እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል?  

 

ጥያቄው?

በዚህ ጽሁፍ መመለስ የምፈልገው ጥያቄ ቀላል ይመስላል፤ እንዴት ያለባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ የተላለፈን ንብረት ማስመለስ፤ የተቋቋመን የመብት ገደብ ማስነሳት ይቻላል የሚለውን ነው፡፡ ቀጥታ ጥያቄውን ወደ መመለሱ ከመሄዴ በፊት፤ ጥያቄው የሚመለከታቸው ሁኔታዎች ምን አይነቶቹን እንደሆነ ግልጽ ላድርግ፡፡

ያለ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ሲባል?

እንደሚታወቀው ንብረትን (የማይንቀሳቀስም ይሁን ልዩ ወይም ተራ የማይንቀሳቀስ) ለሌላ ሰው ውልን መሰረት አድርጎ ለማስተላለፍ የባለቤቱ ሙሉና ነጻ ፈቃድ ያስፈልጋል፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሰጥቷል ነገር ግን ፈቃዱ ሙሉ እና ነጻ አልነበረም የሚባለው የባለቤቱ ፈቃድ በስህተት ወይም በማታለል ወይም በሃይል ተግባር ምክኒያት የተሰጠና በሕጉም መሰረት ውሉ ፈራሽ ውል ሲባል ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን የገለጸው ራሱ ወይም በወኪሉ በኩል ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ሁኔታ የባለቤቱ ፈቃድ ጉድለት አለበት፤ ነገር ግን ንብረቱ ተላልፎ ሊሆን ይችላል ወይም የመብት ገደብ ተቋቁሞ ሊሆን ይችላልና እንዴት ባለቤቱ ንብረቱን ማስመለስ ገደቡን ማስነሳት ይችላል የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡

ባለቤቱ በምንም አይነት መልኩ ፈቃዱን ሳይገልጽ ከሆነስ?

በሁለተኛ ደረጃ የንብረት ማስመለሱና የመብት ገደቡን የማስመለስ ጥያቄ ሊነሳ የሚችለው ከመጀመሪያውኑ ባለቤቱ በምንም መልኩ ፈቃዱን ያልገለጸ ከሆነ ነው፡፡ ባለቤቱ ፈቃዱን ሳይገልጽ እንዴት ንብረት ይተላለፋል ወይም መብት ይገደባል ለሚል ጥያቄ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሁኔታዎች መልስ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

1. አንድ ሰው ህጋዊ ባለቤት ሳይሆን ባለቤት እንደሆነ በማስመሰል ከሌላ ሰው ጋር በመዋዋል ንብረቱን ሊያስተላልፍ ወይም የመብት ገደብ ሊያቋቁም ይችላል፡፡ ንብረቱ ተራ የሚንቀሳቀስ ንብረት ከሆነ ይህን ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ ንበረቱ የማይንቀሳቀስ ወይም ልዩ ተንቀሳቃሽ ቢሆንም ይህን ለማደድረግ ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን ሰነዶችን ፎርጅድ ማድረግ ሊጠይቅ ወይም የሌላ አካል ትብብርን ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እነዚህ ሰነዶች ይህ ሰው ባለቤት መሆኑን የሚያሳዩ ወይም ንብረቱን አስመልክቶ በባለቤቱ ስም ውል የመዋዋል ስልጣን አንዳለው የሚያሳዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Continue reading
  19708 Hits

ስለ ንብረት የዋጋ ግምት ጥቂት ነጥቦች

 

ለፍርድ ቤቶች በሚቀርቡ ክርክሮች ላይ የንብረትን ትክክለኛ የዋጋ ግምት ማወቅ የግድ አስፈላጊ የሚሆንባቸው ጊዜያቶች አሉ፡፡ ለመሆኑ የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ያስፈልጋል? የንብረት የዋጋ ግምት ተገምቶ እንዲቀርብ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት የመገመት ኃላፊነት በሕግ የተሰጠው ለማን ነው? በአሠራር ደረጃ የንብረት የዋጋ ግምት በማን እና እንዴት እየተገመተ ይገኛል? የንብረት ዋጋ ግምትን አስመልክቶ የሚታዩ ችግሮች ምንድን ናቸው? የንብረት የዋጋ ግምት ሲሰራ በመሠረታዊነት ሊካተቱ የሚገባቸው ነጥቦችስ ምንድን ናቸው? የሚሉና ሌሎች ተያያዥ ነጥቦች በዚህ ፅሁፍ በጥቂቱ እንዳስሳለን፡፡        

  1. የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ ለምን ይጠቅማል?

የንብረት የዋጋ ግምት ማወቅ የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፡፡ እነዚህም፡ -

  • ፍትሐዊና ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት እንዲቻል፤
  • የፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ሥልጣን ለመወሰን እንዲቻል፤
  • ለፍርድ ቤቶች ተገቢውን የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ለማከፈል፤
  • ጥፋተኛ ተብለው በወንጀል የሚፈረድባቸው ሠዎች ላይ ተመጣጣኝና የተገኘውን ልተገባ የጥቅም መጠን ወይም የደረሰውን የጉዳት መጠን መሠረት ያደረገ ቅጣት ለመወሰን ነው፡፡
  1. ተከራካሪ ወገኖች የንብረት ዋጋ ግምት መጠን እንዲጠቅሱ የሚጠይቁ ሕጎች የትኞቹ ናቸው?
  • ክስ የሚቀርበው አንድን ንብረት ለማስለቀቅ ወይም ከአንድ ንብረት ላይ ድርሻ ለመጠየቅ በሆነ ጊዜ ክስ የቀረበበትን ንብረት ወይም የንብረቱን ወይም ከንብረቱ ላይ የሚገኘውን የድርሻ የዋጋ ግምት በክስ አቤቱታ ላይ ሊጠቀስ እንደሚገባ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ 222 /1/ /ቀ/ እና 226 /3/ /4/ ላይ ይጠይቃል፤
  • የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋም በወጣው በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀፅ 11 /1/ እና 14 መሠረት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከብር 500,000.00/አምስት መቶ ሺሕ/ በላይ የሆኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን እንዲሁም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከብር 500,000.00/አምስት መቶ ሺሕ/ በታች የሆኑ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን አከራክረው የመወሰን ሥልጣን ተሠጥቷቸዋል፡፡ ተከራካሪ ወገኖችም የሚያቀርቡትን የገንዘብ ወይም የንብረት ክርክር የዋጋ ግምት በክሳቸው ላይ መግለፃቸው የፍርድ ቤቶችን የዳኝነት ሥልጣን የሚወስን በመሆኑ በአዋጁና በሥነ ሥርዓት ሕጉ መሠረት በዳኝነት የሚጠይቁትን የገንዘብ መጠን ወይም የንብረት የዋጋ ግምት የመጥቀስ ግዴታ ተጥሏል፤
  • ስለ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ገንዘብ አከፋፈል በወጣው የ1945 ዓ.ም. አስራ ሁለተኛ ዓመት ቁጥር 15 የሕግ ክፍል ማስታወቂያ ቁጥር 177 መሠረት ከሳሽ የሆነ ወገን ዳኝነት በሚጠይቅበት ገንዘብ መጠን ልክ ለፍርድ ቤቶች የዳኝነት አገልግሎት ክፍያ ሊከፍል እንደሚገባና ተመኑም ተመልክቷል፡፡ በመሆኑም አንድን ንብረት አስመልክቶ የፍትሐብሔር ክስ የሚያቀረብ ሠው ለፍርድ ቤቶች የዳኝነት የአገልገሎት ክፍያ አከፋፈል እንዲያመች የንብረቱን የዋጋ ግምት በክስ አቤቱታው ላይ የመግለፅ ግዴታ አለበት፡፡
  • የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባወጣው የተሻሻለው የቅጣት አወሳስን መመሪያ ቁጥር 2/2006 መሠረት በፍርድ ጥፋተኛ በተባሉ ሠዎች ላይ ቅጣትን ለመጣል በወንጀል ድርጊት የተገኘውን የንብረት ጥቅም ግምት ወይም የደረሰውን የንብረት ጉዳት ግምት ማወቅ አስፈላጊ ከመሆኑም ባለፈ የተጠቀሰው ሕግ የንብረት የዋጋ ግምት መጠን ላይ ክርክር ከተነሳበት የዋጋ ግምቱ ተለይቶ እንዲጠቀስና እንዲቀርብ ይጠይቃሉ፡፡    
  1. በሕጉ መሠረት የንብረት የዋጋ ግምት ላይ ክርክር ከቀረበ ግምቱን የሚገምተው ማን ነው? የግምት ሥራውስ እንዴትና በምን መመዘኛ ይሰራል?

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 250 መሠረት ከተከራካሪ ወገኖች መካከል አንደኛው የሚያቀርበውን የዋጋ ግምት ሌላኛው ተከራካሪ ወገን በዋጋ ግምቱ ባለመስማማት ሊቃወም እንደሚችልና የግምት ክርክር ከተነሳ ደግሞ ፍርድ ቤቶች የሀብቱን ወይም የንብረቱን የዋጋ ግምት በመገመት ለፍርድ ቤቱ እንዲያሳውቁ ምትክ ዳኞችን በመሾም ሊያስገምቱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡ 

በፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ላይ የንብረት ዋጋ ግምት እንዲገምቱ የሚሾሙ ምትክ ዳኞችም የንብረት ዋጋ ግምቱን ምንን መሠረት በማድረግና እንዴት እንደሚከናወኑ የሚያመለክተው ነገር ባይኖርም ምትክ ዳኞቹ የግምት ሥራ ሲሰሩ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 132 እስከ 135 በተመለከቱ ቅድመ ሁኔታዎችና የአሠራር ሥርዓት መሠረት የዋጋ ግምቱን ገምተው ሪፖርት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

Continue reading
  15726 Hits

ንብረት የማፍራት እና ፍትሐዊ ዳኝነት የማግኘት መብት: ከወቅታዊው የሕገ-ወጥ መሬትና ንብረት ማስመለስና ማፍረስ ጋር በተያያዘ

አሁን አሁን በተለያዩ የሃገራችን ክልሎች በተለይ ደግሞ በአዲስ አበባ ዙርያ በሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ከተሞች ላይ ከዕለት ወደዕለት በዜጎች የመዘዋወር መብት፤ንብረት የማፍራት፤ የእኩልነት እና ፍትህ የማግኘት ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች በሕግ ማስከበር ሰበብ ሲጣሱ ማዬት የዕለት ተዕለት ተግባራዊ ኩነት እየሆነ መጥቷል፡፡

የዚህ አጭር ጽሑፍ መነሻ ነጥብም በሕግ ማስከበር ሰበብ ለረዥም አመታት ከማህበረሰቡ ጋር በመቀላቀል ሕገ-መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው ንብረት ያፈሩ ዜጎች ላይ በሕገ ወጥነት ሰበብ እየተወሰደ ያለውን ከገዛ ቤታቸውና ንብረታቸው የማፈናቀል እርምጃን በተመለከተ ዜጎች መብቶቻቸውን በሕግ አግባብ እንዴት ማስከበር እንዳለባቸው የሚያሳይ ፍኖተ ሕግ ነው፡፡

የህጉን ዝርዝር ነጥብ ከመመልከታቸን በፊት አሁን መሬት ላይ ያለው እውነትን በጨረፍታ ለመመልከት መሞከሩ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ በቅርቡ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች መካከል የሰበታ ከተማ አስተዳደር፤ የቡራዩ ከተማ አስተዳደር፤ የለገጣፎ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የሱሉልታ ከተማ አስተዳደር የከተሞቻቸውን የማስተር ፕላን ጋር ተቃራኒ የሆኑ እንዲሁም ቀድሞ ካሳ የተከፈላቸው እና በሕገ ወጥ መንገድ ከመንግስት እውቅና ውጭ ንብረት ያፈሩ ወይም በተለምዶ ወቅታዊ አጠራሩ ሕገ ወጥ ግንባታዎችን  አጭር የማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ነዋሪዎቹ ለዓመታት ይኖሩበት የነበረውን በጉልበታቸውና በጥሪታቸው ያፈሩትን ሃብቶቻቸውን በሃይል ድርጊት እንዲፈርስ በማድረግ በተጨባጭ ዜጎች ከሃብት ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ መደረጉ ለብዙ ቅሬታ መነሻ ነጥብ ሆኖ መገኘቱ ነው የዚህ ጽሑፍ መነሻ ነጥብ፡፡ በመሆኑም ዜጎች ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈጸምባቸው በምን አግባብ መብቶቻቻውን ማስከበር እንደሚችሉ ከኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት እና ከአዋጅ ቁጥር 721/2004 ጋር በማመሳከር ረጂ ናቸው ብዬ ያሰብኳቸውን ነጥቦች ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡  

በቅድሚያ የኢፌዲሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 25 መሰረት ማንኛውም ሰው ልዩነት ሳይደረግበት በሕግ እኩል ያልተነጣጠለ እና አድሏዊ ባልሆነ መልኩ ጥበቃ እንደሚደረግለትና  እኩልና ተጨባጭ የሕግ ዋስትና የማግኘት መብት እንዳላቸው በማያሻማ ቋንቋ የማይገረሰሰ ሰብዓዊ መብት እንደሆነ ደንግጎ ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ከጉዳያችን ጋር ተያያዥነት ባለው መልኩ በዚሁ ሕገ መንግስት አንቀፅ 32 ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በመረጠው የሃገሪቱ አካባቢ የመዘዋዋርና የመኖርያ ቤት የመመስረት እንዲሁም በፈለገው ጊዜ ከሃገር የመውጣት ነፃነት እንዳለውና በአንቀጽ 40/7ም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በመሬት ላይ ለሚገነባው ቋሚ ንብረት ወይም ለሚያደርገው ቋሚ መሻሻል ሙሉ መብት አለው በማለት እርስ በርስ ተመጋጋቢ እና ተደጋጋፊ በሆነ መልኩ የዜጎችን ንብረት የማፍራትና በሃገራቸው በነፃነት የመዘዋወር ዲሞክራሲያዊ መብቶችን በዝርዝር ይጠቅሳል፡፡

Continue reading
  10224 Hits
Tags:

Some Reflections on the Classification of Goods under the Ethiopian Civil code

In different legal systems of the world, properties are classified into different categories such as personal and real, private and public, movable and immovable, absolute and qualified, corporeal and incorporeal, etc. The distinction between these types of property is significant for a variety of reasons. Firstly, classification ensures the proper application of the law. This is because the legal regime that governs goods depends on their nature and accordingly their legal treatment substantially varies. For instance, one's rights on movables are more attenuated than one's rights on immovable (or real property). The statutes of limitations or prescriptive periods are usually shorter for movable than immovable property. Besides, real property rights are usually enforceable for a much longer period of time and, in most jurisdictions, real estate and immovable are registered in government-sanctioned land registers. More essentially, the manner for transfer of the possession or ownership of things depends on their nature. For example, the possession of ordinary corporeal chattels (movable things) may be transferred upon delivery. On the contrary, possession of immovable things requires more additional formalities like registration. In short, classification of property has a paramount importance in facilitating legal regulation of property rights and economic transactions.


When we come to the Ethiopian legal system, the classification of things is not that much clear. The law simply employs the term “good” which is primarily meant to refer the subject matter of property rights in most civil law countries as a bench mark to classify properties. Accordingly, under 1126 of the civil code it is provided that all goods are either movable or immovable. As Ethiopia is largely a civil law country, the use of the terms movable and immovable like other continental systems seems appropriate. Hence, the law recognizes goods as movable or immovable. The term “all” in this provision seems to signify that any thing to be regarded as good or any thing which is regarded as good must have either movable or immovable nature. In other words, a thing to be considered as subject matter of property right, i.e. good, in our legal system, it must fall in either of the class of immovable or movable things as defined by the law itself. However, as it is clearly provided in the Amharic version of the same provision, those goods which may be immovable or movable shall have material existence. The otherwise understanding suggests that at least in principle things to be considered as subject matter of property they must be tangible (corporeal); that can be perceived in our senses particularly that can be touched. Therefore, in the first glance the law seems to exclude incorporeal (intangible) things from the realm of property. Nevertheless, it puts exceptional instances in the subsequent articles where incorporeal things become goods after being assimilated with corporeal chattels (movable goods). In short, even if the law by definition excludes incorporeal things from the scope of property, it has also devised a mechanism where they may be regarded as goods, that is, by assimilating them with movable chattels.


Once the law classified goods as movable or immovable it also suggested what the terms should connote. Thus, under art.1127 it stipulates that corporeal chattels are things which have a material existence and can move themselves or be moved by man with out losing their individual character. Therefore, goods to be corporeal (tangible) movable thing, they must, first, be able to move by themselves or by the force of human beings. Second, when they are moving by themselves or are moved by human power they must not loss their natural (individual) feature, that is, their displacement or movement shall not result in the destruction of the whole or part of them or change of their physical feature. For instance, a marble which is already used for building may be movable, i.e. may be detachable from the building by using force. However, since in most cases, this result in some sort of destruction up on it, the marble may not be included in corporeal chattels. One top of this the law doesn’t seem clear when it says   “…with out losing their individual character”. What is the extent of losing individual character? Is any insignificant change capable of changing the nature of the thing? In our example above, what if the marble in the process of technical detachment slight crack occurred, will it be movable or remains an immovable? In the opinion of the writer, the intention of the legislator doesn’t seem to include slight changes but only those changes that outwardly affected the individual character, meaning, in our instance, any crack shall change the nature of normal marble may be that turns it to particles. In other words, as long as the change is not substantial, the nature of the thing shall not be changed.


On the other hand, article 1130 tries to describe immovables saying that ‘lands and buildings shall be deemed to be immovables’. Thus, unlike other legal systems, our civil code instead of defining immovables in general terms, it gives which things shall be regarded as immovables and it provided land and building as things that are deemed immovable. However, what about other things such as bridges and dams which are by nature immovable in the ordinary meaning of the term? Is the listing exhaustive or illustrative? In this regard two arguments may be raised; firstly, since the law doesn’t clearly say that ‘only’ land and buildings shall be deemed immovables, other things which are immovable by nature [in the literal meaning of the term] shall also be regarded as immovable in law. By contrast, it may be argued that the listing is exhaustive and no other thing shall be deemed immovable except land and buildings. To supplement the second argument, it may be said that in as long as the law doesn’t put the extent of ‘building’ (what things are referred as building?), we shall interpret it broadly  so as to include dams, bridges, fences  and the like in addition to houses. The general jurisprudence is just making land and any permanent establishment on land which can’t be moved from one location to another with out causing destruction upon it as immovable. In line with this, in whatever way the law is interpreted, it must include things such as fences, dams, bridges and the like as immovable goods so far as they are physically attached with the land and in a manner where it is impossible to displace them with out affecting their individual character.


Another point that the reader must also note is that when the law is referring to immovables it is only corporeals which have material existence by virtue of Art. 1126. As to incorporeal immovables like servitude, and others which are inseparable from the corporeal immovable such as land from which they develop as a right, though the law recognizes them under various provisions like art.1359 ff, it excluded them under article 1130 while describing what things are deemed immovable. Therefore, it doesn’t mean that these incorporeal immovables aren’t immovables because art 1130 is simply the follow up of art 1126 which sticks in classifying goods which have material existence (corporeals) only by excluding those which don’t have physical existence.

Continue reading
  13018 Hits
Tags: