- Details
- Category: General - ልዩ ልዩ
- Abyssinia Law | Making Law Accessible! By
- Hits: 19547
እናንት ዳኞች የበየናችሁብኝን የሞት ፍርድ ያለይግባኝ ተቀብያለሁ፡፡ ይግባኝ ብዬ ጉዳዬን የሚመለከትልኝ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቢሆን ኖሮ ይግባኝ ማለት በፈለግሁ ነበር፡፡ ነገር ግን ይህ እንደማይሆን አውቃለውና በይግባኝ የአፄ ኃ/ስላሴን ፊት ማየት አልፈቅድም፡፡
- Details
- Category: General - ልዩ ልዩ
- ኪዳኔ መካሻ By
- Hits: 17649
- ሕገ መንግሥታዊ መሰረት
- የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት
- የዋና አዘጋጅ ኃላፊነት
- በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ለሚፈፀሙ ወንጀሎች የኃላፊነት ቅደም ተከተል
- Details
- Category: General - ልዩ ልዩ
- EthiopianReporter By
- Hits: 15932
‹‹ይሄ የማይታመን ነው፡፡ ዛሬ ለስድስተኛ ጊዜ ዳኛው ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሩኝ፡፡ ከጠዋት 3፡00 እስከ 6፡30 ተቀምጬ እጠባበቃለሁ፡፡ የያዝኩት ጉዳይ ሲጣራ ዳኛው ጉዳዩ ውስብስብ ስለሆነ አይተው እንዳልጨረሱ ይነግሩኛል፡፡
- Details
- Category: General - ልዩ ልዩ
- EthiopianReporter By
- Hits: 14521
ጎሮ ሰፈራ አካባቢ ለወትሮው በሚታጠፍበት ቦታ ላይ ሲደርስ ከፊት ለፊቱ ያሉ ተሽከርካሪዎች ሲፈተሹ ያያል፡፡ ስለዚህ ትራፊክ ፖሊሶቹ የሦስተኛ ወገን ኢንሹራንስ ጨምሮ ስለመሟላታቸው ለሚቀርቡላቸው ጥያቄ አሽከርካሪዎች
ሲመልሱ ተራው ደርሶት በሒደቱ ውስጥ ለማለፍ መጠባበቅ ጀመረ፡፡ መጠባበቁ ከምክንያታዊ ጊዜ ሲያልፍ ወጣቱ ትራፊክ ፖሊሶቹ እንዲያስተናግዱት መጣራት ጀመረ፡፡ ሰሚ አጥቻለሁ ብሎ በማሰቡ ታጥፎ ለመንቀሳቀስ መንገድ ጀመረ፡፡
- Details
- Category: General - ልዩ ልዩ
- Liku Worku By
- Hits: 23722
አብዛኛዎቻችን በልዩ ልዩ መሥሪያ ቤቶች ተቀጥረን የምንሠራ የሕግ ባለሙያዎች በተቀጠርንበት መሥሪያ ቤት ልክ የሕግ ሙያችንን እንወስነዋለን፡፡ የሕግ ባለሙያዎች ስል ዓቃቤ ሕጎች፣ ነገረ ፈጆች፣ ዳኞች፣ የሕግ አማካሪዎች እና መስል የሕግ ሙያን የሚሠሩ ባለሙያዎችን ማለቴ ነው፡፡ በተቀጠርንበት የሥራ ዘርፍ ልምድና ዕውቀት ማሳደግና ማዳበር ይበል የሚያሰኝ ተግባር ቢሆንም በሌሎች የሕግ ዘርፎች መጠነኛ እውቀት እንዲኖረን ማንበብ ሁለገብ ዕውቀት እንዲኖረንና ምሉዕ እንድንሆን የሚያደርገን ይመስለኛል፡፡ ለምሳሌ አንድ ዓቃቤ ሕግ ስለወንጀል እና ስለወንጀለኛ ሕግ ሥነ ሥርዓት ብቻ ቢያውቅ ራሱን ሙሉ የሕግ ባለሙያ ብሎ ለመጥራት የሚያስቸግረው ይመስለኛል፡፡ በተመሳሳይ ይህ ውስንነት በጠበቆች ላይም ሲስተዋል ይታያል፡፡
- Details
- Category: General - ልዩ ልዩ
- Abiyou Girma Tamirat By
- Hits: 22639
ብዙውን ጊዜ በፍትሐብሔር ጉዳዮች ላይ ክስ ያቀረበ ከሳሽ እና መልስ የሚሰጥ ተከሳሽ በክሳቸውና በመልሳቸው እንዲሁም በክርክራቸው ላይ ወጪና ኪሳራ የማቅረብ መብት ይጠበቅልኝ፣ ፍርድ ቤቱ ወጪና ኪሳራ በቁርጥ እንዲከፈለኝ ይዘዝልኝ ሲሉ፤ ፍርድ ቤቶች በበኩላቸው እንደጉዳዩ ዓይነትና ሁኔታ ወጪና ኪሳራ ግራ ቀኙ የየራሳቸውን ይቻሉ ወይም በክርክሩ የተረታው ወገን ለረታው ወገን እንዲከፍል በሚል ትዕዛዝ ሲሰጡ መመልከቱ የተለመደ ነው፡፡ ለመሆኑ ወጪና ኪሳራ ምንድን ነው? የወጪና ኪሳራ ዓላማውስ ምንድን ነው? ወጪና ኪሳራ ሊታሰብ የሚገባው በምን ዓይነት ሁኔታ ነው? ሕጉ ከወጪና ኪሳራ አንፃር ለፍርድ ቤቶች የሰጠው ሥልጣን ምንድን ነው? ወጪና ኪሳራን አስመልክቶ በተግባር ያለው አሠራር ምን ይመስላል? የሚሉና ሌሎች ነጥቦችን በጥቂቱ እንዳስሳለን፡፡