የጋራ ንብረት በሆነው ነገር የጋራ የባለቤትነት መብት እንዲኖራቸው ማድረግ ይችላሉ፡፡ አንደኛው ወገን ይሁንታ ካልሰጠ ለማስገደድ ባይቻልም ሌሎቹ ተጐራባቶች የጋራ የሆነው ግንብ፣ አጥር፣ ኮሪደር ብቻቸውን ሆነው በጋራ መሬቱ ላይ የመገንባትና የንብረቱ ባለቤት የመሆን መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ.  1278 እና 1279(2))

ተገንብቶ የቆየ የጋራ ግንብ በከፊል ወይም በሙሉ በሚፈርስበት ግዜ አንደኛው ተጋሪ ሌላኛውን እንስራው ብሎ መጠየቅ ያለበት ቢሆንም ሌላው ተጋሪ ይሁንታን ካልሰጠ አንደኛው ወገን እንደገና ሊገነባውና የባለቤትነት መብቱ ለብቻው እንዲሆን በማድረግ ያለውን የጋራ ነው የሚል የህግ ግምት እንዲቀር ያደርጋል፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1200 እና 1201፣ 1279) እዚህ ላይ ሊነሳ የሚችለው ጥያቄ ብቸኛ ባለቤት የሚሆነው በራሱ መሬት ላይ ሲገነባው ነው ወይስ በእንቢተኛው ተጋሪ መሬት ላይም ሲገነባ ብቸኛ ባለቤት መሆን ይችላል? የሚል ነው:: ህጉ ለዚህ በፍ/ብ/ሀ/ቁ 1279(2) ላይ የሚሰጠው ግልፅ መልስ ስላለ ብዙ የሚከራክር አይደለም ፡፡

በጋራ የሚገለገሉበት ህንፃ በጋራ መሬት ላይ ያረፈ ነው ተብሎ የመገመትና የጋራ ሃብታቸው እንደሆነ ተደርጎ የመገመት መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1200(1) 1281፤)

የጋራ ባለሃብቶቹ ማህበር (syndicate) የማቋቋም፣ አስተዳዳሪ የመምረጥ፣ በሐራጅ እንዲሸጥ የመጠየቅና በማህበር ሰብሰባዎች ላይ ድምፅ የመስጠትና በውሳኔው ካልተስማሙ ይግባይ ብለው ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት የመሄድ መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1293፣1295፣ 1298፣ 1303፣ 1304፣  1305)

ልዩ የጋራ ሃብቱን ለማደስ ወይም እንደገና ለመገንባት የወጣውን ወጪ ከሌሎቹ የጋራ ባለሃብቶቹ በውል ወይም ከውል ውጭ በክስ የመጠየቅ መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1306፣ 1308 እና 1297)

የልዩ ባለሃብቶች ግዴታዎችን በተመለከተ ያየን እንደሆነም ፡-

የልዩ የጋራ ባለሃብቶች መብትና ግዴታ የሚወሰነው ውል በፅሑፍ የማድረግ ግዴታ አላቸው፡፡ ይህን ፎርም ተከትለው ስምምነቱን ካልፈፀሙ ግን ህጋዊ ውጤት አይኖረውም ወይም ዋጋ አልባ (void) ነው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1283)

ውሉ ንብረቱ በሚገኝበት(situs) የውል መዝጋቢ (notary) ወይም የፍርድ መዝገብ (court registry) መቀመጥና ወራሾች፣ የወደፊት ገዢዎች፣ ወኪሎች፣ የግብር ባለስልጣንና ዋስትና የተሰጣቸው ባለሀብቶች (secured creditors) እንዲያዩት በሚችል አኳኃን መቀመጥ አለበት፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1284)

የጋራ ባለሃብቶቹ ህንፃው የተሰራበትን አላማና የተጋሪዎችን መብት የማክበር ግዴታ አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1290 እና 1291)

መብትን ማስከበር እንዳለ ሁሉ ግዴታዎችን የመሸከም ግዴታ ስለሚኖርባቸው ልዩ የጋራ ሃብቱን እንዳለ ጠብቆ የማቆየት፣ የማደስ እና የማስተዳደር ግዴታ አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1292)

ልዩ የጋራ ሃብት ከሆነ ንብረት ከፊሉ ቢፈረስና ማኅበሩ እንዲሰራ ቢወስን

 

ልዩ የጋራ ባለሀብትነት ቀሪ ስለመሆን

ልዩ የጋራ ባለሃብትነት መብት መሰረቱ የባለሃብቶቹ ውል ሲሆን ይህ ሰምምነት እንደሁሉም ህግ ፊት ዋጋ ያላቸው ተግባራት በአንድ ወቅት ተወልዶ ተጋሪዎች በመብታቸው ሲሰሩበት ከቆዩ በኃላ ቀሪ የሚሆኑባቸው ሁኔታዎችም አሉ፡፡ ከነዚህም ጥቂቶችን ወስደን ያየን እንደሆነ፡-

§የጋራ ባለሃብቱ የነበረውን የባለቤትነት መብት (ownership right) በሽያጭ ወደ ሌላ ሰው ሲያስተላለፍ መብቱ ወደ ገዢው የሚተላለፍ ቢሆንም ከሻጭ አኳያ ሲታይ ግን በሽያጭ ውሉ አማካይነት በጋራ ንብረቱ ላይ የነበረውን መብት ስለሚያጣ መብቱ ቀሪ ይሆናል ፡፡

§የጋራ ባለሃብቱ ሲሞት በጋራ ንብረቱ ላይ የነበረው መብትና ግዴታ ወደ ወራሾች የሚተላለፍ ቢሆንም ከሟቹ አንፃር ሲታይ ግን በሞት ምክንያት ውሉ ቀሪ ይሆናል፡፡

§ልዩ የጋራ ሃብቱ ያረፈበት መሬት ለህዝብ ጥቅም ተብሎ ሲለቀቅ የጋራ ባለሃብቶቹ መብት በመሬቱ ላይ ባሰፈሩት ግንባታ ላይ ስለሚመሰረት በሚለቁበት ግዜ የመልቀቂያ ካሳ የማግኘት ህገ-መንግስታዊ መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በንብረቱ የነበራቸው የጋራ ባለሃብትነት መብት ግን ቀሪ ይሆናል፡፡

§መልሶ እስካልተገነባ ድረስ በጋራ ሃብቱ ላይ ጠቅላላ (total destruction) በሚያጋጥምበት ግዜ ለውሉ መመስረት ምክንያት የሆነው ንብረት ስለማይኖርና በሌለ ንብረት ላይ የጋራ ባለቤትነት መብት ሊመሰረት ስለማይችል የንብረት መብታቸው ቀሪ ይሆናል፡፡

 

ስለዚህ የጋራ የባለሃብትነት መብት መሰረት ግዙፍነት ያላቸው የሚንቀሳቀሱ  ወይም የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች እና ግዙፍነት የሌላቸው ንብረቶች ናቸው፡፡ የመብቱ ዓይነት ተራ የጋራ ባለሃብትነት መብት ይሁን ልዩ የጋራ ባለሃብትነት መብት መሰረታቸው አሁን ባለው የፍ/ብሄር ፍትህ ስርዓት ዓይን ሲታይ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት አንቀጽ 40(1) (7)፣ 31 እና 89(1) ላይ የተደነገጉት ህገ-መንግስታዊ መርሆች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ማለት ግን ህገ-መንግስቱ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን የፍ/ብሄር ህግ እነዚህን የህገ-መንግስቱን መርሆች መሰረት አድርገን መተርጎምና በስራ ላይ ማዋል የለብንም ማለት እንዳልሆነ ግልፅ ሊሆን ይገባል ፡፡ ከፍ ብለን እንዳየነው በፍ/ ብሄር ህጉም ቢሆን እምብዛም ከህገ-መንግስታዊ መርሁ ባልተቃረነ ወይም ባልራቀ መልኩ የንብረት መብት ጥበቃ ተደርጐላቸው የምናገኛቸው በርካታ የጋራ የባለሃብትነት መብቶችና ግዴታዎች አሉ፡፡ ይህ የሚያሳየው የፍ/ብሄር ህጉ እነዚህ መብቶችና ግዴታዎች የሚተዳደሩበት ስርዓትና በመጨረሻም ቀሪ የሚሆኑበት ሁኔታ ያካተተ አስከሆነ ድረስና ህገ-መንግስቱን መሰረት በማድረግ የወጣ አዲስ የንብረት ህግ እስኪኖረን ድርስ ያለውን ህግ ከህገ-መንግስቱ ጋር አጣጥመን በስራ ላይ ማዋል ያለብን መሆኑ ነው ፡፡ የጋራ ባለሀብትነት መብት የንብረት መብት እንደመሆኑ መጠን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት ከወጣ በኋላ በሌሎች የንብረት ነክ ህጎችም ተካቶ የምናገኘው መብት መሆኑን ከፍ ብለን ካየናቸው አዋጆች መረዳት የሚቻል  ቢሆንም ካለንበት ህገ መንግስታዊ ስርዓት ጋር የተጣጣመና የተሟላ የንብረት ህግ የሚኖረን ግን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት መርሆችን መሰረት ያደረገ አዲስና ወጥ የሆነ የንብረት ህግ ሲታወጅ ነው፡

  ልዩ የጋራ ባለሃብትነት (Special joint ownership)

ሁለተኛው የጋራ ባለሃብትነት ግንኙነት ልዩ የጋራ ባለሃብትነት ሲሆን የዚህ መብት መሰረት (subject matter) የጋራ ግንብ፤ አጥር፡ አፓርትማ ወ.ዘ.ተ. ሊሆን ይችላል፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ.1209(1)) ሰዎች በዚህ ዙርያ የሚኖራቸውን መብት በማስመልከት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 40(7) ማንኛወም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም ለሚያደርገው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው፡፡ . . ."  በማለት ሁለት በአዋሳኝ የሚገናኙ ሰዎች በጋራ መሬታቸው ለሚገነቡት ግንብ፡ አጥር ወይም አፓርትማ የጋራ ባለቤትነት መብት እንዳላቸው በማረጋገጥ ይህን መብታቸውን የመሸጥ የመለወጥ የማውረስና የመሬቱ ተጠቃሚነት ሲቋረጥ ንብረቱን የማንሳት ባለቤትነቱን የማዛወር ወይም የካሳ ክፍያ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው ህገ-መንስታዊ እውቅና የተሰጠው የንብረት መብት ነው፡፡ ልዩ የጋራ ባለሃብትነት ከንብረት ህግ አኳያ ሲታይ መብቱም ሆነ ግዴታው የሚመነጨው የጋራ ግንብ፣ አጥር፣ ኮሪደር (በረንዳ) ወ.ዘ.ተ. በሚጠቀሙ አጐራባች ባለሃብቶች መካከል ከሚደረግ ውል ወይም የህግ ግምት ነው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1259 ፤ 1281 እና 1282) ከዚህ ውልና የህግ ግምት የንብረት ህግ ሊመነጩ የሚችሉ የልዩ የጋራ ባለሃብቶች መብቶችና ግዴታዎች ያሉ ሲሆን መብቶችን በቅድሚ ስንመለከት ፡-

 

የልዩ የጋራ ባለሃብቶች መብትና ግዴታ

 

የጋራ ግንብ (common wall) ፣ አጥር፣ መውጪያና መግብያ (ኮሪደር) የሚኖራቸው ሰዎች ከተጋሪው ጋር አብሮ ለመስራትና ለመገልገል የመደራደርና አብሮ ሰርቶ አብሮ የጋራ ንብረት በሆነው ነገር የጋራ የባለቤትነት መብት እንዲኖራቸው ማድረግ ይችላሉ፡፡ አንደኛው ወገን ይሁንታ ካልሰጠ ለማስገደድ ባይቻልም ሌሎቹ ተጐራባቶች የጋራ የሆነው ግንብ፣ አጥር፣ ኮሪደር ብቻቸውን ሆነው በጋራ መሬቱ ላይ የመገንባትና የንብረቱ ባለቤት የመሆን መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ.  1278 እና 1279(2))

ተገንብቶ የቆየ የጋራ ግንብ በከፊል ወይም በሙሉ በሚፈርስበት ግዜ አንደኛው ተጋሪ ሌላኛውን እንስራው ብሎ መጠየቅ ያለበት ቢሆንም ሌላው ተጋሪ ይሁንታን ካልሰጠ አንደኛው ወገን እንደገና ሊገነባውና የባለቤትነት መብቱ ለብቻው እንዲሆን በማድረግ ያለውን የጋራ ነው የሚል የህግ ግምት እንዲቀር ያደርጋል፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1200 እና 1201፣ 1279) እዚህ ላይ ሊነሳ የሚችለው ጥያቄ ብቸኛ ባለቤት የሚሆነው በራሱ መሬት ላይ ሲገነባው ነው ወይስ በእንቢተኛው ተጋሪ መሬት ላይም ሲገነባ ብቸኛ ባለቤት መሆን ይችላል? የሚል ነው:: ህጉ ለዚህ በፍ/ብ/ሀ/ቁ 1279(2) ላይ የሚሰጠው ግልፅ መልስ ስላለ ብዙ የሚከራክር አይደለም ፡፡

በጋራ የሚገለገሉበት ህንፃ በጋራ መሬት ላይ ያረፈ ነው ተብሎ የመገመትና የጋራ ሃብታቸው እንደሆነ ተደርጎ የመገመት መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1200(1) 1281፤)

የጋራ ባለሃብቶቹ ማህበር (syndicate) የማቋቋም፣ አስተዳዳሪ የመምረጥ፣ በሐራጅ እንዲሸጥ የመጠየቅና በማህበር ሰብሰባዎች ላይ ድምፅ የመስጠትና በውሳኔው ካልተስማሙ ይግባይ ብለው ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት የመሄድ መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1293፣1295፣ 1298፣ 1303፣ 1304፣  1305)

ልዩ የጋራ ሃብቱን ለማደስ ወይም እንደገና ለመገንባት የወጣውን ወጪ ከሌሎቹ የጋራ ባለሃብቶቹ በውል ወይም ከውል ውጭ በክስ የመጠየቅ መብት አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1306፣ 1308 እና 1297)

የልዩ ባለሃብቶች ግዴታዎችን በተመለከተ ያየን እንደሆነም ፡-

የልዩ የጋራ ባለሃብቶች መብትና ግዴታ የሚወሰነው ውል በፅሑፍ የማድረግ ግዴታ አላቸው፡፡ ይህን ፎርም ተከትለው ስምምነቱን ካልፈፀሙ ግን ህጋዊ ውጤት አይኖረውም ወይም ዋጋ አልባ (void) ነው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1283)

ውሉ ንብረቱ በሚገኝበት(situs) የውል መዝጋቢ (notary) ወይም የፍርድ መዝገብ (court registry) መቀመጥና ወራሾች፣ የወደፊት ገዢዎች፣ ወኪሎች፣ የግብር ባለስልጣንና ዋስትና የተሰጣቸው ባለሀብቶች (secured creditors) እንዲያዩት በሚችል አኳኃን መቀመጥ አለበት፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1284)

የጋራ ባለሃብቶቹ ህንፃው የተሰራበትን አላማና የተጋሪዎችን መብት የማክበር ግዴታ አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1290 እና 1291)

መብትን ማስከበር እንዳለ ሁሉ ግዴታዎችን የመሸከም ግዴታ ስለሚኖርባቸው ልዩ የጋራ ሃብቱን እንዳለ ጠብቆ የማቆየት፣ የማደስ እና የማስተዳደር ግዴታ አላቸው፡፡ (ፍ/ብ/ህ/ቁ. 1292)

ልዩ የጋራ ሃብት ከሆነ ንብረት ከፊሉ ቢፈረስና ማኅበሩ እንዲሰራ ቢወስን

 

ልዩ የጋራ ባለሀብትነት ቀሪ ስለመሆን

ልዩ የጋራ ባለሃብትነት መብት መሰረቱ የባለሃብቶቹ ውል ሲሆን ይህ ሰምምነት እንደሁሉም ህግ ፊት ዋጋ ያላቸው ተግባራት በአንድ ወቅት ተወልዶ ተጋሪዎች በመብታቸው ሲሰሩበት ከቆዩ በኃላ ቀሪ የሚሆኑባቸው ሁኔታዎችም አሉ፡፡ ከነዚህም ጥቂቶችን ወስደን ያየን እንደሆነ፡-

§የጋራ ባለሃብቱ የነበረውን የባለቤትነት መብት (ownership right) በሽያጭ ወደ ሌላ ሰው ሲያስተላለፍ መብቱ ወደ ገዢው የሚተላለፍ ቢሆንም ከሻጭ አኳያ ሲታይ ግን በሽያጭ ውሉ አማካይነት በጋራ ንብረቱ ላይ የነበረውን መብት ስለሚያጣ መብቱ ቀሪ ይሆናል ፡፡

§የጋራ ባለሃብቱ ሲሞት በጋራ ንብረቱ ላይ የነበረው መብትና ግዴታ ወደ ወራሾች የሚተላለፍ ቢሆንም ከሟቹ አንፃር ሲታይ ግን በሞት ምክንያት ውሉ ቀሪ ይሆናል፡፡

§ልዩ የጋራ ሃብቱ ያረፈበት መሬት ለህዝብ ጥቅም ተብሎ ሲለቀቅ የጋራ ባለሃብቶቹ መብት በመሬቱ ላይ ባሰፈሩት ግንባታ ላይ ስለሚመሰረት በሚለቁበት ግዜ የመልቀቂያ ካሳ የማግኘት ህገ-መንግስታዊ መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በንብረቱ የነበራቸው የጋራ ባለሃብትነት መብት ግን ቀሪ ይሆናል፡፡

§መልሶ እስካልተገነባ ድረስ በጋራ ሃብቱ ላይ ጠቅላላ (total destruction) በሚያጋጥምበት ግዜ ለውሉ መመስረት ምክንያት የሆነው ንብረት ስለማይኖርና በሌለ ንብረት ላይ የጋራ ባለቤትነት መብት ሊመሰረት ስለማይችል የንብረት መብታቸው ቀሪ ይሆናል፡፡

 

ስለዚህ የጋራ የባለሃብትነት መብት መሰረት ግዙፍነት ያላቸው የሚንቀሳቀሱ  ወይም የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች እና ግዙፍነት የሌላቸው ንብረቶች ናቸው፡፡ የመብቱ ዓይነት ተራ የጋራ ባለሃብትነት መብት ይሁን ልዩ የጋራ ባለሃብትነት መብት መሰረታቸው አሁን ባለው የፍ/ብሄር ፍትህ ስርዓት ዓይን ሲታይ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት አንቀጽ 40(1) (7)፣ 31 እና 89(1) ላይ የተደነገጉት ህገ-መንግስታዊ መርሆች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ ማለት ግን ህገ-መንግስቱ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን የፍ/ብሄር ህግ እነዚህን የህገ-መንግስቱን መርሆች መሰረት አድርገን መተርጎምና በስራ ላይ ማዋል የለብንም ማለት እንዳልሆነ ግልፅ ሊሆን ይገባል ፡፡ ከፍ ብለን እንዳየነው በፍ/ ብሄር ህጉም ቢሆን እምብዛም ከህገ-መንግስታዊ መርሁ ባልተቃረነ ወይም ባልራቀ መልኩ የንብረት መብት ጥበቃ ተደርጐላቸው የምናገኛቸው በርካታ የጋራ የባለሃብትነት መብቶችና ግዴታዎች አሉ፡፡ ይህ የሚያሳየው የፍ/ብሄር ህጉ እነዚህ መብቶችና ግዴታዎች የሚተዳደሩበት ስርዓትና በመጨረሻም ቀሪ የሚሆኑበት ሁኔታ ያካተተ አስከሆነ ድረስና ህገ-መንግስቱን መሰረት በማድረግ የወጣ አዲስ የንብረት ህግ እስኪኖረን ድርስ ያለውን ህግ ከህገ-መንግስቱ ጋር አጣጥመን በስራ ላይ ማዋል ያለብን መሆኑ ነው ፡፡ የጋራ ባለሀብትነት መብት የንብረት መብት እንደመሆኑ መጠን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት ከወጣ በኋላ በሌሎች የንብረት ነክ ህጎችም ተካቶ የምናገኘው መብት መሆኑን ከፍ ብለን ካየናቸው አዋጆች መረዳት የሚቻል  ቢሆንም ካለንበት ህገ መንግስታዊ ስርዓት ጋር የተጣጣመና የተሟላ የንብረት ህግ የሚኖረን ግን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት መርሆችን መሰረት ያደረገ አዲስና ወጥ የሆነ የንብረት ህግ ሲታወጅ ነው፡

Read Next

  • Annual Leave in Ethiopia: Your Rights Under Labour Proclamation 1156/2019
    14.May
  • Ethiopia's Forex Bureau Requirements
    Ethiopia's Forex Bureau Requirements
    28.Aug
  • Administrative Law (30)
  • African Human Rights Law (18)
  • African Union Law (6)
  • Alternative Dispute Resolution (33)
  • Agency (6)
  • Bankruptcy Law (4)
  • Civil Procedure (12)
  • Conflict Laws (3)
  • Constitutional Law (5)
  • Construction Law (3)
  • Contract Law (7)
  • Criminal Law (10)
  • Criminal Procedure (6)
  • Criminology (4)
  • Customary Law (4)
  • Employment and Labor Law (17)
  • Environmental Law (5)
  • Evidence Law (6)
  • Family Law (5)
  • Gender and the law (4)
  • Human Right Law (5)
  • Humanitarian Law (7)
  • Insurance, Banking and Negotiable Instrument Law (6)
  • Intellectual Property Law (4)
  • International Organizations (4)
  • Introduction to law and Law of Persons (4)
  • Investment Law (10)
  • Islamic Law (2)
  • Judgment writing (0)
  • Jurisprudence (1)
  • Land Law (10)
  • Law and Development (0)
  • Legal History (0)
  • Legal Profession (0)
  • Legal Research Methods (0)
  • Legal Writing (0)
  • Legislative Drafting (0)
  • Maritime Law (3)
  • Non-Contractual Liability (Tort Law) (10)
  • Pre-Trial Skills and Trial Advocacy (0)
  • Property Law (27)
  • Public Enterprises and Cooperatives (0)
  • Public International Law (0)
  • Refugee Law (0)
  • Sales and Security Devices (0)
  • Sentencing and Execution (4)
  • Succession Law (6)
  • Taxation Law (4)
  • Trade and Business Organizations (2)
  • Administrative Contract (16)
  • Federalism (3)
Copyright © 2025 Abyssinia Law | Making Law Accessible! . All Rights Reserved.
Maintained by Liku Worku Legal Services!
Learn More ×