የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከአቢሲኒያ ሎው ጋር በመተባበር በፍርድ ቤቱ ሥር የሚገኙ የንግድ ችሎቶች የሰጧቸው የተመረጡ ውሳኔዎችን በዚህ ክፍል ያቀርባል፡፡ ዓላማውም ችሎቶቹ የሚሰጧቸው ውሳኔዎች ሥልጣን ባላቸው የበላይ ፍርድ ቤቶች መታየታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለንግድ ማህበረሰብ እና ለሌሎች ተጠቃሚዎች ውሳኔዎቹን ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡