የቴዲ አፍሮ አልበም ምርቃት ክልከላ እና የመሰብሰብ መብት

 

መንደርደሪያ

የዚህ ጽሑፍ መነሻ የቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ መከልከል ሲሆን ጽሑፉ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት በማንኛውም ምክንያት መሰብሰብ አድማሱ እስከምን ነው? የሚለውን መሠረታዊ ነጥብ የሚዳስስ ሲሆን የአልበም ምርቃቱን መከልከል ምክንያቶች በተመለከተ ግን ጸሐፊው በሁለቱም ወገኖች በኩል ያለውን እውነት በማስረጃ ባለማረጋገጡ አቋም ከመያዝ ተቆጥቧል፡፡ ይሁን እንጂ አጋጣሚው በአስፈፃሚውም ይሁን በስብሰባ አዝጋጆቹ ብሎም በማህበረስቡ ላይ ያለውን መደናገር የመሰብሰብ መብትን አድማስ ለማብራራት ምቹ በመሆኑ ጸሐፊው በርግጥ ለቴዲ አፍሮ የአልበም ምረቃ ፈቃድ ያስፈልግ ነበር? ፈቃድ ካስፈለገውስ መከልከል ይቻል ነበር? የመከልከል ተግባሩ የሚጥሳቸው መሠረታዊ ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችና መብቶችስ ምንምን ናቸው? ለሚሉ መሠረታዊ ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት ይሞክራል፡፡

መግቢያ

መሰብሰብ ሰው ሁለት ሆኖ ከተፈጠረበት የታሪክ አውድ ይጀምራል፡፡ ሰው ማህበራዊ እንስሳ ነው ሲባል በሌላ አነጋገር ሰው ይሰበሰባል እንደ ማለት ነው፡፡ ፈጣሪም አዳም ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ሲል ጥንትም ፈጣሪ ሰውን ሲፈጥረው በውስጡ ከሌሎች ጋር የመሆን፣ ከሌሎች ጋር የመምከር፣ ከሌሎች ጋር የመደሰት፣ የመኖር፣ አንድን ነገር በጋራ የማድረግ፣ የማክበር ባሕርይ እንደፈጠረበት ሲያጠይቅ ነው፡፡ እናም መሰብሰብ ከፍ ሲል ፈጣሪ ለአዳም/ለአደም ሄዋንን/ሃዋን ሲፈጥርለት ዝቅ ሲል አዳምና ሄይዋን ቃዬልን ጠርተው ስለ አቤል ጉዳይ ሲጠይቁት ይጀምራል፡፡

Continue reading
  12478 Hits