የሳይበር ክልልና የሀገሮች የለአላዊነት ስልጣን እስከ ምን ድረስ

የሳይበር ክልል ሲባል የኮምፒውተር ፕሮግራሞች፣ ዳታዎች፣ የኮምፒውተርና የቴሌኮምንኬሽን ግንኙነት፣ የኮምፒውተር ስርአትና በአጠቃላይ እነዚህ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ እንዲሁም ተጠቃሚዎችን የሚያካትት ክልል ነው በማለት በአጭሩ መግለጽ ይቻላል፡፡ ታዲያ ይህ ክልል የሀገሮች የፖለቲካ ይሁን የመልክአ-ምድር አቀማመጥ የማይገድበው እንዲሁም በሀገሮችና በህዝቦች መካከል ያለው የባህል፣ የቋንቋና የአኗኗር ዘዴ ጫና የማያሳድርበት ከመሆኑ አንጻር ክልሉን የሚመለከቱ ገና ምላሽ ያላገኙ በሀገሮች መካከል ለውዝግብና ያለመግባባት መንስኤ ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ ነጥቦች መከሰታቸው አልቀረም፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ይህን ዘርፍ እንዴትና በማን ይተዳደር፣ ዘርፉንስ ከህገወጦች እንዴት እንከላከል እንዲሁም በሀገሮችና ዜጎቻቸው ላይ ደህንነትና ጥቅሞች በህገ ወጦች ይሁን በአንድ አንድ የሀገር መንግስታት አመካኝነት አደጋ ሲቃጣ የሀገሮች ምላሽ ምን ሊሆን ይገባል ህገወጦችንስ ለፍርድ የማቅረብ ስልጣን የማን ሊሆን ይገባል በአጠቃላይ የሀገሮች ሉአላዊነት እንዴት ማስከበር ይቻላል እና የመሳሰሉትን ጉዳዮች ላይ ገና ምላሽ ያላገኙ ጥያቄዎች ይነሳሉ፡፡


ከዚህም ብዙም ሳንርቅ ለሳይበር ክልል መፈጠርና ማደግ በዋናነት ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ ካሉት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎች ውስጥ የኮምፒውተሮች ግንኙነት ወይም ደግሞ በይነ-መረብ በዋናነት ከሚጠቀሱ የቴክኖሎጂ ውጤቶች አንደኛው ነው፡ ይህ ዘርፍ ከሚሰጣቸው በርካታ አገልግሎቶችና ከተጠቃሚዎች ብዛት አንጻር በተጠቃሚዎች መካከል ልዩ ልዩ አለመግባባቶች ማጋጠማቸው አይቀርም፡፡ ለምሳሌ ከውል አፈጻጸም፣ የካሳ ጥያቄና አከፋፈል የዳኝነት ስልጣንና የመሳሰሉት አለመግባባትና ግጭቶች ያጋጥማሉ፡፡ ታዲያ እንደእነዚህ አይነት ግጭቶችና ያለመግባባት እንዴት ይፈቱ፡ በተለይም ደግሞ ሀገሮች ዘርፉን በመቆጣጠርና ማስተዳደር እንዲሁም የራሳቸውን ሉአላዊነት ከማስከበር ጋር ተያይዞ ያለባቸውን ክፍተት በመሙላት ረገድ ገና ምላሽ የሚያስፈልጋቸው ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ይነሳሉ፡፡


እንደሚታወቀው ማንኛውም ለአላዊ መንግስት በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና የሚሰጣቸው የሉአላዊነቱ መገለጫ የሆኑ ስልጣኖች አሉት፡፡ ይሄውም፣ አንድ ነጻ የሆነ የሀገር መንግስት እነዚህን የሉአላዊነቱን መገለጫ የሆኑትን ተግባራት በግዛቱ ውስጥ በሚገኙ ሰዎች፣ የሚንቀሳቀሱ ይሁን የማይንቀሳቀሱ ነገሮች እንዲሁም ክንውኖች ላይ ህግ የማውጣት፣ የወጣውን ህግ ተግባር ላይ እንዲውል የማድረግና ያወጣቸውን ህጎች ተጥሰው ሲገኙ ያለማንም ጣልቃ ገብነት ህግን የማስከበርና እንደነገሩ ሁኔታ አጥፊዎችንም ለፍርድ በማቅረብ የማስቀጣት ሙሉ የለአላዊነት ስልጣን አለው፡፡ በመሆኑም ሀገሮች አለም አቀፍ የሳይበር ክልል መፈጠርን ተከትሎ ይህንን የለአላዊነታቸው መገለጫቸው የሆኑትን ስልጣኖች በዚሁ ክልል ላይም ለመተግበር እንዲችሉ ልዩ ልዩ ጥረቶችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡


ይሁን እንጂ የአንድ ሀገር ለአላዊነት ስልጣን እስከምን ድረስ ሊሆን ይገባል በሚለው ላይ አንድ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ አልተቻለም፡፡ ስለሆነም፣ በዚህ ጉዳይ ላይ የተለያዩ ሙህራን የተለያዩ አስተያየቶች ይሰጣሉ፡ ለምሳሌ ይህ ዘርፍ በየትኛው ህግ ሊመራ ይገባል በሚለው ጉዳይ ላይ አንድ አንዶች እንተርኔት ሳይበር ክልል በለአላዊ ግዛቶች መካከል የቴክኖሎጂ፣ የህግና ስርአት ትስስር እንዲፈጠር የሚያደርግ ዘርፍ እንደመሆኑ መጠን ዘርፉ በየትኛው ህግ ሊተዳደር ይገበዋል ያልን እንደሆነ በነጻ ለኣላዊ ሀገሮች መካከል ያለውን ግንኙነት የሚመለከተው የህግ ክፍል አለም አቀፍ ህግ ነው፡፡ ስለሆነም፣ እንተርኔትም በዚሁ የህግ ማእቀፍ ሊተዳደር ይገባል የሚሉ ሙሁራን የመኖራቸው ያክል ሌሎች ደግሞ ልክ ነው በሀገሮች መካከል ላለው ግንኙነት በተመለከተ ግንኙነታቸው የሚመራው በአለም አቀፍ ህግና ስምምነቶች ነው ነገር ግን እንተርኔት የሀገሮች ግንኙነት ጉዳይ ብቻ አይደለም ዘርፉ ከሀገሮች ጋር ያለውን ግንኙነት ቁርኝት እንዲፈጠር በማድረግ አለም አቀፋዊነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህ ጉዳይ የሀገር ውስጥ ጉዳይም ጭምር ነው በቀጥታ በሀገር ደህንነት፣ ሰላም፣ ልማት፣ ዲሞክራሲ እድገትና ውድቀት ላይ ትልቅ ሚና ያለው ዘርፍ ነው፡፡


ስለሆነም ይህ ለአለም አቀፍ ግንኙነት ብቻ የሚተው ጉዳይ አይገባም፡፡ በሌላ በኩል ይህ ጉዳይ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ነው ስለሆነም የሀገሪቱ ህግ ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚ ይሁን ሊባልም የሚችል ጉዳይ አይደለም ምክኒያቱም የሳይበር ክልል በአንድ ሀገር ድንበር የታጠረ አይደለምና ነው፡፡ ለምሳሌ ከተጠቃሚዎች አንጻር ብንመለከተው የየትኛው ሀገር ተጠቃሚ የትኛውም ሀገር ካለው ተጠቃሚ ጋር ግንኙነት በመፍጠር መረጃ ይለዋወጣሉ ሀሳባቸውን ይገልጻሉ የንግድ እንቅስቃሴ ያካሂዳሉ ሌላው ቀርቶ ግንኙነታቸውን በማጠናከር ማህበራዊና ቤተሰባዊ ትስስር እስከመፍጠር ይደርሳሉ፡፡ ስለዚህም በአንድ ሀገር ህግና ደንብ መመራት አለበት የሚለውም በተወሰነ ደረጃ ልክ ሊሆን ቢችልም፣ ነገር ግን ዘርፉ የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ጉዳዮችን አጣምሮ የሚይዝ እንደመሆኑ መጠን፣ በሀገር ውስት ህግ ብቻ መተዳደር ይኖርበታል የሚለውም አግባብነቱ አጠያያቂ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ 

Continue reading
  7538 Hits
Tags:

የሳይበር ክልልና የሀገሮች የለአላዊነት ስልጣን እስከ ምን ድረስ ለሚለው ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ

አቶ ገብረመስቀል (Gebremeskes Gebrewahd) ወቅታዊ የሆነን ጉዳይ በማንሳትህ ላመሰግንህ እወዳለሁ፡፡ ባነሳኸው ጥያቄ ማለትም የሳይበር ክልል በሃገሮች ሉአላዊነት ላይ ምን ፋይዳ አለው? የሳይበር ክልል መተዳደር ያለበት በሃገራዊ ህግ ነው ወይስ በአለም አቀፍ ህግ? በሚሉ ጉዳዮች ላይ የኔ አስተያየት የሚከተለው ይመስላል። በኔ እምነት በቅድሚያ በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ግልፅ መሆን ያስፍልጋል።

·        የሳይበር ክልል ምን ማለት ነው?

·        የሳይበር ክልል ራሱን የቻለ አዲስ አለም (ክልል) ነው ወይ?

·        የሳይበር ክልል እንዴት ይተዳደራል (እንዴት መተዳደር አለበት)?

በሳይበር ክልል ላይ የሚሰጡ ትርጓሜዎች ብዙ ጊዜ የተወሳሰቡ፣ የተጋነኑ አንድ አንዴም ከእውነታ የራቁ መስለው ይታያሉ። የሳይበር ክልል ብዙ ጊዜ ከነባራዊው አለም ውጭ የተፈጠረ አዲስ አለም ተደርጎ ሲቀርብም ይታያል። “የሳይበር ክልል/አለም”  የሚለው ስያሜ በራሱ አሳሳች (misleading) ሊሆን ይችላል። እውነታው ግን የሳይበር ክልል ማለት ኢንተርኔት ማለት ነው። ኢንተርኔትስ ምን ማለት ነው? ኢንተርኔት እርስበርሳቸው የተሳሰሩ ኔትዎርኮች (inter-net) ማለት ነው። ኢንተርኔት የኮምፒውተሮች፣ መሳሪያዎች ወይም ዳታዎች ትስስር ሳይሆን የኔትዎርኮች ትስስር ነው። እነዚህ ኔትዎርኮች እርስበርስ በመተሳሰር አለም አቀፍ ኔትዎርክ (ኢንተር-ኔት) ይፈጥራል በዚህም በቢሊዮን የሚቆጠሩ ኮምፒውተሮች እና መሰል መሳሪያዎች እንዲገናኙ፣ መልእክት እንዲለዋወጡ ያስችላሉ። ስለዚህ የሳይበር ክልል = ኢንተርኔት= እርስበርስ የተሳሰሩ ብዙ ኔትዎርኮች (network of networks) ማለት ነው።

Continue reading
  11041 Hits
Tags:

የሳይበር ክልልና ሀገሮች ለአላዊነታቸውን ለማስከበር የሚከተልዋቸው መርህዎች

ሰላም እንዴት ናችሁ፡፡ በባለፈው ጽሁፌ የሳይበር ክልልና የሀገሮች የለአላዊነት ስልጣን እስከ ምን ድረስ? በሚል ርእስ አንድ ጽሁፍ አስፍሬ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ለዛሬ ደግሞ የሳይበር ክልል ለመቆጣጠር ሀገሮች በመከተል ላይ ያሉት መርህዎች ምን ይመስላል? የሚለውን ለማየት እሞክራለሁ፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሀለፎም ሃይሉ ለሰጡኝ ምላሽ አመሰግናለሁ፡፡


የአንድ ሀገር የለአላዊነት ስልጣን መገለጫ ከሆኑት ውስጥ አንዱ ስልጣን ባለው ሀገር የተሰጠውን ውሳኔ በሌላ አካል (ሀገር/ድርጅት) ሊከለስ ወይም ደግሞ ሊቀለበስ የማይችል ሲሆን ነው ከዚህ አንጻር ሀገሮች አንድን ጉዳይ የለአላዊነት ስልጣን አለን ወይም የለንም ብለው ለመወሰን የሚያስችልዋቸው ልዩ ልዩ መርህዎች አሉ፡፡ ለምሳሌ እንደ ግዛትን፣ ዜግነትን፣ ብሄራዊ ጥቅምን የአለም አቀፍ ስልጣንና የመሳሰሉትን መርሆዎችን በተናጠል ወይም አጣምረው በተግባር ላይ በማዋል የሀገሮቻቸውን ለአላዊነት ተጠብቆ እንዲኖር ያደርጋሉ፡፡ እነዚህን መርህዎች በሳይበር ክልል እንዴት ይተገበራሉ የሚለውን እንደሚከተለው ለመመልከት እንሞክራለን፡፡


ግዛትን መሰረት ያደረገ መርህ


አንድ አንድ ሀገሮች በሳይበር ክልል ውስጥ ለሚነሱ ግጭቶች ይሁን አለመግባባት ግዛትን መሰረት በማድረግ ለጉዳዩ መፍትሄ ማግኘት አለበት ብለው ያምናሉ፡፡ ይህም የሚሆነው ለጉዳዩ መነሻ የሆነው ጉዳይ የተፈጠረው በአንድ ሀገር ግዛት እስከሆነ ድረስ ምንም እንኳን ሌሎች ሀገሮች በድርጊቱ ጉዳት ደርሶባቸው ሊሆን ቢችልም ነገር ግን ግዛትዋ ላይ በመሆን የተፈጸመ እንደመሆኑ መጠን ለጉዳዩ መነሻ የሆነው ሀገር ህግንና ደንብ ተፈጻሚ መሆን አለበት፡፡ የሚል አስተሳሰብ አላቸው፤

ሆኖም፣ ይህ መርህ ለሳይበር ወንጀል ብቻ ሳይሆን በማንኛውም የወንጀል ድርጊት ተፈጻሚ መሆን ያለበት የህግ መርህ ቢሆንም ነገር ግን ከሳይበር ወንጀል ባህሪ አንጻር ሲታይ አንድ ወንጀል ሲፈጸም የበርካታ ሀገሮችን ቴክኖሎጂን በመጠቀም የወንጀል ድርጊቱ የሚፈጸምበት አጋጣሚ ያለ በመሆኑ ለወንጀሉ መፈጸም ግዛታቸውን ከተጠቀመባቸው ሀገሮች ውስጥ የየትኛው ሀገር ህግና ደንብ ተፈጻሚ ይሁን የሚለውን ጥያቄ በአግባቡ የሚመልስ አይደለም፡፡ ስለሆነም መርሁ ከሳይበር ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ጥያቄዎች የግዛት መርህ አግባብነት የለውም ብለው የሚተቹት ቢኖሩም ነገር ግን የግዛት ህግ መፈጸም አለበት ብለው የሚከራከሩ መርሁን ተፈጻሚ እንዲሆን የሚያግዙ ሁለት ንድፈ-ሀሳቦችን ያስቀምጣሉ፡፡ እነዚህም ንድፈ-ሀሳቦች የአውራጅና ጫኝ ንድፈ-ሀሳብና የሰርቨር ህግ ንድፈ-ሀሳብ ናቸው፡፡

Continue reading
  7952 Hits
Tags:

The State of Cybercrime Governance in Ethiopia

Introduction

Like many other countries around the globe, Ethiopia has embraced ICTs and ICT based services as key enabler for social and economic development in the country. Various efforts are also underway to significantly increase Internet connectivity speeds and access. But greater bandwidth will not only mean faster and better internet access but also faster and better means to launch cyber-attacks and opens more opportunities for criminals to exploit naïve users.


In this article I will try to explore the efforts and initiatives being made by the government in fighting cybercrime from three cyberspace governance perspectives namely cyber security-related policies and strategies, legislative frameworks, and institutional arrangements. I will also provide some recommendations on what the government should do so that appropriate plans and measures can be implemented to a safer and secure Ethiopia. 


1. Information Revolution and the New Form of Crime: Cybercrime


The dawn of the information age was proclaimed in 1991 by Alvin Toffler in his book The Third Wave. In this book, Alvin Toffler pointed out the history of the world to date can largely be portrayed as three waves namely the agricultural wave, the industrial wave and the information wave. The world is now at “the third wave” and owing to the revolution in information technology and this ‘third wave’ is called as information age. 

Continue reading
  23887 Hits
Tags: