ጣዕም መቀየሪያዎች የተጨመሩባቸው የሺሻ ትምባሆ ምርቶች መስፋፋትና ሕገ ወጥነት

በኅብረተሰብ ጤና ዘርፍ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሚባል ለውጥ ካስመዘገቡ አገሮች ተርታ ትመደባለች፡፡ የጤና አገልግሎትን በቀበሌ ደረጃ ለማስፋፋት፣ በተለይም በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የኅብረተሰብ ክፍል ማዕከል ያደረገና በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተቸረውን የጤና ኤክስቴንሽን መርሐ ግብር ተግባራዊ በማድረግ፣ የዓለም መንግሥታት ድርጅትን የጤና የሚሊኒየም ግቦችን ለማሳካት ችላለች፡፡ እንደ አብዛኛው ታዳጊ አገሮች ሁሉ ባለፉት ዓመታት የመንግሥት የጤና ፕሮግራሞችና የአጋር ድርጅት ትኩረቶች ውስጥ ወባ፣ ኤችአይቪ/ኤድስና ሳንባ ነቀርሳ የመሳሰሉ ተላላፊ በሽታዎች የመከላከልና ቁጥጥር ሥራ፣ እንዲሁም የሕፃናትና እናቶች ጤናን ማሻሻል በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ሆኖም ግን ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ የአገሪቱ የበሽታዎች ሥርጭት ሁኔታ በለውጥ ሒደት ላይ ያለ ሲሆን፣ በተለይም በከተማዎችና በዙሪያቸው ባሉ ሥፍራዎች በመስፋፋት ላይ የሚገኙት የልብ፣ የመተንፈሻ አካላት፣ ስኳርና ካንሰርን የመሳሰሉ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ይጠቀሳሉ፡፡

  11324 Hits

ሺሻን ለሽያጭ ከማቅረብና ከመጠቀም ጋር ተያይዘው የሚፈፀሙ ወንጀሎች

በልደታ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሺሻ በማስጨስ ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ግለሰቦች እና የማስጨሻ ቤቶች መኖራቸውን የተረዳው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ እና በሥሩ የሚገኙ የተለያዩ ፖሊስ ጣቢያዎች የሺሻ ማስጨሻ ዕቃዎችን እና ሺሻ ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ ሺሻን ሲያስጨሱ የነበሩ ግለሰቦች ላይም የወንጀል ምርመራ የተጣራባቸው ሲሆን በምርመራ መዛግብቱ ላይ በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ በኩል ተገቢውን የሕግ አስተያየትና ውሳኔ መስጠት ይጠበቃል፡፡ ሆኖም ጉዳዩ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ፍርድ ቤቶችና በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ሲታይ ያልነበረ በአንፃሩ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶችና በከተማ ነክ ፍትሕ ጽ/ቤቶች የአቤቱታ ምርመራና የክስ አቀራረብ ንዑስ የሥራ ሂደት ሲታዩ የነበረና ሺሻን አስመልክቶ በቂ መረጃና የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በተጣሩት የምርመራ መዛግብት ላይ ተገቢውን የሕግ አስተያየት እና ውሳኔ ለመስጠት አስቸጋሪ ሆኖ ቆይቷል፡፡

  13987 Hits
Tags: