አስገዳጁ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ የሕንጻ መደርመስን ይከላከለው ይሆን?

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ጉዳይ ልክ የዛሬ አመት ገደማ በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ስሙ ሰሚት በሚባል ስፍራ የተደረመሰውን ህንጻ እና እሱን ተከትሎ የከተማ አስተዳደሩ ባወጣው ደብዳቤ (circular) መሰረት አስገዳጅ የኮንስትራክሽን ኢንሹራንስ በድጋሜ እንዲኖር መደረጉን በማስመልከት ነው፡፡ ኢንሹራንስ (መድን) የሚለው ቃል ሲነሳ ምንግዜም ቢሆን ሊዘነጋ የማይችለውጉዳይ የአደጋ (risk) መኖር ነው፡፡ የአደጋ መከሰት ለመድን ቅድመ ሁኔታ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

  16404 Hits