በአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ መሠረት በተሰጠ የፍርድ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ የአፈጻጸም ክስ በይርጋ ቀሪ ስለሚሆንበት የሕግ አግባብ

መግቢያ

አፈጻጸም ማለት አንድ መብቱ በፍርድ ውሳኔ እንዲከበር ለፍርድ ቤት ክስ ያቀረበ ሰው የፍርድ ውሳኔ አግኝቶ በፍርዱ መሰረት ሳይፈጸምለት ሲቀር ፍርዱ የተፈረደበት ወገን እንደ ፍርዱ እንዲፈጽም የሚገደድበት የሕግ ሥርዐት ነው፡፡ ይህ ስርዐት የሚመራውም በፍትሐብሔር ሥነ- ሥርአት ሕግ ቁጥር 375 ጀምሮ በተደነገጉ ድንጋጌዎች መሰረት ሲሆን በእነዚህ የሕግ ማእቀፎች ተንተርሶ መብቱ እንዲፈጸምልት ሚጠይቅ ወገን የፍርድ ባለመብት ሲባል እንዲፈጽም የሚገደደው ደግሞ የፍርድ ባለእዳ ተብሎ ይጠራል፡፡

Continue reading
  12361 Hits

Hammering Labor Rights: Succinct Summary of the Draft Labor Proclamation

 

Synopsis

Labor is the most important activates of a human being crate both material productivity and social values. Now a day it is not a point of disagreement that the development of any given country is highly dependent upon high level of labor productivity, quality and efficiency. This being said, legally speaking labor right is one of the most fundamental human rights recognizing under various international instrument to which Ethiopia is a party. Furthermore, labor right is one of rights which patronizing to constitutional protection. The draft labor proclamation brought untold roaring from Ethiopia Workers Confederation Union (EWCU) and others stakeholders. This mini-article is meant to summarized and explore the draft labor proclamation.

Historical Background of Labor Right

Although the evolution of labor relations had witnessed considerable national varies even in Europe the general path of development display many similarities. As a general pattern of development, the landlord-tenant relationship and the guild society of the feudal mode of production gradually gave its way to capitalism.Under capitalism mode production the governing and overriding principle was freedom of contract.

Continue reading
  9593 Hits

የመንግሥት ሠራተኞች የሥራ ማቆም መብትና ሕገወጥ ተግባሮች ምንነት በኢትዮጵያ የሕግ ማዕቀፍ

 

የዚህ አጭር ጽሑፍ ዓላማ የሲቪል አቪዬሽን ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማና የፌዴራል ፖሊስ የእስር ዕርምጃ ተከትሎ በተለያዩ ሚዲያዎች በመንግሥት በኩል በተወሰዱት ዕርምጃዎች ዙሪያ እየቀረቡ ያሉ ሕግ ነክ አስተያየቶች ውይይቶች፣ ሰሞነኛ ክርክሮችንና ተያያዥ ነጥቦች መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ የመንግሥት ሠራተኞች ሕጋዊ የሥራ ማቆም መብት የሕግ ወሰን እስከ የት ድረስ ነው? የሚለውን ጥያቄ ከሕገ መንግሥት መሠረታዊ መርሆች አንፃር በመመልከት በመብቱ አፈጻጸም ላይ የሚነሱ አንዳንድ የሕግ ጉዳዮችን በአጠቃላይ በአገሪቱ የተለያዩ የአሠሪና ሠራተኛ መብትና ግዴታዎችን አስመልክቶ በፌዴራል መንግሥት በኩል ከወጡ ሕጎች አንፃር በመጠኑ መዳሰስ ነው፡፡

የሥራ ማቆም መብት ጽንሰ ሐሳብና በሕግ የተሰጠው ጥበቃ

የሥራ ማቆም አድማ ሠራተኞች በሕግ ዕውቅና ተሰጥቶት ያለ የኅብረትና በነፃነት የመደራጀት ሰፊ የሆነው መሠረታዊ መብት አንዱና ወሳኝ ከሚባሉት ውስጥ የሚጠቀስ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የሥራ ማቆም ዕርምጃ ሠራተኞች ለአንድ የተወሰነ ወቅት የሚሠሩትን ሥራ እንዲቋረጥ በማድረግ ለጋራ ፍላጎታቸው በአንድነት በመሆን አቋማቸውን የሚገልጹበት የመታገያ ሥልት ነው፡፡ በአጠቃላይ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ ሁኔታ ከሥራቸው ጋር በቀጥታ በሚገናኙ ማንኛውም ጉዳዮች በተለይም ደግሞ ከተቋማዊ፣ ከማኅበራዊና ከኢኮኖሚያዊ በቀጥታ በሚያያዙ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄያቸውን ሕጉን ተከትለው ለሚመለከታቸው መንግሥታዊ ውሳኔ ሰጪ አካላት የሚያቀርቡበትና ድምፃቸውን ለማሰማት የሚችሉበት የመደራደሪያ ሕጋዊ ሥልቶች ነፀብራቅ እንደሆነ ከሠራዊቶች የቡድን መብቶች ታሪካዊ አመጣጥና ከዳበሩት የሕግ ፍልስፍናዎች የተጻፉ ዓለም አቀፍ የሕግ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ይህም ሲባል መብትና ጥቅማቸውን አንድም በሚመሠርቱት የሠራተኛ ማኅበሮች በኩል ወይም በጋራ በመሆን አሠሪዎቻቸው ላይ ተፅዕኖ ለመፍጠር የሚያስችላቸው ሕጋዊ መንገድ እንደሆነ ዓለም አቀፍ የሠራተኞች መብትን ለማስጠበቅ ከወጡ ስምምነቶች መገንዘብ ይቻላል።

 የዓለም አቀፉን የሠራተኞች መብት በሕግ ጥበቃ ለማሰጠት ከወጡት የተለያዩ ስምምነቶች እንዲሁም አገሮች አባል የሆኑበት የበላይ ጠባቂ የሆነው ተቋም (International Labor Organization (ILO)) አማካይነት በየጊዜው ስለሠራተኞች በነፃነት የመደራጀትና የሠራተኛ ማኅበራት የመመሥረት መብት (Right to Organize & Collective Bargaining Convention (1948/51)) & Freedom of Association & Protection of the Right to Organize Convention) (1948/51)) አስመልክቶ በዝርዝር ከፀደቁት የሕግ ሰነዶች እያንዳንዱ አገሮች በውስጥ የሕግ ማዕቅፎቻቸው ተጨባጭ ሁኔታዎቻቸውን መሠረት በማድረግ ለመብቱ አፈጻጸምና አተገባበር ልዩ ሕጎች በማውጣት ሕጋዊ ጥበቃና ምቹ ሁኔታዎችን እንዲፈጥሩ ግዴታዎችን ያስቀምጣሉ፡፡   በተለይም ኢትዮጵያ አባል የሆነችበትና በ1987 ዓ.ም. በፀደቀው የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት ምዕራፍ 3 አካል የሆነው የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ መብቶችን ለመደንገግ የወጣው የቃል ኪዳን ሰምምነት (International Convenant on Economic, Social, and Cultural Rights (ICESCR)) የሠራተኞች አጠቃላይ መብቶችን በሚመለከት ልዩ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ከመሆኑም በተጨማሪ በቃል ኪዳን ስምምነት ሰነዱ አንቀጽ 8 ውስጥ የሥራ ማቆም ዕርምጃ የመውሰድ መብት የየአገሮቹን ገዥ ሕጎች ተከትሎ በሁሉም መስክ የሚገኙ ሠራተኞች ገደብ ሊጣልባቸው ከሚችሉት ከመከላከያ ሠራዊት፣ ከፖሊስና ከመንግሥት የአስተዳደር ሠራተኞች በስተቀር መብቱ ሳይሸራረፍና ያለአድልኦ በእኩልነት ሊከበር እንደሚገባው ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሆኖም አባል አገሮች በውስጥ ባላቸው ተጨባጭ ሁኔታዎች አንፃር በማገናዘብ በሕጎቻቸው ላይ የተወሰኑ ገደቦች እንዲሁም የሥራ ማቆም ዕርምጃ ፈጽሞ ማድረግ የማይቻልባቸውን ዘርፎች በሚመለከት በዝርዝር ሕግ መከልከል እንደሚችሉ ነገር ግን የሠራተኞች የጋራ መብት ፍፁምነት የሌለው ቢሆንም፣ እንኳን ገደብም ሆነ ክልከላ ለማድረግ የሚቻለው ቢያንስ ቢያንስ ግልጽ የሆኑትን ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኙ ሕጋዊ መሥፈርቶችንና አሠራሮች ጋር ተጣጥሞና መሠረታዊ የሆነውን የመብቱን ዓላማ በማይቃረን መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ያስረዳሉ፡፡

Continue reading
  11007 Hits

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 እና አንዳንድ ጉዳዮች

 

ከዚህ ቀደም በሀገራችን ኢትዮጵያ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይን የሚገዙ ሕጎች እንደነበሩ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በ1955 ዓ.ም የወጣው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 210/1955፣ በ1968 ዓ.ም የወጣው የሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 64/1968፣ የሠራተኛ ጉዳይ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 85/1968፣ ስለአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ የወጣው አዋጅ ቁጥር 42/1985 እና አዋጅ ቁጥር 377/1996 የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ከየካቲት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በግሉ ዘርፍ ያለውን የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነትና መስተጋብር እንደ ዋነኛ ምሰሶ በመሆን ሲያስተዳድር የነበረው ሕግ አዋጅ ቁጥር 377/1996 እና የዚህ አዋጅ ማሻሻያ ሕጎቹ አዋጅ ቁጥር 466/1997 እና አዋጅ ቁጥር 494/1998 ነበሩ፡፡ እነዚህ ሕጎች ከ14 አመታት በላይ በሥራ ላይ የዋሉ በመሆናቸው አሁን ካለው የማህበረሰብ እድገት ጋር የተጣጣሙ ባለመሆናቸው የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቀን ሰኔ 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባደረገው 4ኛ አመት የሥራ ዘመን 48ኛ መደበኛ ስብሰባው የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ረቅቅ አዋጅን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

ይህም ሕግ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ዓ.ም ሆኖ ነሐሴ 30 ቀን 2011 ዓ.ም በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በሥራ ላይ ውሏል፡፡ ይህ አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ምን ምን ሀሳቦችን አካቶ ነው የተሻሻለው? ለሠራተኛው ምን ዓይነት ሕጋዊ ጥቅምና መብቶችን አካቷል? እንዲሁም የአሠሪ ግዴታና መብት ምን ይመስላል? የሚሉትን ጉዳዮች እና አዲሱን አዋጅ ከተሻረው የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 በማነፃፀር በወፍ በረር (Bird’s Eye View) እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡

አዲሱ የአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ከዚህ ቀደም የነበረውን አዋጅ ከነ ማሻሻያዎቹ በመሻር እና የግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጄንሲ አዋጅ ቁጥር 632/2001ን በአዲሱ አዋጅ ውስጥ በማካተት ነው በሥራ ላይ የዋለው፡፡

Continue reading
  75228 Hits

በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወቅት የአሠሪና ሠራተኛ ግንኙነት - የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፕሮቶኮል አንድምታ

 

ዓለማችን ላይ የፈረንጆቹ 2020 የተወሳሰቡ ችግሮችን ይዞባት መጥቷል፡፡ ከቻይና ውሃን በትንሹ ተነስቶ በወራት ውስጥ ዓለምን ካዳረሰው የኮሮና ቫይረስ የሚስተካከል ችግር ግን ይመጣል ብሎ የገመተ አልነበረም፡፡ ይህ ቫይረስ በቀጥታ በሰው ልጆች ጤና እና ህይዎት ላይ እያሰከተለ ከሚገኘው ኪሳራ እና ውድመት በሚስተካከል ደረጃ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችንም እያስከተለ ይገኛል፡፡ ከአሜሪካ ስቶክ ማርኬት እስከ ኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ ከአውሮፓዊያኑ የንግድ ልውውጦች እስከ ኢትዮጵያ የአበባ ንግድ፤ ከካናድ የጥራጣሬ ግብይት እስከ አዲስ አበባ የአትክልት ተራ ንግድ ድረስ ብዙ መመስቃቀሎችን እያስከተለ ይገኛል፡፡ በዚህ መመሰቃቀል ውስጥ ብዙ አካላት ተጎጂ የሚሆኑ ቢሆንም በተለያዩ ሁኔታዎች ላይ ተቀጥረው እንደሚሰሩ ሰራተኞች ግን የችግሩ ቀጥተኛ ገፈት ቀማሽ አይገኝም፡፡ በተለይ ከአሜሪካ የቅጥር ገባያ እየሰማን እንዳለነው ብዙ ድርጅቶች ሰራተኞቻቸውን እየቀነሱ እያጋጠማቸው ያለውን የገንዘብ እጥረት በማቃለል ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ በሀገሪቱ የሚገኘውን የሥራ አጥ ቁጥር ወደ ስላሳ በመቶ እያደረሰው ይገኛል፡፡ ይህ ችግር ወደ ኢትዮጵያ መከሰቱ የማይቀር ነው፡፡ ብዙ የግል ድርጅቶች ስራቸውን ሙሉ ለሙሉ እያቆሙ በሚገኝበት በዚህ ጊዜ የሠራተኛን የደሞዝ ወጪ ያለምንም ችግር የመሸፈን አቅም ይኖራቸዋል ተብሎ አይጠበቅም፡፡    

ይሄን ችግር ከግምት ውሰጥ በማስገባት የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በዚህ ሳምንት መጋቢት /2012 ዓ/ም ከአሠሪዎችና ሠራተኛ ማህበራት ጋር በመነጋገር አሠሪዎች በዚህ ወቅት ለሰራተኞቻቸው ወጥ የሆነ ምላሽ እንዲሰጡ የሚያስችል የኮቪድ 19 የሥራ ቦታ ምላሽ (workplace Response) የተመለከተ ፕሮቶኮል (ፕሮቶኮል ወይም ፕሮቶኮሉ) አውጥቷል፡፡ የዚህ ፕሮቶኮል መነሻ የዓለም ስራ ድርጅት (አይ.ኤል.ኦ) በተፈጥሮ እና በሰው ሰራሽ አደጋዎች ሳቢያ ሀገራት እና የስራው ዓለም ሲጠቃ የቀውስ አስተዳደር ምላሽን በተመከተ በተቀመጠው ጋይድ ላይን መሰረት መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ይህ አጭር ዳሰሳ ፕሮቶኮሉ በአሠሪዎች እና በሰራተኞች ላይ የሚጥለውን መብትና ግዴታ ከማየት ባለፈ የፕሮቶኮሉን ህጋዊ አንድምታ እና መሰል ጉዳዮችን አይዳስስም፡፡

  1. ፕሮቶኮሉ ዓላማ

የፕሮቶኮሉ አሠሪዎች ያላቸውን ህልውና ለማስቀጠል የሠራተኛ የደሞዝ ወጭን በመቀነስ የሚወስዷቸውን እርምጃዎች እና ሰራተኞች ደግሞ በዚህ ወቅት ሊደርስባቸው የሚችለውን ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊ ቀውስ ከግምት ውስጥ በማስገባት የአሠሪውን ህልውና እና የሰራተኞችን ማህበራዊ ዋስትና በማመጣጠን ወጥ ምላሽን ለመስጠት ያለመ ነው፡፡ በፕሮቶኮሉ ላይ እንደተጠቀሰው የቫይረሱን ወረርሽን ባስተማማኝ መልኩ ለመከላከል እና ወረርሽኙ ቢከሰት ጉዳትን ለመቀነስ እንዲሁም ወረርሽኙ በሀገሪቱ ኢኮኖሚ፤ በድርጅቶች ቀጣይነትና ህልውና እና በሠራተኞች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ የሚፈጠረውን አሉታዊ ተፅዕኖ መቀነስ ነው፡፡

  1. የአሠሪ ግዴታዎች

ወረርሽኙን የመከላከያ እርምጃዎችን መውሰድ

Continue reading
  7018 Hits