በሰዎች መነገድ/ሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ምንድነው?

በአገር ውስጥ እና በተለይም ወደ ሌሎች አገራት የሚካሄድ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውር በኢትዮጵያ ውስጥ የላቀ ትኩረት እያገኘ መጥቷል፡፡ ይህም ትኩረት በቅርቡ ጉዳዩ እያገኘ ካለው ሰፊ የሚድያ ሽፋን ባሻገር ችግሩን ለመፍታት በተከታታይ በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የሕግ፣ የፖሊሲና የፕሮግራም እርምጃዎች ላይ ይንፀባረቃል፡፡ ለዚህ ጉዳይ የተሰጠው ትኩረት ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም አልፎ አልፎ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ምንነት ጋር በተያያዘ የተወሰነ ግራ መጋባት ይታያል፡፡ ይሕ አጭር ጽሁፍ ይህንን ክፍተት ለመሙላት ለሚደረው ጥረት አስተዋጽኦ ያደርጋል በሚል እምነት የተዘጋጀ ነው፡፡

ትርጉም

የተ.መ.ድ. እ.ኤ.ኤ. በ2000 ዓ.ም. ያወጣውና የፓሌርሞ ስምምነት በመባል የሚታወቀው ስምምነት በሰዎች መነገድ ወይም ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ለብዝበዛ ዓላማ ሰዎችን (በተለይም ሴቶችና ሕፃናትን) በኃይል፣ በዛቻ፣ በተንኮል፣ በማታለል፣ በመጥለፍ ወይም በተበዳይ ላይ ኃላፊነት ላለው ሰው ገንዘብ ወይም ሌላ ጥቅም በመስጠት መመልመል፣ ማጓጓዝ፣ ማስተላለፍ፣ መደበቅ ወይም መቀበል ማለት እንደሆነ ይገልፃል፡፡ ሕፃናትን በተመለከተ ለብዝበዛ ዓላማ እስከሆነ ድረስ ሕፃናቱን መመልመል፣ ማጓጓዝ፣ ማስተላለፍ፣ መደበቅ ወይም መቀበል በራሱ በሰዎች መነገድ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ በሴቶችና በልጆች መነገድን የሚከለክለው የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 597 እና 635 ላይም ይኸው ትርጉም ተሰጥቶታል፡፡ ከዚህ ትርጓሜ መረዳት እንደምንችለው በሰዎች መነገድ በዋነኛነት ሦስት ነገሮችን ያጠቃልላል፡፡ እነዚህም፡ - (1ኛ) በኃይል ወይም በማታለል መመልመል (ምልመላ)፣ (2ኛ) በአገር ውስጥ ወይም ወደ ሌላ አገር በህጋዊ ወይም ህገ-ወጥ መንገድ ማዘዋወር (ዝውውር)፣ እና (3ኛ) አዘዋዋሪዎች ተበዳዮችን የገንዘብ ጥቅም ማግኛ ማድረጋቸው (ብዝበዛ) ናቸው፡፡

በሰዎች መነገድ ከሌሎች የሰዎች ዝውውር ክስተቶች ጋር በተለይም ከኢ-መደበኛ የሰዎች ዝውውር እና ከሕገወጥ የድንበር ዝውውር ጋር የሚምታታበት ሁኔታ ይከሰታል፡፡ ይህም የሰዎች ንግድ ተጎጂዎች እንደ ወንጀለኛ የሚታዩበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ በአጠቃላይ ሰዎች በአገር ውስጥ ወይም ወደ ውጭ አገር ከቦታ ወደ ቦታ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ወይም ስደት ስራ ፍለጋ፣ ለተሻለ ህይወት፣ መሳደድን በመፍራት፣ ከጭቆና ወይም የተፈጥሮ አደጋ ለመሸሽ ብሎም የመኖሪያ ቦታን ለመቀየር ሲባል ሊካሄድ ይችላል፡፡ በአንፃሩ በሰዎች መነገድ ዓላማው ብዝበዛ ሲሆን ስደተኞች ለዚህ ሁኔታ ተጋላጭ ናቸው፡፡

ከሁለት ዓመታት በፊት በአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት የተደረገው ጥናት እንደሚያመለክተው በመካከለኛው ምስራቅ አገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን መካከል 76.7 በመቶ የሚሆኑት የሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ሰለባዎች ናቸው፡፡ በተለይም እድሜያቸው ከ18 አመት በታች ከሆኑት እና ወደተለያዩ የሰሜን አፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ስራ ፍለጋና ሌሎች ምክንያቶች ከተጓዙት ኢትዮጵያውያን መካከል 7.5 በመቶ የሚሆኑት እድሜያቸው ከ13 እስከ 17 አመት መሆኑን እና ከነዚህም ውስጥ 87.1 በመቶ የሚሆኑት የሕገወጥ ዝውውር ሰለባዎች እንደነበሩ ሌሎች ጥናቶች አመልክተዋል፡፡ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በአገሪቱ እስከ 50 ሺህ ኢትዮጵያውያን የሚገኙ ሲሆን እስከ 95 በመቶ የሚሆኑት እዚያ የሚደርሱት በሕገወጥ ደላሎችና አዘዋዋሪዎች በኩል ነው፡፡

Continue reading
  23135 Hits
Tags:

What is Trafficking in Persons?

The issue of trafficking in persons from and within Ethiopia has become a critical issue of concern for the country. The level of concern is clearly reflected in the increased media coverage of the situation of victims of trafficking as well as the measures taken by the government to address the problem through legislative, policy and programmatic mechanisms. While the current attention to the issue is to be commended, there also appears to be some level of confusion as to what trafficking in persons is. The current brief article is an attempt to help clarify the problem.

Definition

The UN Protocol to Prevent, Suppress and Punish Trafficking in Person, Especially Women and Children that supplements the UN Convention against Transnational Organized Crime (2000), known as the Palermo Protocol, defines trafficking in human beings as: ‘the recruitment, transportation, transfer, harbouring or receipt of persons, by means of the threat or use of force or other forms of coercion, of abduction, of fraud, of deception, of the abuse of power or of position of vulnerability or of the giving or receiving of payments or benefits to achieve the consent of a person having control over another person, for the purpose of exploitation’. Where children are concerned, the Protocol stipulates that ‘recruitment, transportation, transfer, harbouring or receipt of a child for the purpose of exploitation shall be considered ‘trafficking in persons’ even if this does not involve any of the means set forth in the definition.’ Trafficking in persons consists of three essential components: 1st) Recruitment – by force or deception; 2nd) Transportation – within a country or across borders, legally or illegally; and, 3rd) Exploitation – traffickers financially benefit through the use or sale of the victim.

The complex phenomenon of trafficking is often confused with other forms of people movement, such as irregular migration and smuggling. As a result, people who have been trafficked are treated as criminals rather than victims. Migration is the movement of people from one place to another within a country, or from one country to another prompted by the need for work, a better life, the fear of persecution, work, the horrors of war or disaster, or just because they want to live somewhere else.

A study conducted by IOM and other institutions indicated that 76.7% of all Ethiopian migrant workers living in the Middle Eastern countries engaged in different sectors of employment are victims of trafficking. Other studies have indicated that 7.5% of all Ethiopian migrants who have left their country for employment and other purposes were between the ages of 13 – 17 years at the time of their migration. The Study also showed that 87.1% of these migrants were trafficked.The Ethiopian Embassy in South Africa estimated that approximately 45,000 to 50,000 Ethiopians live in South Africa. It is estimated that 95% or more of these Ethiopian arrivals enter South Africa through irregular means.

Continue reading
  15538 Hits
Tags: