The Right to Bail in Cases Involving Sexual Offences against Children

1 Introduction

This post was originally prepared for use in the internal publications of the Ethiopian Human Rights Commission in an effort to strengthen the engagement of the Commission in protecting and promoting the rights of victims of sexual offences while at the same time ensuring the due process rights of the accused. However, it never got to see the light of day for reasons unrelated to its content. Now that we are done with the adoption of a criminal justice administration policy and taking up the revision of the criminal procedure code, it may be time to give it another try.

Children are the most vulnerable individuals in our society; they are also the most precious commodity that the world has and have a right to be protected from all forms of abuse

2  Trends in the Prevalence of Sexual Offences against Children

Sexual offences, especially those against children, are among the least reported offences in countries like Ethiopia. This has to do with the private nature of the settings in which the offences take place, the relationship of vulnerability between the victims and perpetrators, cultural tolerance of some forms of sexual violence against children, inaccessibility of the formal legal system to child victims and their families and other structural causes. Whatever the case, it is impossible to draw a comprehensive picture of the prevalence of sexual offences against children in Ethiopia.

Continue reading
  11674 Hits

ፍርድ ቤቶች የዘነጓቸው አንገብጋቢ የተገልጋይ መብቶች

 

ፍርድ ቤቶች ሐምሌ 30 ሥራቸውን ካጠናቀቁ አንድ ሳምንት ሆናቸው፡፡ በየዓመቱ በክረምቱ አጋማሽ ተዘግቶ በመስከረም መጨረሻ የሚከፈተው ፍርድ ቤት ክረምት ጭር ይላል፡፡ የተወሰኑ የወንጀል ችሎቶችና ተረኛ ችሎቶች ካልሆኑ በቀር ፍርድ ቤቱ ከመደበኛው ሥራ ይቀዘቅዛል፡፡ አዲስ ፋይል መክፈት፣ አስቸኳይ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ (ለምሳሌ እግድ) መስጠት፣ ከበድ ያሉ የወንጀል ጉዳዮች ከመመልከት ውጭ መደበኛ ቀጠሮ አይስተናገድም፡፡ በዚህ በክረምት ወቅት ችሎቶቹ አይሠሩም ማለት እንጂ አስተዳዳሪዎቹ፣ ስለ ፍርድ ቤቶቹ የተሻለ አሠራር፣ የዳኞች አቅም የማጎልበት ሥራ፣ ስለ ሥራቸውና አገልግሎት አሰጣጣቸው የሚቀርቡ ቅሬታዎችን የማስተካከል ሥራ ላይ ይጠመዳሉ ተብሎ ይታሰባል፡፡ ፍርድ ቤቱ ልማዳዊ የፍርድ ቤት አሠራሮችን በማስቀረት፣ የዳኞችን ሥነ ምግባር በመቆጣጠር እንዲሁም ለተገልጋዮች ምቹ የሚሆንበትን ሥራ የሚያስብበት ወቅት በመሆኑ፣ በዚህ ጽሑፍ በፍርድ ቤቶች የተዘነጉ ግን ተገልጋዮችን እየጎዱ ባለ ልማዶችና አሠራሮች ላይ የተወሰነ ምልከታ ለማድረግ እንሞክር፡፡

የመፀዳጃ ቤቱ ነገር

መፀዳጃና ፍርድ ቤት ምን አገናኛቸው እንዳልይባል ከገጠመኝ ልጅምር፡፡ በልደታ ፍርድ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የተገልጋዮች መግቢያ በቀኝ በኩል ባሉት የድሮ ሕንፃዎች ጀርባ ሰዎች ተጣድፈው ሲገቡ ቀልቤን ሳቡኝ፡፡ ገንዘብ ቤት ወይም ኮፒ ቤት የሚሄዱ ቢመስልም ፍጥነታቸው የሚያሯሩጥ ሰው ያለ ነው የሚመስለው፡፡ ቀረብ ብዬ አንድ ወዳጄን ‹‹ሰዎቹ የት እየሄዱ ነው?›› ብዬ ስጠይቀው፣ ‹‹የተፈጥሮ ግዴታ ወጥሯቸው›› በማለት ሰዎቹ የሽንት ወረፋ ለመያዝ እንደሚቻኮሉ ነገረኝ፡፡ ከፍርድ ቤት ቅጥር ውጭም ባለጉዳዮችና ጠበቆች ሳይቀሩ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት ካለው ኒያላ ሆቴል ጀርባ ለሽንት ማዘውተራቸው የተለመደ ነው፡፡ ድንገት ተራቸው ደርሶ ከተጠሩ ‹‹ኒያላ ሆቴል ለሽንት ሄደው ነው›› ቢባል የሚረዳ ይኖር ይሆን? ፍርድ ቤቶቻችን በጤና መሥፈርት አንፃር ቢገመገሙ ኖሮ አሁን ካሉበት ደረጃ የባሱኑ ዝቅ ሊሉ እንደሚችሉ መገመት ይቻላል፡፡ በርካታ ባለጉዳይ የሚስተናገድበት ፍርድ ቤት ለባለጉዳዮች፣ ለጠበቆች፣ ለነገረ ፈጆች የሚሆኑ መታጠቢያ ቤቶችና የመፀዳጃ ቤቶች የላቸውም፡፡ አዲስ በተሠራው የልደታው ፍርድ ቤት ሕንፃ ሳይቀር ሽንት ቤት ባለመኖሩ ጠበቆችና ባለጉዳዮች ከፍርድ ቤት ውጭ በየካፌውና ሬስቶራንቱ ሲዞሩ ይውላሉ፡፡ በዚህ ዘመን ዘመናዊ ሕንፃዎች አይደሉም የገጠሩ ማኅበረሰብ እንኳን የመፀዳጃ ቤት እንዲያዘጋጅ በሚመከርበት ወቅት፣ ትናንሽ ግሮሰሪዎችና ካፌዎች እንኳን መፀዳጃ ቤት ለደንበኞቻቸው በሚያቀርቡበት ጊዜ ፍርድ ቤቶች ረዥም ሰዓት ለሚያስቆሙዋቸው ባለጉዳዮቻቸው የተፈጥሮ ግዴታቸውን የሚወጡበት ቦታ አለማዘጋጀታቸው ደንበኛ ተኮር እንዳይሆኑ አድርጓቸዋል፡፡ በሰኔ ወር በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በተዘጋጀ ጉባዔና የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር በሐምሌ አጋማሽ በፍትሕ ሚኒስቴር ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ጠበቆች ‹‹ኧረ የመፀዳጃ ቤቱን ነገር አደራ!!›› የሚል መልዕክት ለፍርድ ቤቶቹ አመራሮች አሰምተዋል፡፡ አንዳንድ ጠበቆች ከልምዳቸው እንደሚናገሩት ከፍተኛ ታዋቂነት ያላቸውና የውጭ ዜጎች ሳይቀሩ የመፀዳጃ ቤት ጥያቄ ባቀረቡ ጊዜ አለማስተናገዳቸው የፍርድ ቤቱን ገጽታ እንደሚያጎድፈው ይናገራሉ፡፡ ሕፃናትና ነፍሰ ጡሮች፣ አረጋውያንና የታመሙ ሰዎች በሚገኙበት ፍርድ ቤት ለአስቸጋሪ ሁኔታ የሚጠቅም መታጠቢያ ቤትና መፀዳጃ ቤት አለመኖሩ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ የድሮዎቹ ፍርድ ቤት ለዳኞች መፀዳጃ ቤቶችን ሲያዘጋጁ ባለጉዳዮቹንም አይዘነጉም ነበር፡፡ ለዚህ ነው በአዲስ ባልተተኩት የድሮ ሕንፃዎች ንጽህናቸው አጠያያቂ ቢሆንም፣ ለባለጉዳዮች ሽንት ቤቶች አዘጋጅተው የምናስተውለው፡፡ የሽንት ቤት ነገር የፍርድ ቤቶች አስተዳዳሪ አካል የክረምት የቤት ሥራ ይሆናል ብለን ተስፋ እናድርግ፤ ካልሆነ ጤና ጥበቃ የሽንት ቤቱን ጥያቄ በይግባኝ እንዳይመለከተው፡፡

ጊዜ ዋጋ የሚያገኘው መቼ ነው?

Continue reading
  12967 Hits
Tags:

The Role of ICT in Judicial Reform in Ethiopia

 


Introduction

Ethiopia has been implementing justice reform programs for more than 15 years now.  This program is comprehensive and includes all the justice institutions at the federal and regional levels.  Within each institution, the reform program incorporates various components. 

ICT is used as an important tool to achieve many of the objectives set in the justice reform program.  Thus ICT is not seen as an end by itself but as a means to achieve other justice ends.  The ICT system was locally designed, implemented and expanded within this mindset.  The current system used by the courts is quite advanced but it reached this stage by responding to growing justice needs some of which were created by the new ICT system itself.

 

Continue reading
  6939 Hits

የሰበር ሰበር ስልጣን በኢትዮጵያ የህግ ስርዓት ውስጥ ያለው እንድምታ፡- ህገ- መንግስታዊ መሰረትና በዝርዝር ህግ ውስጥ የሚካተትበት አግባብ

የኢትዮጵያ የህግ ስርዓት በተለያዩ የመንግስት የአስተዳደር ስርዓት ውስጥ በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ልዩነቶች ሲታዩበት የነበረ ቢሆንም አደረጃጀቱም የዚያኑ ያክል ተለዋዋጭነት የነበረው መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ በተለይም ከያዝነው ርዕስ ጋር በተያያዘ የፍርድ ቤቶች አደረጃጀትና በጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ውሰኔ የመስጠት ሂደት በተለያዩ ስርዓቶች የተለያየ ሂደት ሲኖረው ተስተውሏል፡፡ 1980ዎቹ አጋማሽ በፊት የነበሩት ስርዓቶች የአህዳዊ ስርዓትን የሚከተሉ ከመሆናቸው አንፃር የፍርድ ቤቶች አደረጃጀት በዚሁ አይነት አተያይ የተቀረፀ ነበር፡፡

በዘውዳዊው ስርዓት የነበረውን የፍርድ ቤቶች አደረጃጀት ስናይ በተሻሻለው ህገ መንግስት አዋጅ ቁጥር 149/1948 ምዕራፍ  6 ስለ ዳኝነት በሚዘረዝረው ስር  አንቀፅ 108 እና አንቀፅ 109 ስር የዳኝነት ስልጣን በህግ ለተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የተሰጠ እንደሆነ እና የጠቅላይ የንጉሰ ነገስት ፍርድ ቤትና እንዲሁም በህግ እንደሚወሰን ወይም እንደሚፈቀደው ሌሎች ፍርድ ቤት እንደሚኖሩ ይደነግጋል፡፡ ከዚህ ድንጋጌ አንፃር በሐገሪቱ አንድ ማዕከላዊ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሚኖርና ይህም በሐገሪቱ ለሚነሱ ጉዳዮች የመጨረሻ ውሳኔ እንደሚሰጥ እንዲሁም 1966 . የተዘጋጀው የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ረቂቅ አንቀፅ 120 መሰረት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሐገሪቷ የመጨረሻ ፍርድ ቤት እንደሆነና ይህም ህገ መንግስትን ጭምር የመተርጎም ስልጣን እንዳለው ይደነግጋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የይግባኝ ፍርድ ቤቶችና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች እንደሚኖሩ አስቀምፀጧል፡፡

 

በሌላ በኩል የኢትዬጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስትን ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 1/1967 ምዕራፍ 14 አንቀፅ 102 (12) በህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊኩ የበላይ የዳኝነት አካል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሆነና ይህም በሐገሪቱ ፍርድ ቤቶች ሁሉ የሚከናወኑ የዳኝነት ተግባሮች የመቆጣጠር ስልጣን ያለው መሆኑን ያስቀምጣል፡፡

ከእነዚህ  የሁለት ህገ መንግስት ድጋጌዎችና ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስትን ለማቋቋም ከወጣው አዋጅ ለመረዳት እንደሚቻለው በአህዳዊ ስርዓት ውስጥ አንድ የጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሚኖር እና ፍርድ ቤቱም የመጨረሻ ውሳኔ እንደሚሰጥ ያስረዳናል፡፡

Continue reading
  14403 Hits

የፍርድ ቤቶች የእግድ ትእዛዝ ተፈፃሚነት እስከየት ድረስ ነው?

 

 

ለአንድ ሀገር ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ መረጋገጥ እንዲሁም ሰብዓዊ መብቶች መከበር በሕግ አግባብ የተቋቋሙ ገለልተኛ፣ ነፃ፣ ተጠያቂነት ያለባቸው እና በሕዝብ ዘንድ አመኔታን ያተረፉ ፍርድ ቤቶች ሚና የጎላ እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ ያለሕግ እና ያለፍርድ ቤቶች ሰላም፣ ዲሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነትና ፍትሕ በአንድ ሀገር ውስጥ ይኖራል ብሎ መገመት አይቻልም፡፡

እነዚህ ፍርድ ቤቶች አሁን ባለው የሀገራችን ሕገ-መንግሥት ነፃ ሆነው መቋቋማቸውን እና በሀገሪቱ ውስጥ በፌዴራልም ሆነ በክልል ግዛቶች ሥር ብቸኛው የዳኝነት አካል እንደሆኑ ሕገ-መንግሥታዊ ማረጋገጫ አግኝተዋል፡፡ በዚህም አግባብ ሥራቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ፡፡

በሰዎችም መካከል አለመግባባት ሲፈጠር በሰላማዊ መንገድ በስምምነት፣ በድርድር ወይም በሽምግልና ወይም በእርቅ ለመፍታት ካልቻሉ ሥልጣን ወዳላቸው መደበኛ ወይም ሕጋዊ እውቅና ወደተሰጣቸው ፍርድ ቤቶች እንደሚሔዱ ይታወቃል፡፡

Continue reading
  10307 Hits

የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ አግባብነትን በተመለከተ

ግምቱ ተለይቶ የሚታወቅ የፍትሐ ብሔር ክርክር ጉዳይ በመያዝ በፍርድ ቤት ክስ የሚመሰርት ወይም የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ የሚያቀርብ ማንኛውም ተከራካሪ በፍትሐብሔር ሥነሥርዓት ሕግ ቁጥር 215/1 እና ስለ ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ገንዘብ አከፋፈል በ1945 ዓ/ም በተደነገገው ደንብ መሠረት የዳኝነት ክፍያ ይከፍላል። በዚህ ክሱን በከፈተበት ፍርድ ቤት በተሰጠው ውሳኔ ቅር የተሰኘ ተከራካሪ ደግሞ የይግባኝ አቤቱታውን ይግባኝ ለመስማት ሥልጣን ወዳለው ፍርድ ቤት ያቀርባል። ይህ የይግባኝ አቤቱታ እንዲሰማለት ደግሞ በሥር ፍርድ ቤት የከፈለውን የዳኝነት ክፍያ 50% መክፈል ይጠበቅበታል። የዚህ አጭር ማስታወሻ ዓላማም የዚህ የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ አግባብ የማይሆንበትን ኹኔታ መጠየቅ ነው።  

ከሶስቱ የመንግሥት አካላት አንደኛው የሆነው ፍርድ ቤት በተለያዩ ምክንያቶች (በማስረጃ ምዘና፣ በሕግ አተረጓጎምና አተገበባበር ወዘተ) ለተገልጋዩ/ለተከራካሪው ተገቢውን እና ትክክለኛውን አገልግሎት/ውሳኔ ባለመስጠቱ ምክንያት ተከራካሪው ውሳኔውን ለማሳረም የሚያወጣው የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ አግባብነት በሁለት ተከፍሎ ሊታይ ይገባል። ይኸውም፣ ይግባኝ ባዩ በሥር ፍርድ ቤት የተሰጠው ውሳኔ አግባብ አይደለም ተብሎ በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት የሚሻር ከሆነ፣ ቀድሞውኑ ወደ ይግባኝ የሄደው በሥር ፍርድቤቱ ሥህተት ነውና የከፈለው የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ ተመላሽ ሊደረግለት ይገባል። ነገር ግን የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ በይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤትም የሚፀና ከሆነ ይግባኝ ባዩ ላገኘው አገልግሎት የዳኝነት ክፍያውን ሊከፍል ይገባል።

ይህ የይግባኝ የዳኝነት ክፍያ ይግባኝ ባይ ጉዳዩ በይግባኝ ከታየለት በኋላ የረታ ወይም የቀድሞው ውሳኔ የተሻረለት ከሆነ የወጪና ኪሣራ ዝርዝር በማቅረብ ከተረቺው ሊጠይቅ ይችላል የሚል መከራከሪያ ሊቀርብ ይችላል። ነገር ግን ከዚህ ጋር በተያያዘ የሕጉ አንድምታ እና የሰበር ውሳኔዎች ትርጓሜ ሁል ጊዜ ተረቺ ወጪና ኪሣራ ሊሸፍን ይገባል የሚባለው ከቅን ልቦና ውጪ ሌላኛውን ተከራካሪ ለወጪ የዳረገ ተከራካሪ ካለ ብቻ ነው እንጂ በሁሉም ጉዳዮች ወጪና ኪሣራ ይሸፍናል ማለት እንዳልሆነ መገንዘብ ይቻላል። ከዚህ ባለፈም አሁን አሁን በሰፊው እየተለመደ የመጣው «ግራ ቀኙ ወጪያቸውን ይቻሉ» የሚል ትዕዛዝ ይህ እንዳይቻል ያደርጋል።

በመሆኑም፣ ይህ ሀሳብ ቢተገበር ሁለት ጥቅም አለው። አንደኛው ጥቅም አንድ ተከራካሪ ያለጥፋቱ በመንግሥት አካል (በሥር ፍርድ ቤት) በተሰራበት ስህተት በይግባኝ መንገላታቱ ሳያንስ ለተጨማሪ ወጪ ከመዳረግ የሚያድነው መሆኑ ነው። ከላይ እንደገለፅነው የውሳኔው በይግባኝ መሻር የሚያመላክተው የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ ሥህተት መሆኑን ነው። ሁለተኛው እና ዋነኛው ጥቅም ግን መንግሥት እንደማንኛውም ግለሰብ እና አገልግሎት ሰጪ ሁሉ ራሱ በዘረጋው አሰራር ከገዛ ራሱ ሥህተት ተጨማሪ ገቢ ማግኘት የለበትም የሚለውን መሠረታዊ የፍትሐዊነት ዕሳቤን በመተርጎም የፍትሕ ተደራሽነትን ማጎልበት ነው።

በአጭሩ የዚህች አጭር ማስታወሻ ድምዳሜ በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ታይቶ የተሻረ የሥር ፍርድ ቤት ውሳኔ ላይ የተከፈለ የዳኝነት ክፍያ ለይግባኝ ባዩ ተመላሽ ሊሆን ይገባል የሚል ነው፤ ምክንያቱም ለዚህ ወጪ የተዳረገው በሥር ፍርድ ቤቱ ሥህተት ነውና።

  6256 Hits

አዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ 1234/2013 ምን አዲስ ነገር ይዟል - በወፍ በረር

 

 

መግቢያ

የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ 1234/2013 በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የተቋቋመ 15 ከፍተኛ የሕግ ባለሙያዎችን በአባልነት ያካተተ የዳኝነት ሥርዓት አማካሪ ጉባኤ ረቂቁ ተዘጋጅቶ በፌደራል ፍርድ ቤቶች አመራሮች፣ በሕግ ባለሙያዎች እና በሕዝብ ተሳትፎ ዳብሮ ከሁለት አመታት ቆይታ በኋላ ጥር 13 ቀን/ 2013 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል።

ይህ አዲሱ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ 1234/2013 ከነባሩ የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 25/88 እና ይህን አዋጅ ካሻሻሉት ሌሎች አዋጆች ቁጥራቸው 138/1991፣ 254/1993፣ 321/1995 እና 454/1997 ከሆኑት አዋጆች ምን የተለየ አዲስ ነገር ይዞ መጥቷል? እንዲሁም ለአዳዲሶቹ ሕጎች መነሻ ዋና ዋና ምክንያቶቹስ ምን ምን ናቸዉ የሚለዉን በወፍ በረር እንመልከት።

Continue reading
  21387 Hits
Tags:

የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ስልጣን ከአዲሱ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ አንፃር

 

በአሁን ሰዓት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሁለት የከተማ አስተዳደሮች ማለትም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም የከተማ አስተዳደሮች ህጋዊ ጥንስሳቸው የአዲስ አበባ ከተማ ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያለው ሲሆን የድሬዳዋ ከተማ ደግሞ የቻርተር መሰረት ያለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት በኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 49 (1) መሰረት የፌዴራሉ መንግስት ርዕሰ ከተማ አዲስ አበባ ነው በማለት ለከተማው እውቅና ሰጥቷል፡፡ የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 49 (2) የአዲስ አበባ ከተማ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ስልጣን እንዳለውም ደንግጓል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 የድሬዳዋ ከተማን በማቋቋም እራሱን በራሱ እንደሚያስተዳድር ደንግጓል፡፡

ማንኛውም የከተማ አስተዳደር እራሱን በራሱ ሲያስተዳድር በህግ አግባብ የተቋቋሙ ሶስቱ የመንግስት አካላት ማለትም ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈፃሚና ህግ ተርጓሚ አካላት ይኖራቸዋል፡፡ በዚህም አግባብ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቻርተር አዋጅ ቁጥር 361/95 እንዲሁም የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በቻርተር አዋጅ ቁጥር 416/96 መሰረት የራሳቸውን የከተማ ፍርድ ቤቶች አቋቋመው በስራ ላይ ይገኛሉ፡፡ የከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ማለት የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤቶች ማለት እንደሆነ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀፅ 2 (10) በግልፅ አመላክቷል፡፡

እነዚህ የከተማ ፍርድ ቤቶች የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 በስራ ላይ ሲውል ስልጣንና ሀላፊነታቸውን በማሻሻል ብቅ ብሏል፡፡ እነዚህ የከተማ ፍርድ ቤቶች ምን አይነት አዲስ ስልጣን ተጨመረላቸው?፣ በፍትሐብሄር እና በወንጀል ጉዳዮች ስልጣናቸው እስከምን ድረስ ነው? እና በተጨመረላቸው ስልጣን ምክንያት የስራ ጫና ሊኖር ስለሚችል ምን አይነት ዝግጅት ማድረግና በህዝብና በተገልጋዩ ማህበረሰብ አመኔታ ያላቸው ፍርድ ቤቶች ለመሆን ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል የሚሉትን እንደሚከተለው በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡

 

Continue reading
  9804 Hits

ሕዝባዊ ፍርድ፣ ፍርድ ቤቶች እና ገላጋይ ዳኞች

 

የፍርድ ቤቶችን ችግር ለመፍታት፣ ጫናቸዉን ለመቀነስ፣ የሚያቀርቡትን የዳኝነት አገልግሎት ጥራት ለመጨመር ከሚቀርቡት የመፍትሄ ሃሳቦች መካከል አማራጭ የሙግት መፍቻ ስልቶችን (ለምሳሌ ግልግል ዳኝነት) ማበረታት ነዉ።

አማራጭ ስልቶችን ማበረታታት ተገቢ ነዉ፣ ጠቃሚ እስከሆነ ድረስ።  ነገር ግን ፍርድ ቤቶች በችግሮች በተተበተቡበት ሁኔታ፣ ምንም እንኳን ሕጉ ለአማራጭ ስልቶች እውቅና እና ድጋፍ ቢሰጥም፣ የፍድ ቤቶችን ችግር በመፍታት ወይም አለመግባባትን በመቀነስና በመፍታት ረገድ ግን የሚፈይደው ነገር ጥቂት ነው፡፡

የፍርድ ቤቶች መጠናከር ነዉ ቅድሚያ ሊስጠዉ የሚገባዉ። ፍርድ ቤቶች ሲጠናከሩ (ለምሳሌ በፍጥነት ዉሳኔ ሲሰጡ፣ ዉሳኔዎቻቸዉ ግልጽ፣ ተደራሽ፣ ተገማች ሲሆኑ፤ ሙስና ሲቀንስ) ብቻ ነዉ፤ ግለሰቦችና ድርጅቶች ሌሎች አማራጭ የግጭት መፍቻ ስልቶችን ሊጠቀሙ የሚችሉት። ፍርድ ቤት ቢሄዱ፤ መቼ፣ እና ምን አይነት ዉሳኔ፣ በምን ዋጋ ማግኘት እንደሚችሉ መገመት ሲችሉ ብቻ ነዉ አማራጭ መንገዶችን ለመጠቀም ሊወስኑ የሚችሉት።

ወደ ፍርድ ቤት ነዉ የሚሄዱት። ፍርድ ቤቶችራሳቸዉ በችግሮች በተተበተቡበት ሁኔታ፣ ምንም እንኳን አንደኛዉ ወገን ዉጭ በገላጋይ ዳኞች መዳኘት ቢፈልገም፣ ሌላኛው በተለይ ደግሞ የፍርድ ቤቶችን ችግር የሚፈልገው ላይስማማ ይችላል፡፡ በዚህም የበለጠ ፍርድ ቤት እንዲጨናነቅ ያደርገል፡፡

Continue reading
  9349 Hits

የሰበር ዓላማ ወጥነትን ማስፈን ወይስ ሕገ-ወጥነትን ማስፋፋት?

 

ጊዜው እ.ኤ.አ 1954 ነው፡፡ ለአለም ሀገራት የዲሞክራሲ አርአያና መምህር ነኝ ብላ በምትደሰኩር በአሜሪካ ሀገር ነጭና ጥቁር ተማሪ በአንድ ላይ አይማርም ነበር አሉ፤ ምክንያቱም ጥቁር ተማሪ ከነጭ ተማሪ ጋር በአንድ ላይ እንዲማር መፍቀድ ማለት በነጭ ተማሪዎች ሞራልና ክብር መቀለድ ነው ብላ ታምን ነበር፤ አሜሪካ፡፡ በመሆኑም ጥቁሮችና ነጮች ተለያይተው ይማሩ ነበር ማለት ነው፡፡ በዚሁ አይን ያወጣ አድልዎ የተበሳጨው ብራውን የተባለው ግለሰብ በአሜሪካ ሀገር የካንሳስ ክልል የትምህርት ጉዳይ ቦርድን በፍርድ ቤት ገተረው፡፡ ሚስተር ብራውን ለጥቁሮች ሽንጡን ገትሮ ከተከራከረ በኃላ ጥቁሮችን አንገት የሚያቀና ፍርድ አስፈረደ፡፡ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጥቁርና ነጭ ተማሪዎች ተለያይተው እንዲማሩ ማድረግ የሰው ልጆች በተፈጥሮ እኩል ሆኖው የመፈጠር መብትን የሚቃረን በተለይም ደግሞ የጥቁሮች ክብርና ሞራል የሚነካ እኩል የትምህርት እድል የሚነፍግ ህገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ ከተፈጥሮ ሕግና የአሜሪካ ህገ መንግስት ጋር የሚጣረስ ነው ሲል ለሰው ልጆች እኩልነት የሚያረጋግጥ ፍርድ ሰጠ፡፡ ጥቁሮች ከነጮች ጋር ያለአድልዎና ልዩነት ሳይደረግባቸው እኩል የትምህርት እድል የማግኘትና የመማር መብት አላቸው የሚል መደምደሚያ ላይ ተደረሰ፡፡ በዚሁ ውሳኔ የተበሳጨው "ጆርጅያ ኩሪዬር" የተባለ ጋዜጣ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በመቃወም ዳኞችን እንዲህ ሲል ገለፃቸው፡፡

“No man knows today what his rights are in this country. No man today has any liberties left. His rights and his liberties are in the laps of the nine crazy men who sit on the Supreme Court bench. And the lord only knows what these crazy men will do next. Today they are most dangerous tyrants that ever existed. Like Hitler, Mussolini, and the other modern day tyrants, they are mentally deranged. They are crazed with a desire to serve a minority for political purposes. Their insanity has made them unscrupulous in the methods they have employed to do the bidding of this minority. They are mentally deranged tyrants ruling as unscrupulously as any tyrant in all of history. The members of this court must be curbed or they must be removed from the bench.”

ትችቱ ወደ አማርኛ ስንመልሰው በዚች ሀገር መብቱን እና ነፃነቱን የሚያውቅ ሰው የለም፡፡ ነፃነቱንና መብቱን በጠቅላይ ፍርድ ቤት ወንበር ቁጭ ባሉ በእነዚህ  ዘጠኝ ያበዱ ዳኞች እጅ ላይ ነው፤በቀጣይም እነዚህ እብድ ዳኞች የሚሰሩት ነገር ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ አሁን በዘመናችን አይተነው በማናውቅ ሁኔታ እነዚህ ዳኞች አደገኛ አምባገነኖች ናቸው፤እንደ እነ ሂትለር፣ሙሶሎኒና ሌሎች ዘመናዊ አምባገነኖች በጭካኔ ያበዱ ናቸው፤ለፖሊቲካ አላማ ሲባል አናሳ ማህበረሰብን ለማገልገል አብደዋል፡፡ እብደታቸውን አናሳውን ለማገልገል ይሉኝታ እንኳን ሊገድበው አልቻለም፤እነዚህ ሰዎች ሊወገዱ ይገባል ለማለት ነው፡፡ (ትርጉም የራሴ)

እኔ ደግሞ እላለሁኝ፡፡ ያበዱት ዳኞቹ ሳይሆን ጋዜጣውን ያወጣው ፀኃፊ ራሱ ነው፡፡ ይህ ጋዜጣ በወቅቱ ይዞት የወጣ ትችት ብሽቅ እና በዘረኝነት የተነዳ ከአንድ ዲሞክራሲያዊት ሀገር ፈፅሞ የማይጠበቅ ነው፡፡ የእብደት እብደት፡፡ ይህ ማለት ከፍትህ እና ከእኩልነት አንፃር የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ ከትክክልም በላይ ነበር፡፡

Continue reading
  7596 Hits