የዜግነት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥ የቅድመ ሁኔታዎቹ ቅድመ ሁኔታ ስለመሆኑ:- ለአቶ ግዛው ለገሰ የተሰጠ ምላሽ

 

 

ስለ ዜግነት አዎጁ በፃፍኩት ጽሑፍ ላይ አቶ ግዛዉ ለገሰ የተባሉ የሕግ ባለሙያ የፃፉት ምላሽ ደርሶኝ ተመለከትኩት፡፡ (የአቶ ግዛው ለገሰ ጽሑፍን ለማግኘት ይህንን ይጫኑ፡፡ ) በመጀመሪያ ጸሐፊው የሕግ ባለሙያ እንደመሆናቸውም ብሎም ጽሑፉን ያወጡት እሳቸው ስላልተስማሙበት የሕግ ጽሑፍ ምላሽ ለመስጠት እንደ መሆኑ አቶ ጀዋር መሐመድን ለመደገፍ አልፃፍኩትም ለማለት አቶ ጀዋር የራሱ ጉዳይ ብለው ጽሑፉን መጀመራቸው፤ በጽሑፉ ውስጥ ለተነሱ እያንዳንዱ ክርክሮች ተገቢውን የሕግ ክርክር ከማንሳት ይልቅ በአመዛኙ በተራ የአዋቃለሁ ባይነት ጉራ ተሞልተው እኩይ ሴራ የሚሉ ያልተገቡ ቃላቶች መጠቀማቸው ብሎም በጽሑፉ ውስጥ  ለድምዳሜቸው ማስረጃ አድርገው ስላቀረቡት የሕግ ግምት (presumption of law) ምንነት ያሉት ነገር አለመኖሩ እና ሃሳባቸው ልክ ስለመሆኑ የሚደግፍ የሕግ አስተምሮ ሳይጠቅሱ በደፈናው የሕግ ግምት ያልገባው የሚል የወረደ ምላሽ መስጠታቸው ከሙያ ሥነ-ምግባር የወጣ ተራ ብሽሽቅ የመሰለ መውረድ ሆኖ አግንቼዋለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ የመጀመሪየው ጽሑፍ በግልፅ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት ላይ ብቻ አተኮሮ እንደተፃፈ በተገለፀበት ሁኔታ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ስለሌላቸው እንደ በሕግ ዜግነት ስለማግኘት የመሳሰሉ ለምላሹ ፋይዳ በሌላቸው ዝርዝሮች ላይ ማተኮራቸውም አስቀድመው ላልተስማሙበት ጽሑፍ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በቂ እድል ነፍጓቸዋል ጊዜያቸው አጥንቱን በመጋጥ ላይ መዋል ሲገባው መረቅ ለመጠጣት ውሏል፡፡

እንግዲህ ከዚህ ቀጥየ የአቶ ግዛው የክርክር ነጥቦችን በእኔ መረዳት በሕግ እና በክርክር መርሆች አይን ስሁት መሆናቸውን እንደሚከተለው አሰረዳለሁ፡፡ ትክክለኛው እና አሳማኙ ክርክር የማን ነው የሚለው መዳረሻ የአንባቢ እንጂ የጸሐፊዎች ባለመሆኑ እንደ አቶ ግዛው የኔ ሃሳብ የጉዳዩ ዳርቻ ነው የሚል ትዕቢት አይዳዳኝም፡፡ በጉዳዩ ላይ ስፅፍም የጉዳዩ ትኩረት ማግኘት ትኩረት ከመሳቡ ውጭ የተለየ አትኩሮት ለጉዳዩ እንደሌለኝ በቅንነት ስገልፅ ይህን ማመን ወይም መጠራጠር በእጃችሁ ነው፡፡

የአቶ ግዛው ጽሑፍ አልፋ እና ኦሜጋ በዜግነት አዋጁ ላይ የተጠቀሱት ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች የሕግ ግምት በመሆናቸው ያለምንም የተለየ ሥርዓት ዜግነት ያሰጣሉ ቅድመ ሁኔታዎቹ አልተሟሉም ካለ ማስረጃ የማቅረብ ሃላፊነት (የማስረዳት ሸክም) የኮሚቴው ነው የሚል ነው፡፡

Continue reading
  7541 Hits
Tags:

የኢትዮጵያ ዜግነትን መልሶ ስለማግኘት - የኢትዮጵያ ዜግነትን ያለባለሥልጣኑ (ኤጀንሲው) ውሳኔ መልሶ ማግኘት የማይቻል ስለመሆኑ

 

ሰሞኑን የአቶ ጀዋር መሐመድን ኢትዮጵያዊ ዜግነት መልሶ የማግኘት ጉዳይ በኦፌኮ እና በምርጫ ቦርድ መካከል ክርክሮችን ማስነሳቱን በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየሰማን እንገኛለን፡፡ በመሆኑም የዜግነት ሕጉ ኢትዮጵያዊ ዜግነት መልሶ ስለማግኘት ስላሰቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች እና ዜግነት መልሶ ማግኘት ስለሚረጋገጥበት መንገድ ያለኝን መረዳት ለማካፈል ወደድኩኝ፡፡

አቶ ጀዋር መሐመድ አስቀድመው የኢትዮጵያ ዜጋ የነበሩ በመሆናቸው ነገር ግን በሕግ ዜግነታቸውን ከቀየሩ በኋላ መልሰው ዜግነታቸው እየጠየቁ በመሆኑ ለዚህ ጉዳይ ተገቢነት ያለው ድንጋጌ ስለዜግነት የሚደነግገው የአዋጅ ቁጥር 378/96  አንቀፅ 22  እና 23/2/ሐ ነው፡፡ በዚህ መሠረትም ኢትዮጵያዊ የነበረ ነገር ግን በሕግ የሌላ ሀገር ዜግነት ያገኘ ሰው የሚከተሉትን መሠረታዊ ጉዳዮች ከተሟሉ ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን መልሶ ያገኛል፤

  1. አስቀድሞ ኢትዮጵያዊ የነበረ መሆኑ፤
  2. ወደኢትዮጵያ ተመልሶ በመምጣት መደበኛ መኖሪያውን በኢትዮጵያ ውስጥ ከመሠረተ፤
  3. ይዞት የነበረውን የሌላ ሀገር ዜግነት ከተወ፤
  4. ዜግነቱ እንዲመለስለት ለኢሚግሬሽን እና ስደተኞች ባለሥልጣን ካመለከተ፤
  5. ጥያቄው ለዜግነት ጉዳይ ኮሚቴ ቀርቦ በባለስልጣኑ ተቀባይነት ካገኘ፡፡

ከፍ ሲል በዝርዝር የተመለከቱ ጉዳዮች አንድ ሰው ኢትዮጵያዊ ዜግነቱን መልሶ ለማግኘት ቅድመ ሁኔታዎች በመሆናቸው እና እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች የተሟሉ መሆን አለመሆናቸውን የማረጋገጥ እና የውሳኔ ሐሳብ የመሰጠት ሥልጣን ደግሞ የዜግነት ጉዳይ ኮሚቴ በመሆኑ በአዋጁ አንቀጽ 23/3 መሠረት የዜግነት ይመለስልኝ ጥያቄው በባለሥልጣኑ አማካኝነት ለኮሚቴው ቀርቦ ኮሚቴው የውሳኔ ሃሳብ ለባለሥልጣኑ አቅርቦ መወሰን ይገባዋል፡፡

Continue reading
  10411 Hits
Tags:

የውርስ ጉዳይን የተመለከቱ የይርጋ ገደቦች

መግቢያ

ማንኛውም ሰው አንድ የፍርድ ውሰኔ ሊያገኝ የሚገባ ጉዳይ ያለው እንደሆነ ጉዳዩን ለማየት በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ሊያቀርብ ሚችልበት የጊዜ ገደብ በልዩ ልዩ የሕግ ድንጋጌዎች ላይ ተመልክቶ ይገኛል፡፡ ይህን መሰል የጊዜ ገደብ በሕግ አጠራር ይርጋ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ትርጓሜውም በሕግ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ባለመብት የሆነ ወገን መብቱን ለመጠየቅ ተገቢውን ትጋት ማድረግና የመብት ጥያቄውን ማቅረብ ያለበት ሲሆን ይሄን ሳያደርግ ቢቀር ግን መብቱ በይርጋ (በጊዜ ገደብ) ቀሪ የሚሆን ይሆናል የሚል ነው፡፡

Continue reading
  20975 Hits

Is US action under the Ambit of International Law? Human Right and International Peace and Security at Risk?

“Whoever ill-treats a citizen indirectly injures the State, which must protect that citizen.” Vattel, on ‘The Law of Nations’

The corpus of international law is the most controversial area of law opened for legal battles, when different actors interpret it to favor their interest while taking actions. This regime of law has faced criticism for not having enforcement mechanisms which can be consider as an area of law like a lion without having a teeth. Leaving this behind, this piece assess the US drone strike of Iranian commander which took place in 3 January 2020 in light of international law through doctrinal analysis of different sources.  

The world has learn from the atrocities of the two world wars and promised among other things to maintain international peace and security as well as to save succeeding generations from the scourge of war under the preamble of the UN charter. The charter under article 2(4) urge all member states to refrain from the threat or use of force against the territorial integrity or political independence of any state. This system of territorial integrity is a matter of sovereignty which is attributable to the Westphalia system of 1648. However, states have an inherent right in exceptional circumstances to resort to use of force under the ambit of art. 51 of the UN charter in situations of individual or collective self-defense if an armed attack occurs against a Member of the United Nations, until the Security Council has taken the measures necessary to maintain international peace and security. It’s only in these two scenarios that the charter allowed use of force by states against another state. In this vein, unsettled issues are evolving which are controversial to employ force by states such as, use of force for humanitarian intervention, protection of nationals abroad and national liberation movements.

The US action: Where it falls? Is it under the ambit of International Law?

In the first days of 2020 the Trump administration employed the bush doctrine of anticipatory self-defense in assassinating the Iranian Commander Soleimani in Baghdad. The action of US is not only limited in affecting one UN member state’s sovereignty (Iran) rather it is also unwarranted interference against the territorial integrity of a third UN member state which is Iraq without its knowledge. This shows how power affects the international system and how it gives unfettered freedom for the superpowers in disregarding international law.

Continue reading
  5573 Hits

ስለወለድ እና የወለድ ወለድ አስተሳሰብ ደንቦች በጨረፍታ

 

 

  1. መግቢያ

ሰዎች ንብረታቸውን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በተመለከተ አንድን ግዴታ ለማቋቋም ወይም ለመለወጥ ወይም ለማስቀረት ባላቸው ተወዳዳሪ ግንኙነት በሁለት ወይም በብዙ ሰዎች መካከል ስምምነት ሲፈፅሙ ውል እንዳደረጉ ከኢትዮጵያ የፍትሐብሄር ህግ ቁጥር 1675 መረዳት ይቻላል፡፡ አንድ ውል ከተደረገ በኋላ በአንደኛው ወይም በሁለቱም ተዋዋይ ወገኖች ላይ ግዴታን ይጥላል፡፡ ይህንን ግዴታ በተባለው ጊዜ አለመፈፀም ወይም ጊዜ ካልተቀመጠ ደግሞ ማዘግየት የሚያስከትለውን ኪሳራ በተመለከተ ተዋዋይ ወገኖች ገደብ ወይም ቅጣት ወይም አንድ የተወሰነ ወለድ ግዴታውን ያልፈፀመ ተዋዋይ ወገን ውሉን ላከበረው ወገን እንዲከፍል ሲዋዋሉ መመልከት ወይም በፍርድ ቤቶች ሲወሰን ማየት የተለመደ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ወለድና የወለድ ወለድ (Interest on interest or compound interest) አስተሳሰብ ደንቦችን በተመለከተ እና ተያያዥ ጉዳዮችን የኢትዩጵያ ህጎች ላይ ተመስርተን በጨረፍታ እንደሚከተለው እንዳስሳለን፡፡

  1. ትርጓሜ

ወለድ የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ስንመለከተው አንድ ገንዘብ ያበደረ ሰው ተበዳሪው ብድሩን በመጠቀሙ ላበዳሪው ወገን በበኩሉ የሚከፍለው ወይም አንድ የባንክ ደንበኛ ያለውን ገንዘብ በአንድ ባንክ ገንዘብ ተቀማጭ ሲያደርግ በመቶኛ የሚታሰብ ገንዘብን የሚመለከት ወይም ተበዳሪ የወሰደውን ገንዘብ ወይም እቃ በወቅቱ ባለመመለሱ የተነሳ የሚከፈል የገንዘብ ካሳ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ወለድ ለገንዘብ ብድር ብቻ የሚከፈል ሳይሆን አንድ ግዴታን ባለመፈፀም ወይም በማዘግየት እና ይሄ ፍሬ ነገር ሲረጋገጥ የሚከፈል ጭምር ነው፡፡ በተጨማሪም ወለድ በስምምነት ወይም ያለስምምነት ማለትም በህግ አግባብ ሲወሰን ሊከፈል የሚችል ገንዘብ ነው፡፡ ለዚህ ፅሁፍ ዓላማ ሲባል በመቶኛ የሚታሰበውን ገንዘብን በሚመለከት ብቻ ያለውን እናያለን፡፡

የወለድ ወለድ ማለት በሚከፈል ወለድ ላይ በስምምነቱ ወይም በህግ መሰረት ወለዱን በወቅቱ ያልከፈለ ወገን በወለዱ ላይ የሚከፍለው ተጨማሪ የወለድ ወለድ እንደመቀጫ ያለ ገንዘብ ማለት ነው፡፡

Continue reading
  21139 Hits
Tags:

የሰበር ዓላማ ወጥነትን ማስፈን ወይስ ሕገ-ወጥነትን ማስፋፋት?

 

ጊዜው እ.ኤ.አ 1954 ነው፡፡ ለአለም ሀገራት የዲሞክራሲ አርአያና መምህር ነኝ ብላ በምትደሰኩር በአሜሪካ ሀገር ነጭና ጥቁር ተማሪ በአንድ ላይ አይማርም ነበር አሉ፤ ምክንያቱም ጥቁር ተማሪ ከነጭ ተማሪ ጋር በአንድ ላይ እንዲማር መፍቀድ ማለት በነጭ ተማሪዎች ሞራልና ክብር መቀለድ ነው ብላ ታምን ነበር፤ አሜሪካ፡፡ በመሆኑም ጥቁሮችና ነጮች ተለያይተው ይማሩ ነበር ማለት ነው፡፡ በዚሁ አይን ያወጣ አድልዎ የተበሳጨው ብራውን የተባለው ግለሰብ በአሜሪካ ሀገር የካንሳስ ክልል የትምህርት ጉዳይ ቦርድን በፍርድ ቤት ገተረው፡፡ ሚስተር ብራውን ለጥቁሮች ሽንጡን ገትሮ ከተከራከረ በኃላ ጥቁሮችን አንገት የሚያቀና ፍርድ አስፈረደ፡፡ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጥቁርና ነጭ ተማሪዎች ተለያይተው እንዲማሩ ማድረግ የሰው ልጆች በተፈጥሮ እኩል ሆኖው የመፈጠር መብትን የሚቃረን በተለይም ደግሞ የጥቁሮች ክብርና ሞራል የሚነካ እኩል የትምህርት እድል የሚነፍግ ህገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ ከተፈጥሮ ሕግና የአሜሪካ ህገ መንግስት ጋር የሚጣረስ ነው ሲል ለሰው ልጆች እኩልነት የሚያረጋግጥ ፍርድ ሰጠ፡፡ ጥቁሮች ከነጮች ጋር ያለአድልዎና ልዩነት ሳይደረግባቸው እኩል የትምህርት እድል የማግኘትና የመማር መብት አላቸው የሚል መደምደሚያ ላይ ተደረሰ፡፡ በዚሁ ውሳኔ የተበሳጨው "ጆርጅያ ኩሪዬር" የተባለ ጋዜጣ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ዳኞችን እንዲህ ሲል ገለፃቸው፡፡

“No man knows today what his rights are in this country. No man today has any liberties left. His rights and his liberties are in the laps of the nine crazy men who sit on the Supreme Court bench. And the lord only knows what these crazy men will do next. Today they are most dangerous tyrants that ever existed. Like Hitler, Mussolini, and the other modern day tyrants, they are mentally deranged. They are crazed with a desire to serve a minority for political purposes. Their insanity has made them unscrupulous in the methods they have employed to do the bidding of this minority. They are mentally deranged tyrants ruling as unscrupulously as any tyrant in all of history. The members of this court must be curbed or they must be removed from the bench.”

ትችቱ ወደ አማርኛ ስንመልሰው በዚች ሀገር መብቱን እና ነፃነቱን የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ ነፃነቱንና መብቱን በጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንበር ቁጭ ባሉ በእነዚህ  ዘጠኝ ያበዱ ዳኞች እጅ ላይ ነው፤በቀጣይም እነዚህ እብድ ዳኞች የሚሰሩት ነገር ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ አሁን በዘመናችን አይተነው በማናውቅ ሁኔታ እነዚህ ዳኞች አደገኛ አምባገነኖች ናቸው፤እንደ እነ ሂትለር፣ሙሶሎኒና ሌሎች ዘመናዊ አምባገነኖች በጭካኔ ያበዱ ናቸው፤ለፖሊቲካ አላማ ሲባል አናሳ ማህበረሰብን ለማገልገል አብደዋል፡፡ እብደታቸውን አናሳውን ለማገልገል ይሉኝታ እንኳን ሊገድበው አልቻለም፤እነዚህ ሰዎች ሊወገዱ ይገባል ለማለት ነው፡፡ (ትርጉም የራሴ)

እኔ ደግሞ እላለሁኝ፡፡ ያበዱት ዳኞቹ ሳይሆን ጋዜጣውን ያወጣው ፀኃፊ ራሱ ነው፡፡ ይህ ጋዜጣ በወቅቱ ይዞት የወጣ ትችት ብሽቅ እና በዘረኝነት የተነዳ ከአንድ ዲሞክራሲያዊት ሀገር ፈፅሞ የማይጠበቅ ነው፡፡ የእብደት እብደት፡፡ ይህ ማለት ከፍትህ እና ከእኩልነት አንፃር የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ ከትክክልም በላይ ነበር፡፡

Continue reading
  7828 Hits

በኢትዮጵያ የሲቪክ ምህዳር መብቶች ጥበቃ እና የሚስተዋሉ አንዳንድ ችግሮች

 

 

 

“The importance of ensuring the broadest possible civic space in every country cannot be overstated…The protection of the civic space, and the empowerment of human rights defenders, needs to become a key priority for every principled global, regional and national actor."

Continue reading
  10101 Hits

The Role of ICT in Judicial Reform in Ethiopia

 


Introduction

Ethiopia has been implementing justice reform programs for more than 15 years now.  This program is comprehensive and includes all the justice institutions at the federal and regional levels.  Within each institution, the reform program incorporates various components. 

ICT is used as an important tool to achieve many of the objectives set in the justice reform program.  Thus ICT is not seen as an end by itself but as a means to achieve other justice ends.  The ICT system was locally designed, implemented and expanded within this mindset.  The current system used by the courts is quite advanced but it reached this stage by responding to growing justice needs some of which were created by the new ICT system itself.

 

Continue reading
  7200 Hits

የማናከብረውን እና የማንተገብረውን ሕግ ማውጣት ከሕግ አልባነት አይሻልም- መረጃ የማግኘት መብት

 

ሕግ ጭራሽ ካለመከበሩ በከፋ ተመርጦ ሲከበር የበለጠ አልተከበረም፡፡ አሁን ባለን መረጃ ሀገሪቱ ከቻይና ጋር ስለገባነው የብድር ስምምነት የሚያትትውን 1000ኛውን አዋጅ ካወጀች ብኋላ  እንኳ ከመቶ በላይ አዋጆች ወጥተዋል፡፡ ኑሮው፣ ፖለቲካው፣ ኢኮኖሚውና ማህበራዊ ጉዳያችን ብዙ ነው እና ሕጎቹ በዙ አይደለም ጉዳዩ፡፡ ስንቱ በርግጥ ወጥቶ ሥራ ላይ ዋለ ነው ጥያቄው፡፡ የማናከብረውን እና የማንተገብረውን ሕግ ማውጣት ከሕግ አልባነት አይሻልም፡፡ 

ይህ ጽሑፍ ስለ መረጃ ነፃነት ነው፡፡ ሰብአዊና አለማቀፋዊ የሆነው የመረጃ ነፃነት  መብት ተጥሷል፡፡ በአጭር ቋንቋ ህገ መንግስቱ ተጥሷል፡፡ የተጣሰው ደግሞ ህጉ በወጣለት ህዝብም ፤ ህጉ በወጣበት መንግስትም ፤  ህጉ በወጣላቸው ሚዲያዎችም ጭምር ነው፡፡

ሁሉን ብፅፍ ቀለም አይበቃም እንዲል ሊቁ እኔ ግን እናተን በረጅም ጽሑፍ ላለማሰልቸት  እንደሚከተለው አሳጥሬዋለሁ፡፡ በሕገ መንግሥቱ የተከበረው እና የታፈረው የዜጎች መረጃ የማግኘት መብት በሚዲያዎች እና በመንግስት ተቋማት በአደባባይ እየተሻረ ነው፡፡ ግልፅ ነው ዜጎች ስለማናቸውም ጉዳይ እጅግ ውስን ከሆኑ በስተቀሮች በቀር መረጃ የማግኘት መብት አላቸው፡፡ ዴሞክራሲ ጎዞ ጀምሯል የሚባለው ጠያቂ ሚዲያ ፣ መለሽ መንግስትና አድማጭ ህዝብ ሲኖርም ጭምር ነው፡፡ ያለ መረጃ ነፃነት ዴሞክራሲ የለም አይኖርምም፡፡ ካልተማሩ እንዴት ያውቃሉ ካላወቁ እንዴት ይጠይቃሉ እንዲል መጽሐፍ የመረጃ ነፃነት ወይም መረጃ የማግኘት መብት የዴሞክራሲ አምድ ነው፡፡

ሚዲያዎች መንግስት ሃላፊዎችን እና የመንግስት ተቋማትን የሚያጋልጡ መረጃዎችን ጨምሮ ማናቸውንም የህዝብ መረጃ የመጠየቅ ጠይቆ የማግኘት መብትም ግዴታም አለባቸው፡፡ መንግስት እጅግ ጥቂት ከሆኑ እንደ ሃገር ደህንነት የሚመለከቱ ጉዳዮች በቀር ምን? ለምን? እንደሚሰራ ዜጎች የማወቅ እና በጉዳዩ ላይ በሻቸው መንገድ ሃሳባቸውን የመግለፅ መብትና አቋም የመያዝ መብት አላቸው፡፡ ጉዳዩ አዋጃዊ አይደለም ህገመንግስታዊ ጭምር ነው፡፡  ስለዚህ  ይህን መብት አለማክበር ህገ- መንግስትን አለማክበር ነው፡፡ ህገ-መግስት አልተከበረም የሚባለው የየግል ቁስላችን ሲናካና ትላንት ድንጋይ ወደ መንግስት ሲወረወር  ዛሬ የፌደራል ስረአቱ ሲነካ ብቻ አይደለም ፡፡ በህገ-መግስቱ በግልፅ እና በቅድሚያ የተደነገጉት የግለሰብ እና የህዝብ መብቶች ሲጣሱም ጭምር ነው፡፡ የህገ-መንግስቱን  መጣስ ሁሌ ከፌደራል ስረአት መከበር አለመከብር ጋር ማያያዝ ህገመግስቱ  ለግለሰቦች የሰጣቸውን በረጅም የህዝቦች ትግልና መሰዋትነት  አለማቀፋዊነት ደረጃ ያገኙ  መብቶችን መጣስ ነው፡፡ መቼስ ስረአቱ የተዘረጋው ለህዝቦች መብት ሰላም እና ደህንነት ከሆነ የግለሶችን እና የህዝቦች መብት እየጣሱ ስረአቱን መጠበቅ ውሃውን እያፈሰሱ  ቧንቧውን እንደመንከባከብ ያለ አባካኝነት ነው፡፡

Continue reading
  8124 Hits

Birth registration and rights of the child

 

1 Introduction

Birth registration is defined as the ‘official recording of a child’s birth by the State’. It is also a lasting and official record of a child’s existence, which usually include the ‘name of the child, date and place of birth, as well as, where possible, the name, age or date of birth, place of usual residence and nationality of both parents.’

Birth registration is an internationally recognised fundamental right, it is recognised under Article 24 of the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR), which states that ‘every child shall be registered immediately after birth.’ The Convention on the Rights of the Child (CRC) also stipulates that  

[t]he child shall be registered immediately after birth and shall have the right from birth to a name, the right to acquire a nationality and, as far as possible, the right to know and be cared for by his or her parents.

Continue reading
  7629 Hits