የኑሮ ውድነት እና የሸማቾች መብት ጥበቃ በኢትዮጵያ ሕግ

በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 51 እና 55 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የፌደራል መንግሥቱ የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት እንደ ኢትዮጵያዊያን አቆጣጠር 2006 ዓ.ም የንግድ ውድድር እና የሸማቾች ጥበቃን በአንድ የሚመራ የሕግ ማዕቀፍ ያዘጋጀ ሲሆን የዚህ ሕግ አላማ ተደርገው በአዋጅ ቁጥር 813/2006 መግቢያ ላይ ከተቀመጡ ነገሮች አንዱ እና ዋነኛው ነገር ለሸማቹ ማህበረሰብ ጤናማ የሆነ የግብይት ሥርዓት መዘርጋት እና ከአወጣው ገንዘብ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ የንግድ እቃ ወይም አገልገሎት እንዲያገኝ ማስቻል ነው። ይህን ጠቅላላ አላማም በአዋጁ ውስጣዊ ክፍሎች በተካተቱ በርካታ የሸማቾች መብቶች እና የንግዱ ማህበረሰብ ግዴታዎች ድንጋጌ ተደራሽ ለማድረግ ተሞክሯል።

  12586 Hits