ስለቀዳሚ ምርመራ (Preliminary Inquiry) ፍርድ ቤት ተልዕኮ፣ ሥልጣን እና ተግባር

በዘመናዊ አሠራር የወንጀል ጉዳይን እንዲከታተል የተቋቋመ እያንዳንዱ መሥሪያ ቤት ለፍርድ ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዩች አይነትና ብዛት ለመለየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ይቀይስለታል፡፡ ይህ እንዲሆን የሚያሰፈለገውም በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው ወንጀል ሰርተሃል ተብሎ በሚከሰሰበትና ለፍርድ በሚቀርብበት ጊዜ ብዙ ችግር ሊገጥመው እንደሚችል የታወቀ ነው፡፡ በወንጀል ተግባር ተከሶ ለፍርድ የሚቀርብ ሰው የሚደርስበት የማሕበራዊና የኢኮኖሚያዊ ቀውስ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ስለዚህ የዚህ አይነቱ ከባድ ጉዳት ሊደርስ የሚገባው በእርግጥ ወንጀል በሰሩና ወንጀል ለመስራታቸውም የማያጠራጠር ማስረጃ በቀረበባቸው ሰዎች ላይ መሆን አለበት፡፡ አንድን ሰው ወንጀል ሰርተሃል ብሎ መክሰስና በማሕበራዊ ኑሮ ውስጥ ያለውን ክብር ዝቅ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ ክሱን በማስረጃ ማረጋገጥና ተከሣሹን ጥፋተኛ ማስደረግ ግን በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ ስለዚህ በማስረጃ ሊረጋገጡ የማይችሉ ወንጀሎች በተቻለ መጠን በአጭሩ መቋጫ እንዲያገኙ ማድረግ የመንግሥት ሃላፊነት ነው፡፡

  16321 Hits

በኢትዮጵያ ሕግ የግል የኮንስትራክሽን ውሎች ምንነት፣ የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮችና የመፍትሔ ሀሳቦች

“And they said, Go to, let us build us a city and a tower, whose top may reach unto heaven; let us make as a name, lest we be scattered abroad upon the face of the whole earth…Therefore is the name of is called Babel; because the Lord did there confound the language of all earth…” Genesis 11:4-9

  26453 Hits

የማይደፈረውን ፍርድ ቤት መድፈር

በአንጌሳ ኢቲቻ የተጻፈውን ‹‹ችሎት መድፈር፡- ሕጉና የአሠራር ግድፈቶች›› የሚለውን ሳነብ እ.አ.አ በታኅሣስ 2013 በተመሳሳይ ርዕስ የጻፍኩትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ፡፡ በዚህ ጽሑፌ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ማለት ነው? የኢትዮጵያ ሕግ ስለ ፍርድ ቤት መድፈር ምን ይላል? የሕጉ ዓለማስ ምንድነው፣ የወንጀሉ አወሳሰን ልዩ ባህርይስ እንዴት ይታያል፣ በአፈጻጸም የሚታዩ ችግሮች ምንድናቸው የመሚለውን እዳስሳለሁ፡፡

  11978 Hits

ችሎት መድፈር፡- ሕጉ እና የአሠራር ግድፈቶች

የኢፌድሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 449፦

449. ፍርድ ቤትን መድፈር

(1) ማንም ሰው በፍርድ ቤት ምርመራ በሚደረግበት ወይም የፍርድ ሥራ በሚከናወንበት ጊዜ፦

ሀ/ ፍርድ ቤቱን ወይም የዳኝነት ሥራ በማከናውን ላይ ያለን ዳኛ በማናቸውም መንገድ የሰደበ፣ ያወከ ወይም በእነዚሁ ላይ ያፌዘ ወይም የዛተ እንደሆነ ወይም

ለ/ የፍርድ ቤቱን ሥራ በማናቸውም ሌላ መንገድ ያወክ እንደሆነ

ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እሥራት ወይም ከሦስት ሺህ ብር በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል። ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ ሳያደርግ ወድያውኑ በጥፋተኛው ላይ ቅጣት ሊወስን ይችላል።

  15378 Hits

በወንጀል ጉዳይ የመጨረሻ ውሳኔን እንደገና ስለማየትና በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ

በወንጀል ጉዳይ  የፍርድ ውሳኔ የሰጠው ፍርድ ቤት በድጋሜ ጉዳዩን ማየት ማለት ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ከሰጠ በኋላ የግዜ ገደብ ሳይኖረው ጉዳዩን በድጋሜ በተለያዩ ምክንያቶች ማየትና በድጋሜ ውሳኔ መስጠት ማለት ነው፡፡ በተለይም በዚህ ዘመን የሐሰት ሰነዶች የመቅረባቸው ጉዳይ እራስ ምታት በሆነበት፣ ሐሰተኛ ምስክርነትን መሠረት በማድረግ በተቃራኒ ተከራካሪ ወገንም ሆነ በፍርድ ቤቱ ሊደረስበት ባለመቻሉ የተሳሳተና የተዛባ የፍርድ ውሳኔ በሚሰጥበት ዘመን የእነዚህን ሐሰተኛ ማስረጃዎች ግዜ ሳይገድበው የሚያገኝ የወንጀል ጉዳይ ተከራካሪ ወደዛው ፍርድ ቤት በመሄድ የተገኘውን አዲስ ማስረጃ መሠረት በማድረግ ክርክር በድጋሜ አድርጎ ውሳኔው እንዲሰተካከል ለማድረግ የሚያስችል የሕግ አካሔድ መኖሩን አስፈላጊነት ሁሉም የሚስማማበት ነው፡፡ አንዳዴም እንደሚሰማው በህይወት ያለን ግለሰብ ገድለኃል ተብሎ ጥፋተኛ የተባለን ግለሰብ ሞተ የተባለው ግለሰብ በህይወት መኖሩ ቢታወቅ እንኳን ጥፋተኛ የተባለውን ግለሰብ ነፃ የሚያወጣ የሕግ አካሔድ ሊኖር የሚገባ ስለመሆኑም የሚያስማማ ነው፡፡ በቅርብ ግዜ በተላለፈ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኞች ከሚያጋጥማቸው ጉዳዮች በመነሳት የሐሰት ሰነዶች እና የሐሰት ምስክርነት ጉዳይ ከግዜ ወደ ግዜ እየተበራከተ መምጣቱን ሲናገሩ መስማቴ ትዝ ይለኛል፡፡ ይህን መሰል የፍትሕ ጠር የሆነ ተግባር ሙሉ ለሙሉ ማጥፋት ባይቻል እንኳን ይህ ሁኔታ በታወቀ ግዜ ግን ጉዳዩን ውሳኔውን የሰጠው ፍርድ ቤት በድጋሜ እንዲያይ የሚያስችልና ሐሰተኛውን ማስረጃ እና የተሳሳተውን ውሳኔ ለማስተካከል የሕግ መሠረት ሊኖረን ይገባል፡፡

  13754 Hits

ኢትዮጵያ ውስጥ በሚሠሩ ፊልሞች ላይ የሚታዩ የሕግ ግንዛቤ ክፍተቶች

ፊልሞችን ሰርቶ ለሕዝብ ማቅረብ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 ላይ የተቀመጠው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት አንደኛው መገለጫ ነው፡፡  ሀሳብን የመግለፅ መብት ከመንግሥት ገደብ (Limitation) ሊጣልበት የሚችለውም ውስን በሆነ ምክንያት እንደሆነ ይሄ ሕግ መንግሥት የሚያስቀምጠው ጉዳይ ነው (አንቀጽ 29/6ን መመልከት ይቻላል)፡፡ አዋጅ ቁጥር 533/2007 እና ከዛ በፊት የወጡ ሕጎችም ትልቅ ጥበቃ ሊደረግለት የሚገባውን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ሊገደብ የሚችልበትን አግባብ ያስቀምጣሉ፡፡ ሀሳብን የመግለፅ መብት በሕግ የሚገደበውም ሦስት መሠረታዊ ፍላጎቶችን (Interests) ለመጠበቅ ሲባል ብቻ ነው፡፡ እነዚህም፡-

  11893 Hits
Tags:

(Non) retroactivity of Ethiopian Criminal Law

A criminal law may be changed owing to various reasons. Obsoleteness, loopholes and insufficiency of penalties on the part of the existing criminal law are some of the justifications which may warrant its amendment or replacement. Even though changing a criminal law following changes in circumstances is vital and advisable, the advent of a new criminal law may create the difficulty of determining the temporal scope of application of the former and the new laws. An interesting solution for such problem is the principle of nonretroactivity of criminal law, which states that a criminal law is applicable only to offences committed subsequent to its enactment. Nevertheless, this principle has some exceptions, which allow the retrospective application of a criminal law.

  18961 Hits

አንዳንድ ምልከታዎች ስለ መገናኛ ብዙኃን እና የሐሰት ዘገባዎች

ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እጅግ መሠረታዊ መብት ከመሆኑ የተነሳ የተለያዩ ሀገራት ሕጋዊ ጥበቃ የሚያደርጉለት ሲሆን በአለማችን ላይ በአንባገነንነታቸው የሚታወቁ መንግሥታት ሰይቀሩ መብቱ ሳይሸራረፍ በሀገራቸው እንደሚጠበቅ ይከራከራሉ። በዚህ ጽሑፍ ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት በሰፊው ከሚተገበርበት ስለ መገናኛ ብዙኃን መብት እንመለከታለን። በመጀመሪያው ክፍል የመገናኛ ብዙኃን ለምን የሐሰት ዘገባዎችን ይሠራሉ በተለይም በመንግሥት ይዞታ ሥር የሚገኙ ወይም ዋነኛ የፋይናንስ ምንጫቸው በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ከመንግሥት የሆነ የሚለውን እናያለን። በመቀጠል የመገናኛ ብዙኃን የሰሩት ፕሮግራም እውነታን ያዘለ ሆኖ ሳለ የእርምት ወይም መልስ የመስጠት መብት ያለው አካል ሐሰተኛ ማስተባበያ ይዞ ቢቀርብ የማስተላለፍ ግዴታ አለባቸው ወይስ የለባቸውም የሚለውን እንመለከታለን። በመጨረሻም ነፃ ሚዲያ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ከሀገራችን ሕጎች አንፃር አጭር ዳሰሳ እናካሔዳለን።

  9358 Hits
Tags:

ያለ ፈጣን የፍርድ ሂደት ዋስትና የሚያስከለክል የወንጀል ድንጋጌ የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 20 የሚፃረር ተግባር ስለመሆኑ

ዋስትና በሕገ መንግሥትም ሆነ የሕገ መንግሥቱ የበታች በሆኑ በርካታ ሕጎች የታፈረና የተከበረ መሠረታዊው ከሆነው የሰው ልጅ የመዘዋወር ነፃነትና ንፁሕ ሆኖ የመገመት መብት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ሰብዓዊ መብት ነው፡፡ የሰው ልጅ እንደፈለገ ለመዘዋወር ሁለት እግሮች የተሰጡት፤ በአንድ ቦታ ተወስኖ እንዳይቀመጥ ሰዋዊ ተፈጥሮ ነፃ አድርጎ የፈጠረው ይህን ተፈጥሮውንም አብዝቶ የሚወድ ነፃ ፍጡር ነው፡፡ ይህ ፍጡር አሳማኝ የሆነ ማስረጃ በማቅረብ አንዳች ወንጀል መፈፀሙ ካልተረጋገጠበት በስተቀር ንፁህ ሆኖ የመቆጠር መብትም አለው፡፡ 

  13689 Hits
Tags:

ሕግ የማታከብረው ከተማ

በከተማችን ሰማይ ላይ የሰፈረ መንፈስ አለ የሆነ ህጻኑን ወጣቱን አዛውንቱን የሚፈታተን መንፈስ፡፡ በራዲዮ ቢራ፣ በቴሌቭዥን ቢራ፣ በቢልቦርዶች ገፅ ላይ ቢራ ሆኗል ከተማው፡፡ ዛሬ ዛሬ ቢሮ ከሚለው ስም ይልቅ ቢራ የሚለውን ስም መስማት የተለማመደ ሆኗል፡፡ እኔም በእለት ተእለት እንቅስቃሴም ውስጥ በሁለት ነገሮች እርግጠኛ ነኝ ከእሁድ በስተቀር ቢሮ እንደምገባና አንድ የቢራ ማስታወቂያ ጆሮየ እንደሚሰማ፡፡ ከወዳጅ ዘመዶቼ ይልቅ አዲሱ ዓመት መልካም እንዲሆንልኝ አብዝተው የተመኙልኝም የቢራ ማስታወቂያዎች ናቸው፡፡ ቢራ ስትጠጣ አዲሱ ዓመት የሰላም የጤና የብልፅግና ይሆንልሀል ዓይነት ፉገራ እየፎገሩኝ፡፡ ይህን ያህል ቢራ የሕይወታችን ገፅታ ሆኗል፡፡ ስለቢራ ላለመስማት ብር ብሎ ከመጥፋት ውጭ አማራጭ የለም በመዝናናታችን መኃል፣ በመንገዶቻችን ዳርቻ፣ በስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎቻች ቢራ አለ፤ ቢራ መኖሩ አይደለም ችግሩ፣ ችግሩ ቢራ አብዝቶ መኖሩና እየተነገረበት ያለው መንገድ ነው፡፡ ቢራ የማኅበራዊ የሥነልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ሕይታችን ጋሬጣ ሊሆነ በሀገሪቱ ሰማይ ላይ አንዣቧል፡፡

  11891 Hits